Sunday, October 31, 2010

ጉድና ጅራት ከወደኃላ ነው እንዲሉ

የርሶ ብዕር አስተያየት ተሳትፎ ሕብረተሰባችንን ይጠቅማል ያሉትን አይንፈጉን ገንቢነቱ ቦታ ይኖረዋልና!

ማሳሰቢያ፡ ይህ ገጽ የተዘጋጀው የተለያዩ የኅብረተሰባችንን ሀሳብ ለመለዋወጫ እንጂ ለሚሰጡት ማንኛውም አስታየቶች በማንኛውም መንገድ ተጠያቂ አይደለም። ጉግል ድርጅትም ኃላፊነት አይወስድም። ኃላፊነቱ በሙሉ የአስታየት ሰጪው ብቻ ነው።


ጉድና ጅራት ከወደኃላ ነው እንዲሉ!

የተወደዳችሁ የገጻችን ተከታታዮች እንደምን አላችሁ? እኛ በእርሱ ጸጋ ለዚህ ላደረሰን እግዚሀብሔር ለገናናው ስሙ አሁንም እስከዘላለሙ ክብር ምስጋና ይሁን። አሜን።


ጋሼ ተኮላ (ተኩላው) ስለ ቀድሞው መሪያችን ቢል ክሊንተን መጽሀፍ በእርግጠኝነት አንብበህ በሚገባ ተረድተህ በራስህ የተረጎምከውን ስላካፈልከን እውነት ከሆነ በርታ በማንበብ ብዙ እውቀት ይገበያልና። ነገር ግን እንግሊዘኛ ችሎታህ ተርጉሞ ለሌላ ለማካፈል ቀርቶ ለራስህም ለመረዳት ገና ዳዴ እያልክ ነህና የተሳሳተ ትርጉም ላለመጨበጥ የቋንቋ ዕውቀትህን ለማሳደግ የግድ ትምህርት ለመቁጠር ወደ ባለሙያዎቹ መዝለቅ እንደሚገባህ እያካፈልንህ፣ ይህ ባይቻልህ እውቀቱ ያላቸው በትርጉሙ ቢረዱህ መልካም ነው። ትርጉም እራሱን የቻለ ሙያ ነውና።  ባለፈው ወዳጅህ ቀዳዳው ከዳኛ አንደበት የሰማውን የእንግሊዘኛ ቃል “እስብሊት“ የሚለውን አብሮህ ሲጨፈላልቀው ከርሟልና። በተለይ እያንዳንዱ የቃላት ሕጋዊ ትርጉሙ ጥንቃቄ እንድናደርግ
ለማሳሰብ ነው። ከዚህ ሌላ ዛሬም መዋሸት ይብቃህ ፣ ዕድሜ አልመክርህ ብሎህ ሰው በጣፈው ከመናገር የራስህን ደግመህ ደጋግመህ በየጊዜው የጣፍከውን ወደ ኃላ ተመልሰህ አንበው። ከስህተትህም ተማር‘። ‘ሀሰት አድርጌ ጥፌ ተገኝቼ ስለጠቆማችሁኝ አመሰግናለሁ‘ ብቻ ብትጥፍ እኛም ከሰው ስህተት አሊያም የሚሰራ ሰው ብለን በዘለልነው ነበር። ከኛም ጥሁፍ ሀሰት ካገኘህበት ጠቁመን በደስታ ለማስተካከልና ካለፈው ለመማር ወደኃላ የማንል ለመሆናችን ካንተ በላይ ዋቢ አንፈልግምና።

ከዚህ በመቀጠል ወደ እርዕሳችን ስንመለስ “ጉድና ጅራት ከወደኃላ እንዲሉ“ በቅርቡ የተጀመረው “http://www.dfwethiopiancommunity.blogspot.com/ “ ገጽ ጥሁፍ አጣጣሉ ወደፊት እንደኛ በሂደት እያደገና ተወዳጅነትን እያተረፈ እንደሚመጣ ተስፋችን ከፍተኛ ነው። በውስጡ አልፎ አልፎ የሚላመጥ ፍሬ አለው፤ በትላንትናው ጥሁፉ ባስነበበው ግን “ እግዚኦ “ የሚያሰኝ ነውና ፤ ኽረ ዳላስ ላይ ምን አደንዛዥ በሽታ ነው በኢትዮጵያ ተወላጆች መካከል የገባው? ምን አይነት ጉድ ይዛችሁ ነው የምትኖሩት? ለመሆኑ በወገኑ ላይ ይህ አይነት በደል ሲፈጸም የሚችል አንጀት መቼ ተጀመረ? ምን አይነት ልቦና ይዛችሁ ነው አብራችሁና አቅፋችሁ የምትኖሩት? በከተማው ያላችሁ የተማራችሁም ሆነ ያልተማራችሁ ፤ ወጣቶችም ሆነ አዛውንት ነን የምትሉ ሁሉ ፤ የሀይማኖትም ሆነ የግብረ ሰናይ ድርጅት ወይም የሰብአዊ መብት አባላትም ሆነ የሕግ ሙያተኞች የሆናችሁ የኢትዮጵያ ተወላጅና ወዳጆች ሁሉ የሞራልና የሕግ ግዴታችሁን ትወጡ ዘንድ እያሳሰብን አስቸኳይ እርምጃ እንደምትወስዱ  ተስፋ እናደርጋለን። እኛም የሞራልና የህግ ግዴታ ስላለብን መረጃዎች በእጃችን እንደገቡ ለዳላስ ካውንቲ አቃቤ ጽ/ቤት በማስተላለፍ ጉዳዩ በዚያ ተመርምሮ የህግ መጣስ ካለበት አግባባዊ እርምጃ እንዲወሰድ የተቻለንን ሁሉ እንደምናደርግ ቃል እንገባለን።

እርሶስ ምን ይላሉ?

Saturday, October 30, 2010

ጳውሎስ በቃለ ጉባዔው ላይ አልፈርምም አሉ

የርሶ ብዕር አስተያየት ተሳትፎ ሕብረተሰባችንን ይጠቅማል ያሉትን አይንፈጉን ገንቢነቱ ቦታ ይኖረዋልና!

ማሳሰቢያ፡ ይህ ገጽ የተዘጋጀው የተለያዩ የኅብረተሰባችንን ሀሳብ ለመለዋወጫ እንጂ ለሚሰጡት ማንኛውም አስታየቶች በማንኛውም መንገድ ተጠያቂ አይደለም። ጉግል ድርጅትም ኃላፊነት አይወስድም። ኃላፊነቱ በሙሉ የአስታየት ሰጪው ብቻ ነው።



የሚቀጥለው የተገኘው ከደጀሰላም ጦመር ላይ መሆኑን በቅድሚያ እንገልጻለን
OCTOBER 30, 2010

ሰበር ዜና:- አቡነ ጳውሎስ በቃለ ጉባዔው ላይ አልፈርምም አሉ
አርእስተ ዜና
(ደጀ ሰላም፤ ኦክቶበር 30/2010፤ ጥቅምት 20/2003 ዓ.ም):-
አቡነ ጳውሎስ ሐውልቱ እንዲፈርስ የታዘዘበትን እና የሁሉም ሊቃነ ጳጳሳት ስምምነት የተገለጸበትን ውሳኔ በያዘው ቃለ ጉባኤ ላይ ‹‹አልፈርምም›› በማለት እና ሲጠየቁም ዝምታን በመምረጥ ቀድሞ ሲገለጽ በቆየው እምቢታቸው ጸንተዋል፡፡

አቡነ ይሥሐቅ

አቡነ ጎርጎርዮስ
 ከፓትርያሪኩ ጋራ ሌሎች አራት ሊቃነ ጳጳሳትም በተለያየ ምክንያት የሐውልቱ መፍረስ የተገለጸበትን ቃለ ጉባኤ አልፈረሙም፡፡ ሲኖዶሱ ከ43 ያላነሱ በአገልግሎት ላይ የሚገኙ ጳጳሳት እና ሊቃነ ጳጳሳት በአባልነት ይገኙበታል፡፡
 የጠቅላይ ቤተ ክህነቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ ብፁዕ አቡነ ፊልጶስ የሐውልቱን ማስፈረስ ውሳኔ እንዲያስፈጽሙ በስማቸው ተለይቶ በመግለጫው ላይ መስፈሩን በመቃወም ለመፈረም ፈቃደኛ አልሆኑም፡፡ ብፁዕነታቸው ‹‹ከእኔ ስም ይልቅ ቢሮው ነው መጠቀስ ያለበት›› የሚል አቋም እንዳላቸው ተነግሯል፡፡
 አቡነ ይሥሐቅ፣ አቡነ መቃርዮስ እና አቡነ ጎርጎርዮስ (ከዚህ በፊት ሐውልቱን ሲቃወሙ ቆይተዋል) ‹ፓትርያሪኩ ሳይፈርሙ በፊት አንፈርምም› በሚል እና ሌሎች ምክንያቶች ለመፈረም ፈቃደኛ አልሆኑም፡፡
 በሕገ ቤተ ክርስቲያን ስለ ቅዱስ ሲኖዶስ የስብሰባ ሥነ ሥርዐት አንቀጽ ሁለት ንኡስ አንቀጽ 4/ሀ ሃይማኖትን እና ቀኖና ቤተ ክርስቲያንን በሚመለከት ጉዳይ ከጠቅላላው አባላት ከአራት ሦስቱ እጅ በተገኙበት ሲኖዶስ በማድረግ በሙሉ ድምፅ ውሳኔ ማሳለፍ እንደሚገባ ተደንግጓል፡፡
በሕገ ቤተ ክርስቲያኑ አንቀጽ 15 ንኡስ አንቀጽ 1 ፓትርያሪኩ በተሰጠው ሐላፊነት መሠረት ሃይማኖትን እና ቀኖና ቤተ ክርስቲያን የመሠበቅ እና የማስጠበቅ፤ በአንቀጽ 16 ንኡስ አንቀጽ 1 መሠረት ደግሞ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን ሃይማኖት የሚያፋልስ፣ ቀኖና ቤተ ክርስቲያንን የማይጠብቅ፣ ቤተ ክርስቲያንን የሚያስነቅፍ ተግባር ፈጽሞ ከተገኘ፣ ታማኝነቱ እና ተቀባይነቱ በካህናት እና ምእመናን ዘንድ ተቀባይነት ያጣ ሆኖ ይህም በትክክል ከተረጋገጠ በቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ ከሥልጣን እንደሚወርድ ተደንግጓል፡፡
ፓትርያሪኩ ዛሬ ዘጠኝ ሰዓት ላይ በተጠራው ጋዜጣዊ ጉባኤ በቅዱስ ሲኖዶሱ አባላት ስምምነት የተደረሰበትን መግለጫ እንደሚያነቡ ይጠበቃል፡፡ መግለጫውን ለማንበብ ፈቃደኛ ካልሆኑ ብፁዓን አባቶች የወከሉት የሲኖዶሱ አባል እንዲያነቡት ይደረጋል ተብሏል፡፡

Wednesday, October 27, 2010

አቡነ ጳውሎስ ሐውልት እንዲፈርስ

የርሶ ብዕር አስተያየት ተሳትፎ ሕብረተሰባችንን ይጠቅማል ያሉትን አይንፈጉን ገንቢነቱ ቦታ ይኖረዋልና!

ማሳሰቢያ፡ ይህ ገጽ የተዘጋጀው የተለያዩ የኅብረተሰባችንን ሀሳብ ለመለዋወጫ እንጂ ለሚሰጡት ማንኛውም አስታየቶች በማንኛውም መንገድ ተጠያቂ አይደለም። ጉግል ድርጅትም ኃላፊነት አይወስድም። ኃላፊነቱ በሙሉ የአስታየት ሰጪው ብቻ ነው።


ቅጂ ከሪፖርተር

(በየማነ ናግሽ)

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ትናንት በዋለው ዓመታዊ ስብሰባ፣ በቦሌ መድኃኔአለም ቤተክርስቲያን ቅጥር ጊቢ ተሰርቶ የነበረው የፓትርያርክ አቡነ ጳውሎስ ሐውልት እንዲፈርስ፣ ከኢትዮጵያ ሚሌኒየም ጊዜ ጀምሮ በየቤተክርስቲያኑ ቅጥር ግቢዎች የሚገኙና ምስላቸውን የያዙ ቢልቦርዶች እንዲነሱ መወሰኑን ምንጮች ለሪፖርተር ገለጹ፡፡ ካለፈው ዓርብ ጥቅምት 12 ቀን 2003 ዓ.ም. ጀምሮ ቅዱስ ሲኖዶሱ ባካሄደው ዓመታዊ ስብሰባ ከፓትርያርኩ ጋር በተያያዘ ውሳኔዎችን ያስተላለፈ ሲሆን፣ በአዲስ አበባ ቦሌ መድኃኔአለም ቅጥር ጊቢ የሚገኘው በፓትርያርኩ ምስል የተሠራው ሐውልት፣ ከቤተክርስቲያኗ ሕግጋት ውጪ ነው በሚል እንዲፈርስ ቅዱስ ሲኖዶሱ በሙሉ ድምፅ መወሰኑን ምንጮች ገልጸዋል፡፡

እንደ ምንጮቹ ገለጻ ከሆነ፣ ቅዱስ ሲኖዶሱ በዚሁ ዓመታዊ ስብሰባው ከትናንት በስቲያ በፓትርያርኩ ዙሪያ አንዳንድ ጉዳዮች ለውይይት የቀረቡ ሲሆን፣ ከእነዚህም መካከል የፓትርያርኩን ምስል የያዙ በየቤተክርስቲያኑ ቅጥር ጊቢዎች የሚገኙ ቢልቦርዶች፣ የፓትርያርኩ 18ኛው በዓለ ሲመታቸውን በማስመልከት ስለተሠራው ሐውልትና ጳጳሳትን እርስ በርስ ያናቁራሉ ስለተባሉ አንዳንድ ግለሰቦች ማብራሪያ እንዲሰጡ ፓትርያርኩ ተጠይቀዋል፡፡

ለትናንትና ምላሽ ይዘው እንዲቀርቡ በቅዱስ ሲኖዶስ ጥያቄ የቀረበላቸው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ፓትርያርክ አቡነ ጳውሎስ፣ በመጀመሪያ ምንም ስህተት እንዳልሠሩ የተከራከሩ ቢሆንም፣ በተለይ ሐውልቱን በተመለከተ ግን መመረቁን አላውቅም የሚል ምላሽ መስጠታቸውን ምንጮች አረጋግጠዋል፡፡

የሐውልቱንና የቢልቦርዶቹን መሠራት በተመለከተ ከቤተክርስቲያኗ ሕግ ውጪ መሆኑን ሕግን አጣቅሰው የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት የተከራከሩዋቸው ሲሆን፣ በመጨረሻም ስህተት መሆኑንና እንዲፈርስ ሲሉ የሲኖዶሱ አባላት በሙሉ ድምፅ መወሰናቸው ታውቋል፡፡

ቅዱስ ሲኖዶስ ይህንን ውሳኔ የሰጠው፣ ‹‹የተሰራው ሥራ ከአበው ትውፊትና ከቤተክርስቲያኗ ሕግ በተፃራሪ ነው›› በሚል መሆኑን ምንጮች አክለዋል፡፡

ከዚህ በተጨማሪ፣ ወ/ሮ እጅጋየሁ በየነ የተባሉት ግለሰብ አባቶችን እርስ በርስ በማጣላት የሚታወቁ ስለሆነ ወደ መንበረ ፓትርያርኩ ቅጥር ግቢ እንዳይገቡ ሲኖዶሱ የተስማማ ሲሆን፣ ውሳኔው በቤተክህነት አስተዳደር ሥራ አስኪያጅ ደረጃ እንዲሰጥ መደረጉን ምንጮቹ አረጋግጠዋል፡፡

በአጠቃላይ ሲኖዶሱ ቤተክርስቲያኗን በሚመለከት ባደረገው ውይይት፣ የፓትርያርኩ አመራር ቤተክርስቲያኗን እንደጎዳት፣ ሥርዓት አልበኝነት መስፈኑን፣ ሙስና መንሰራፋቱንና አምባገነንነት በገሐድ መታየቱ በዋነኛነት ተጠቅሷል፡፡

ከትናንት በስቲያ በዋለው የሲኖዶሱ ስብሰባ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ የነበሩት ሊቀ ማዕምራን ፋንታሁን ሙጬ እንዲነሱና በሀገረ ስብከቱ ላይ ያደረሱት ጥፋት ካለ በኦዲት ተጣርቶ በሕግ ተጠያቂ እንዲሆኑ ተወስኗል፡፡

Friday, October 22, 2010

ከደረቅም ደረቅ ፣ ከእርጥብም እርጥብና ከበሰበሰውም ብስብስ መሆን ይቻላልን? ክፍል ፫

የርሶ ብዕር አስተያየት ተሳትፎ ሕብረተሰባችንን ይጠቅማል ያሉትን አይንፈጉን ገንቢነቱ ቦታ ይኖረዋልና!

ማሳሰቢያ፡ ይህ ገጽ የተዘጋጀው የተለያዩ የኅብረተሰባችንን ሀሳብ ለመለዋወጫ እንጂ ለሚሰጡት ማንኛውም አስታየቶች በማንኛውም መንገድ ተጠያቂ አይደለም። ጉግል ድርጅትም ኃላፊነት አይወስድም። ኃላፊነቱ በሙሉ የአስታየት ሰጪው ብቻ ነው።


ከደረቅም ደረቅ ፣ ከእርጥብም እርጥብና ከበሰበሰውም ብስብስ መሆን ይቻላልን?

ክፍል ፫

የተወደዳችሁ የገጻችን ተከታታዮች እንደምን አላችሁልን? ጸጋው የማያልቅበት እግዚሀብሔር ለዚህ ሰአት ፈቃዱ ሆኖ ሁላችንንም ስላደረሰን ለታላቁና ገናና ስሙ አሁንም ክብርና ምስጋና ይሁን። አሜን።

እንደምታስታውሱት ያለፈውን ጥሁፋችንን የገታነው የአካባቢያችሁ የመረዳጃ ማህበር ውስጥ ሾልኮ አመራሩን ጨብጦ የነበረውን ተፈራወርቅ አሰፋ የሚባለው እስስት ግለስብ ካቆመው የውንብድና ቡድን ውስጥ አንዱ ሕገወጥ ሰውን የማስተላለፍ (ሁማን ትራፊክ) ንግድ ነው። በሰብአዊ መንገድ ቢሆን መልካም ነበር ነገር ግን ከጅምሩ እስከመደምደሚያው የገንዘብ ጥቅም ለማግኘት ሆን ተብሎ የተፈጠረ ቡድን ነው። ከኢትዮጵያና ከሌሎች ሀገሮች ያሉትን ወገኖቻችንን ከፍተኛ የሆነ ገንዘብ በማስከፈል በዚያ ሀገር ባሉ ደላሎቻቸው አማካኝነት፣ እንደዚሁም በዚሁ አሜሪካን በተለያየ ከተማ ውስጥ በሚገኙ ወኪሎቻቸው አማካይነት እየተቀበሉ ያስገቡአቸው ሰዎች ቁጠራቸው ብዙ ነው። በለስ ያልቀናቸውም ከሜክሲኮ ይዞ በደቡብ ሀገሮች በእስር ያሉ ወይንም በተለያየ ምክንያት ሕይወታቸውን ያጡት፣ ብለውም ቴክሳስ ላይ ተይዘው ከብዙ ስቃይና መከራ በኃላ ወደመጡበት ሀገር የተመለሱትን በዚህም የገንዘብ መቅለጥ ብቻ ሳይሆን በራሳቸው ሕይወት እንግልት የከፈሉት ሁሉ የእስስቱ ተፈራወርቅና የሱ ቡድን ሰለባዎች ናቸው።

በለስ ቀናቸው ከሚባሉት ደግሞ ውስጥ በዳላስ ቤተሰብ ወይም ዘመድ ያላቸውና ወይንም የዚሁ ሕገወጥ ቡድን አባሎች ጋር በተለያየ መልኩ ንክኪ ያላቸው ብቻ ናቸው። ሌሎችም እድል ሆኖ ሳይያዙ የገቡ ሲኖሩ ሊሎቹ ቴክሳስ ላይ የተያዙት ግን በቤተሰቦቻቸው ግፊት አድርገውባቸው በመረዳጃው ማህበር ስም ከኢምግሬሽን አስከባሪው ክፍል ጋር በመነጋገርና በመጻጻፍ ያስለቀቁዋቸው አሉ። አንዳንዶችንም ተጨማሪ ገንዘብ አስከፍለዋቸዋል። የዚህ ቡድን አባል ከሆኑት ውስጥ ከፍተኛውን ሚና የሚመራውና ሕይወቱን ሙሉ ወግ ያለው ስራ የማያውቀው፣ የረባም ትምህርት የሌለው ፣ ሲፈልግም የፍቺ ባለሙያ፣ ሲፈልግ የኢሚግሪሽን ወይም የታክስ ባለሙያ ነኝ እያለ በከተማችሁ የሚያውደለድል፤ በእርሱ  የታክስ ስራ አይ አር ኤስ የባንክ ሂሳባችሁን የተያዘባችሁ ፣ በጋብቻችሁ ውስጥ እክል መኖር ሰምቶ ረዳት መስሎ ገብቶ ወይንም አንዳችሁ ችግራችሁን አዋይታችሁት ከሆነ፣ ገንዘብ አገኛለሁ ብሎ ነገር አበላሽቶባችሁ ከለፋችሁት ንብረት አፈናቅሎ ፣ ከልጆቻችሁና ከትዳራችሁ አለያይቶ፤ የኢምግሪሽን ጉዳያችሁን አበላሽቶ ፣አማርኛውን እንኳን ጠንቅቆ መናገር የማያውቅ አስተረጉማለው እያለ ያለችሎታው በየፍርድ ቤቱና ኢምግሬሽን መስሪያ ቤቶች በመውሰድ  ፈቃድ ሳይኖረው እያጭበረበረ ከወገኖቻችን የሚገፍ ነውረኛውና የህብረተሰቡ ዝቃጭ የሆነው መንግስቱ ታደሰ (ቴድ መርካቶ) ሰለባ የሆኑትን የዳላስ ነዋሪ የሆነው  ቤቱ ይቁጠረው። ይህ ግለሰብ ዋነኛው በከተማችሁ የሕግ ወጥ ሰዎችን አስተላላፊ ንግድ ውስጥ የተዘፈቀ በሱም ምክንያት ሕይወታቸው የተበላሸ ብሎም ሕይወታቸውን ባጡት ደም የታጠበ ሰው ነው። እንግዲህ ይህ ለገንዘብ ሰው የበላ ፍጡር በቆየ ጓደኛው ዘውገ ቃኘው በሚሉት ዝንጀሮ አማካይነት ነበር ከነእስስቱ ተፈራወርቅ ከሚሉት ጋር ይሰሩ የነበሩት። ከጥቂት አመታት በፊት ባንድ ወቅት ከረጀ በተባለው የከተማችሁ ምግብ ቤት የነሱ ሰለባ በነበረ ግለስብ ስሙ  እምሩ የሚባል ተጠርቶ በነበረው ስብሰባ የተገኛችሁ ሕያው ምስክር አሁንም አላችሁ። በተለይም በሕጋዊ የሙያ ፈቃድ የትርጉም ስራ ላይ የምትገኙና ዳላስ ውስጥ ነዋሪ ሆናችሁ በአስተርጓሚነት በአንዳንድ የኢምግሪሽን ፍርድ ቤት ወይም እስር ቤቶች የተገኛችሁ፣ በተለይም በደቡብ ቴክሳስ ጠረፍ ወደአለው የዘለቃችሁ፤ እስረኛ ወገኖቻችን ከዳላስ መሆናችሁን ስትነግሯቸው የነዚህን ግለሰቦችን ስም እያነሱ እንድትነግሩላቸው የተጠየቋችሁ ሁሉ እውነታው ለናንተ ግልጽ ነውና ይሉኝታ ሊይዛችሁ አይገባም። ለወገኖቻችሁ ጉስቁልና እንደዚሁም ሕይወታቸውን ባጡት በነዚህ ግለሰቦች ሕገወጥ ንግድ ሰለባዎች ስትሉ ለሚመለከተው ያላችሁን መረጃ (ኢንፎርሜሽን) እንድታስተላልፉ አበክረን እናሳስባለን።

ሌላው የመረዳጃ ማህበር መጠቀሚ በሆነ (ሌተር ሄድ) ና ማህተም በእስስቱ ተፈራወርቅ ፊርማ ባረፈበት ከእውነት ውጭ የሆነ ጥቅማጥቅም ያገኙ ግለሰቦችና ቤተሰቦች በተለይም የእርሱ አጋሮችና ቡድኖች በአሀዝ ለመጥቀስ የበዛ ነው። በተለይም በህብረተሰቡ ውስጥ ምንም ግልጋሎት ላላበረክቱት እንዳደርጉ ተቆጥሮና እንደ ሞዴል ተጠቅሰው በተለያየ መንገድ እስከ ከፍተኛ ተቋም ትምህርት እድል ካገኙት ውስጥ እንደ በትሩ ገ/እግዚሀብሔር ቤተሰብ ለናሙና ስናስቀምጥ፣ ለራሱና ለአጋሮቹ እስከ ገንዘብ ጥቅም እንዲያገኙ ያደረጋቸው ብዙ ነው። አሁንም የሱ አጋር የተባሉት እንቅስቃሴ በመያደርጉ ሰባዊ ድርጅቶች ስም ብዙ ምዝበራ እያደረጉ ናቸው። ለምሳሌ ጥቂቶችን  ለመጥቀስ እንደ ዓይን ባንክ ፣ በትሩ ዩዝ፣ ቼምበር ኦፍ ኮሜርስ፣ ወዘተ….. ኸረ ስንቱ ተወግቶ ሌላው የሚገርመው በዳላስ ቅዱስ ሚካኤል ስም በትሩ ግ/እግዚሀብሔር የምንትስ ሊቀ መንበር ፣ ይልማ ፈለቀ የምንትስ ሊቀ መንበር እያሉ የድፍረታቸውና የንቀታቸው ብዛት ዓይን አፍጦ በታቦት ስም ቁማር ሆኖ ነው የሚገኝ። እንግዲህ ፈረስ ያደርሳል እንደሚባለው ገብታችሁ ማበራየት የናንተው የዳላሶች ጉዳይ ነው። ሌላም ብዙ ጉዳዮች አሉ በዳላሶች ላይ እየተቆመረ የሚገኝ። በተከታታይ የጣፍነው ትንሹን ክፍል እንጂ የእስስቱ ተፈራ ያልተነካካበት ከፖለቲካ፣ ከሲቪክ ብሎም አጽራረ ቤተ ክርስትያን ድርጅት የለም። አንዳንዴም እርግጥ እንደ ሌሎቹ ወገኖቻችን በመድህን ዋስትና ሽያጭ ብሎም በታወን ካር (ሊሞ) ብቻ ገቢ ነው የሚተዳደረው ከዚህም አልፎ ቁጥሩ የበዛ ድርጅት ውስጥም የጎላ ተሳትፎ የሚያደርገው እንዴት ሆኖ ነው? ብለንም ራሳችንንም እንደ የዋህ ለመጠየቅ ያዳዳናል። ነገር ግን ሀቁ ከሊሞ የማስመሰያና የመደበቂያ ስራ ፣ የመድህኑም ስንት ከመቶ ቢሆን የተቀረው ስንት በመቶ ይሆን? ብለን ለናንተ እንተወዋለን። እንግዲህ  በእስስቱ ላይ ባለ ብዙ ተከታታይ መጽሀፍ የሚያስጥፍ ጉደኛና ነውረኛ ስለሚወጣው ለዛሪ በዚህ እንቋጭለት።

እንግዲህ ሰው ወደ ትውልድ ሀገሩ የመውጣትና የመግባቱን መብት ወያኔ የሰጠ ቢሆንም (ለሁሉም አይደለም)። እስስቱም ቢሆን የተለያየ የተቃዋሚ ቡድኖች አባል እንዲሁም አመራር ውስጥ የሆነ ብሎም የዳላስ መረዳጃ ማህበርም አንደኛው ተቁዋሚ ድርጅትን የመራ ፣ የደረሰን መርጃ እንድሚለው በቅርቡ በውን ወደ ኢትዮጵያ ይገባልን? እንደ ሀገሩ ዋ..ው..! ብለን ለናንተው ውድ አንባቢዎቻችን እንተወዋለን።

እንግዲህ እንደምትሰጡን አስተያየታችሁ ስለተቀሩት ግለሰቦች በቁ.፬ እንገናኝ ወይስ እንደነዚህ ግለሰቦች ባሕርይ  ከደረቅም ደረቅ ፣ ከእርጥብም እርጥብና ከበሰበሰውም ብስብስ መሆን ይቻላልን?  ይህ ነው የጥሩ ዜግነት መስፈሪያ? ይህንን አይነት ጉድስ እንዴት የዳላስና አካባቢ ነዋሪ የኢትዮጵያ ተወላጅ መለያ ምግባሩ ይሆናል? የተማርን ነን የምትሉና እናመዛዝናለን የምትሉ ለመሆኑ አላችሁን? ከኢትዮጵያ ነን የምትሉ ሁሉ ከደረቀውምም አብራችሁ ልትደረቁ ነውን ፣ ከእርጥብም አብራችሁ ልትረጥቡ ፈገለጋችሁን? ወይስ ከበሰበሰውም አብራችሁ መበስብስ መረጣችሁ?  መልሳችሁን አትንፈጉን?


እርሶስ ምን ይላሉ?

Wednesday, October 20, 2010

ከደረቁም ደረቅ፣ ከእርጥቡም እርጥብና ከበሰበሰውም ብስብስ መሆን ይቻላልን?

የርሶ ብዕር አስተያየት ተሳትፎ ሕብረተሰባችንን ይጠቅማል ያሉትን አይንፈጉን ገንቢነቱ ቦታ ይኖረዋልና!

ማሳሰቢያ፡ ይህ ገጽ የተዘጋጀው የተለያዩ የኅብረተሰባችንን ሀሳብ ለመለዋወጫ እንጂ ለሚሰጡት ማንኛውም አስታየቶች በማንኛውም መንገድ ተጠያቂ አይደለም። ጉግል ድርጅትም ኃላፊነት አይወስድም። ኃላፊነቱ በሙሉ የአስታየት ሰጪው ብቻ ነው።


የተወደዳችሁ የገጻችን ተከታታዮች እንደምን አላችሁ? ክብሩና ምስጋናው የበዛው አምላክ አሁንም ለእርሱ ይሁን።

ባለፈው ከጀመርነው  ከመቀጠላችን በፊት በትላንትው ዕለት ተኮላ መኮንን (ተኩላው)  መረዋ በተባለው  ገጹ የለጠፈውን ተመልክተነዋል።  ለመጀመሪያ ጊዜ በሰባራ ምሑር ብዕራቸው ብሎ በመጥቀሱ ከሱ የተሻለና አቻ ሊሆነው የማይችለውንና በሀቅ የጨበጥነውን የዕውቀት መጠናችንን እውቅናን በመቀበሉ በልዩነታችንም እንዲሁ ይከፈትልህ ነው የምንል። በእርግጥ እኛ ጥሩ አማርኛ ጠሀፊዎች አይደለንም ፣ ይህንኑ ከመጀመሪያው  የገለጽነው ሲሆን ከዕለት ወደ ዕለት ለመማርና ለማሻሻል ከመጣር ወደ ኃላ አንልም። እዚህ ውስጥ የገባነውም በናንተ አጽራረ ቤተ ክርስትያንንና የጨበጣችሁትን የወያኔ ፭፪ ገጽ አስፈጻሚ  ሎሌነት ሚና፣ የዚሁም እንቅስቃሴ ውጤታችሁ ክፍል የሆነው  የሜይ፪ቱ ተግባራችሁ በማንነታችን፣ በባሕላችን፣ በሀገራችንና በሀይማኖታችን በአለም መድረክ አሉታን ያመጣብንና አንገታችንን ያስደፋን በመሆኑ ነው። ዛሬም ይህንኑ ተግባር እራስህንም  ስትነጥልና ስታወግዝ አናይህም በተቃራኒው ስትስተገብር እንጂ።  

አንድ ነገር መረዳት ያለብህ ስድብ ማለት ምን ማለት እንደሆነ የእንግሊዙንም ሆነ የአማርኛውን መዝገበ ቃላት ለማንበብ ሞክር የሚገባህ ከሆነ። አንተን በሙሉ አፋችን ውሸታምና ሌባ ነህ ብለን ብንጥፍ ያ ሀቅ ነው። ምክንያቱም ደጋግመህ ያንተ ያልሆነው  ሰርቀህና ዋሽተህ መገኘትን በሚገባ ቀደም ባለው ጥሁፋችን አስቀምጠነዋል። ባፍ ይጠፉ እንዲሉ ባዲሱም ጥሁፍህ ደግመህ ዋሸህ። “ዋሽተን አናውቅም ስንል ለአፋችን ሳንሆን ከልባችን ነው። ዋሽተን ያገኛችሁን እለት የመሞታችን የመጨረሻውም የመጀመርይውም ወቅት ሆነ ማለት ነው።“ ብለህ ትላንት አስነበብክ ከዚያ በፊት የናንተ ልሳን የሆነው መለከት የተባለው ሲመጣ ገጽህን እንደምትዘጋ የጣፍከውን ዘንግተህ ነው ወይስ የያዘህ ሰይጣን አስቶህ እንደ ውሻ መልሶ የሚያልከሰክስህ። ሴቷ ሱሪህን ካስፈታችሁ ቆይቷል አሁን ደግሞ በግልጽ መጦመር ጀምራለች እንጂ እንዳንተ ሀገር እያወቀው ማንነትህን ስሟን ደብቃ አልወጣችም፣ ቀዳዳና ዋሾነትን አቁመህ ፣ ከሰይጣን ጎዳና ወጥተህ ፣ ቃልህን ጠብቀህ ፣ የወያኔ መልዕክተኛነትህን ከቤተ ክርስትያን አውጥተህ ብትቀመጥ እኛም ልንተውህ በተገደድን። የዳላስ ህብረተስብም ባንተ ላይ መጠቋቀም አቁሞ ፣ ቤተሰቦችህም ባንተ አስነዋሪ ምግባር ከመሸማቀቅና አንገት ከመድፋት ቢተነፍሱ መልካም ነበር።    

ያለፈው ጥሁፋችን ያነገተው በሙሉጌታ (ሞላው) ወራሽ (ቀዳዳው) በተባለው  አጽራረ ቤተ ክርስትያን ግለሰብ ሲሆን ወደ ተቀሩት ከመዝለቃችን በፊት ትንሽ የምንጨምረው ይኖረናል።

ቀደም ብሎ ጀምሮ ከሚደርሱን አስታየቶች ውስጥ የዚህ ቀዳዳ ሚሽት ስለ ባሏ ጸረ ቤተ ክርስትያን ተግባር አታውቅም እንጂ ብታውቅ ኖሮ ትገታው ነበር የሚል ሲሆን፣ እኛ ግን በአስተያየቱ አንስማማም። ምክንያቱም ገጻችን በአለም ዙሪያ የደረሰ ከመሆኑም በላይ ዳላስን የሚያውቁ በኢትዮጵያ ውስጥ የሚኖሩ ሁሉ በሚገባ የሚከታተሉት በመሆኑ በርሷና በትዳሯ ላይ እየተፈጸመባት ያለውን ጥቃት የሚያስገነዝባት አንድ እንኳን ዘመድ ወይ ወዳጅ የላትም? እርሷም ጥበብ በሰፈነበት የአለም ክፍል እየኖረች ይህን ካዳገታት ምኗን ነው ያገባት? ከጭቃ አድቦልብሎ ባሏ የፈጠራት የሱ ፍጡር ሆና እንደሱ የተለየች እስካሎነች በቀር፣ በጋብቻ ላይ ሲማግጥ፣ ከሕብረተሰቡ የተለየ ድርጊት ሲፈጽም በዚህም ሲለይ፣ ልጆቿ እንደ ሌሎች ህጻናት በቤተ ክርስትያን ውስጥ ተሳትፎ የማያደርጉ፣ ወዘተ…. ምነ አይነት ኦርቶዶክሳዊ ወላጅ ናት ሀይማኖቷን በዚህ የልጆቿ ዕድሜ የማታስተዋውቅ? የእውቀትና የትምህርት ድሀ ናት እንኳን ብንል ባሏም የእርሷ ቢጤ ነገር ግን ስለ ልጆቿ በቀለም ትምህርት ለመጎልበት የሚያስፈልጋቸውን ክትትልና እርዳታን እንዴት ልትሰጣቸው ትችላለች? የልጆቻቸውስ የወደፊት እድልና ፋንታ ምን ይሆን?  እንደኛ አስተሳሰብ ከሆነ ሁለቱም በትምህርትና በዕውቀት ያልገበዩት ነገር ግን በገንዘብ ሊገዙት የሚፈልጉት ዝና ክብርና ሥልጣንን ለመያዝ ማንኛውንም መስዋዕት ማድረግን ነው። በትምህርት ዜሮ መሆንና በአቋራጭ ድንቁርናን ለመሸፈን ያልዋሉበትን፣ያልወጡበትንና ያልወረዱበትን፣ ያልሰሩበትን ጨርሶም ያላነበቡትንና ምርምር ባላደረጉበት በሰሙት ጫፍ ብቻ አዋቂ ባለሙያ (ኤክስፐርት) ለመሆን የሚሞክሩ፣ አለማወቅንና አለመማርን እንደ እፍረትና ሞት በመቁጠር ለመጋረድ በሚያደርጉት ሀሰት ተግባር ከሚተበተቡ ህሊናቸውን ሰብስበው የሚገባውን እርምት በማድረግ ፊደል ቢቆጥሩ ለልጆቻቸውም ጥሩ ምሳሌነትን ባተረፉ።

ነገር ግን ሁሉንም በገንዘብ እወጣዋለው የሚል ህሊና ፈጣሪ አምላኩን  ይረሳውና ገንዘብ ብቻ ማምለክን ይያየዘዋል። በእውነትም ለሁለት አምልኮ መገዛት ስለማይቻል የቀዳዳውም ሚስት አስተያየት ሰጪዎች እንደሚሉት ሳይሆን የዛሬ ኑሮዋን የምታመልክና አልጋዋ ላይ እንኳን ብትይዘው ደንታም የማይሰጣት ግብዝ ፍጡር ሆና ነው የምትመሰል። የቧላም ሥነምግባር ምንም የማይሰማትና ህሊናዋ የደነዘዘች በመሆኗም ጭምር ነው ለእርሱ እኩይ ተግባር አካልነቷን እያስመሰከረች የምትገኝ። መጽሀፉም አንድ አካል አንድ አምሳል የሚለው ሀረግ ለነዚህ እርኩሶች ምሳሌ ባናደርገውም ባህሪያቸውን ያስገነዝባል እንላለን። እርሱን የተጠጋ ሁሉ ከችግር እንደማይወጣ ቅንና ትሁት የሆነው አስማማው የተባለው ወንድሙም የከይሲ ወንድሙን ምክር ተቀብሎ ይመሰል በፓርክሌንና ግሪንቪል መጋጠሚያ ላይ ያለውን የነዳጅ መሸጫ በሽያጭ ግብር ምክንያት ነው አሉ ካለፈው ቀዳሚት ጀምሮ ተዘግቶበታል።እንግዲህ የሙላው ቀዳዳውን ለዛሬ በዚሁ እምንቃጨው።

ሌላው የዚሁ ተመሳሳይ በሆነው መንገድ የለቀቀው ፣ በወቅቱ በከተማችሁ የታወቀውና በበጎ ስራው ይከበር የነበረው፣ የአቶና የጋሼ ስም ተሰጥቶት የነበረው፤ ምንም እንኳን ቀደም ሲል ከርሱ ጋር የንግድ ሽርክና ገብተው ሲፈርስባቸው እንዲህ አድርጎን ተለያየን እንጂ ወይንም ስራው ሲሻሽል ተመጣጣኝ ካሳ ተቀብዪ ነው የማይሉትን፣ ከእውነት የራቀና አሉባልታ የሚያናፍሱበትን ትተን በእውነትም ግለሰቡ በወቅቱ ጥሩ ኢትዮጵያዊም ነበር፣  የቸገረውን በተቻለው ረድቷል፣ ቤተ ክርስትያንም ስታቋቁሙ የተቻለውን አስተዋጾ አድርጓል ይህ ሀቅ ነው። ከኛ የሚለየው ለቤተ ክርስትያን ያደረገውን የንዋይ ስጦታን በመጠቀም ደብሩ ላይ ተጽእኖ ለማድረግ ሞክሮ ሳይሳካለት ሲቀር ወደ እርኩስ መንፈስና ተግባር መግባቱ ይህንንም ተከትሎ የመጣው ውጤት ያጠቃላይ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ተከታዮችንና ባጠቃላይ የኢትዮጵያ ተወላጆችና ወዳጆችን ያሳዘነና አንገት ያስደፋው የሜይ 2ቱ ብጥብጥ ውስጥ በቀጥታና በተዘዋዋሪ ተሳትፎ ማድረጉ ነው። ይህ ግለሰብ ስሙ ኃይሉ እጅጉ ወይም ከቀን በኃላ በእርጅናውና በከተማችሁ አንቱ ተብሎና ተከብሮ በመቀመጫው ዘመን ቀዩ ሰይጣን የሚል ቅጥያ ስም ያገኘው።

ቀዩ ሰይጣን (ኃይሉ እጅጉ) በግል የንግድ ስራ ላይ ከኢትዮጵያ ጀምሮ ለብዙ አመታት የኖረና በዳላስም በቂ ንብረት ያደራጀ ጠንካራ ሰው ቢሆንም ከሕዝቡም ተስማምቶ የሚኖር ነበር። በቅርብ ጊዜ ወደ ትውልድ ሀገሩ በመመላለስ አንዳንድ የሚጠቀምባቸውን የስራ መስኮችን በመቃኘት ለመተግበር በሚያደርገው እንቅስቃሴ፣ ቀደም ሲልም አባ ጳውሎስ ይተዋወቅ ስለነበር ከርሳቸውም በጥግጊ አውቆትም ሆነ ሳያውቀው አዲስ ምህታት (ቫይረስ) ይዞ በመምጣት፤ ይህንኑ ለሚሰሙት ሁሉ ለመቀባት ሙከራው አልሳካለት በማለቱ ነበር። የእርሱ አዲሱ በሽታው የሚካኤል ደብር አባ ጳውሎስን እንዲቀበልና እንዲያድር የማድረግ ዘመቻ ነበር። እንደ አግባቡ ከሆነ ህሊና ያለው ማንም ሰው በተለይም እርሱ ከደብሩ ምስረታ ጊዜ ጀምሮ የደብሩ መሰረታዊ አቋም ምን እንደነበር በሚገባ የተረዳ ሆኖ ሳለ አድፍጦና ቀን ጠብቆ ፤ የደብሩ አባላት በማይፈቅዱትና በማይቀበሉት መንገድ ተጽዕኖ ማድረግ እንዲሁም ያለውን ስርዐት ማፍረስ ውስጥ ካለመግባት ተቆጥቦ ወይንም ከደብሩ አባልነት እራሱን ማግለልና ጣልቃ አለመግባት የሚገባው ተግባር ነበር። ነገር ግን እራሱን ከሌሎች አጽራረ ቤተ ክርስትያን ጋር አሰልፎ ደብሩን ለማፍረስ በግምባር ቀደምትነት ከሚንቀዠቀዡት አንዱ ሆኖ ተሰልፋል። በዚህ ሥነ ምግባሩ ደብራችሁን የአባ ጳውሎስ ገጸ በርከት ሊያደርግና ለውለታውም በኢትዮጵያ ውስጥ መሳካት ያቃተውን የንግድ ስራ ትብብር እንዲገጥመው ብሎም ወያኔ ያዘጋጀውንም ባለ ፭፪ ገጽ አጀንዳን ለማመቻቸት እየተሳተፈ እንደሚገኝ መረጃዎች ምስክር ናቸው። የግል የንዋይ ጥቅሙ እንዲሳካለት በመታወር ብቻ የሚያደርገው ምግባር ዕምነቱንና ሀይማኖቱ እንደሌለው፣ ብር ሆዳምነቱን ያስቀደመ አድርጎታል። ፈጣሪ አምላኩንም በዚህ ዕድሜው ክዶ ገንዘብ አምልኮቱን አስቀድሞ የገዛ ራሱ ያቆመውን ደብር ለሚከሱ ከአጋርነት አልፎም እንደ ጀብዱ እኔ ነኝ ደብሩን ለከሰሱት የጠበቃውን የምከፍል ብሎ የሚናገር ቀይ ሰይጣን ነው።

በእድሜውም ሆነ በብስለት ደረጃ ከርሱ የማይቀርቡት ጋር ዛሬ ደብራችሁን እየወጉ ካሉ እንደ ቀዳዳው ሙላው ጋር ጓደኝነት የገጠመውና የቀድሞ ወዳጆቹን አንገት ያስደፋ። የማታ ማታ እየቀረበ እድሜው የመሸበት መሆኑንም የዘነጋ መስሎ የሚታየው፣ በጌታ የመጠሪያው ቀን ላይ ያለ መሆኑ እንዴት ይዘነጋዋል? ሲሆን እርሱ ዛሬ በጥባጭ ሳይሆን ሽማግሌ በመሆን የተጣላና የተቀያየመ ቢኖር የማስታረቅና የማስማማት የጨዋ ስራና ምግባር  በማድረግ የፈጣሪን መምጫ መጠበቅ መሆን ነበር። ይህ በመረጃ ተደግፎ የሚገኝ የሱ አጽራረ ቤተ ክርስትያን ተሳትፎና የገንዘብ አስተዋጾ የዚህም ውጤት ሆኖ ደብሩ ያወጣውን የመከላከያ ወጪ ማስመለስ የግድ ነውና እንግዲህ እርሱንና ብጤዎቹ እንደ ሰፈሩ መሰፈር እንዲሉ ፣ የምታመልኩትና ኃይል የሰጣችሁ ገንዘብ ከናንተ ወዳችሁም ሆነ  ተገዳችሁ የምትተፏት መሆኑን ነው ከወዲሁ ማስገንዘብ የምንወደው።

ከዚ አልፈን ደግሞ ሰሞኑን ወደ ኢትዮጵያ ለመሄድ በዝግጅት ላይ የሚገኘውን የቀድሞ የኢትዮጵያ ሰራዊት የሻለቃ ማዕረግ አለው የሚባለውና ስረ መሰረቱም የሻገተ ጮሌ አርጎ ራሱን የሚቆጥረው አቶ ተፈራወርቅ አስፋው ነው። መደጋገም ወይም ኩረጃ ባይሆንብን፤ ስለዚሁ ግለሰብ በዚህ ሳምንት ውስጥ ሰንበቴ http://www.senbete.blogspot.com/ ላይ ብዙ ዘግቦበታልና ወደዚሁ ገጽ እንድትገቡ እየጋበዝን የራሳችንን ባጭሩ እንደሚቀጥለው እናቀርባለን። ይህ ግለሰብ ወደዚህ ዳላስ የመጣውና ለብዙ ጊዜ የኖረው በመንግሥት ድጎማ በሚደገፍ የቤት ኪራይ ውስጥ ነው። ከመምጣቱም በፈት የደርግ ወታደሮች ሳይቀሩ በተለይም መኮንኖችን ያለው የወያኔ መንግሥት አስሮ እንደነበር ገሀድ ነው። የተፈራ ግን ምንም ማስረጃ ልንጨብጥ አልቻልንም ይሁን እንጂ ተለጣፊ ሆኖ የሰራቸውን በማስረጃ እስናገኝ ድረስ ከዛ ብንታቀብም ባለሟል እንደነበር ትክክል ነው።

ዳላስ በገባበት ወቅትም መጀመሪያ የተጎዳኘው ከጸረ ወያኔ ጎራ ሲሆን እራሱን ተቃዋሚ አድርጎ  በተለያየ የድርጅት አባልና መሪ ብሎም ተቃራኒ ጎራ ማቋቋምን ነበር። የዳላስ ፎርትዋርዝ የኢትዮጵያን መረዳጃ ማህበር ከመቃብር በላይ ያለ ብቻ በመሆኑና ተቆርቋሪ  ያጣ ድርጅት በጠራው ጠቅላላ ስብሰባ የተገኘ በመጥፋቱ አጅሬው ዘው ብሎ ገብቶ ያለ ምርጫ መሪነቱን ያዘ። እዚህ ላይ የሱ ምንም ጥፋት የለውም። የአካባቢው ነዋሪ የሆነው አጠቃላይ ሕብረተሰብ ድክመት ነውና ከዚህ መማርና መሳተፍ ማድረግ ከጸጸት ያድናል። ይህ በመረዳጃ ማህበር መሪነት ዕድል ራሱን እንደፈቀደው በህረተስቡ ስም የተለያዩ ተግባራትን ያለ ታዛቢ እንኳን ሲቆምርበት ኖረ። የተለያዩ የከተማችሁን የፖለቲካ ድርጅቶችን እያኮላሸ አጠፋቸው። እርዳታን ከድርጅቱ የሚጠይቁትንም ግለስቦች እንዳይረዱ ነገር ግን የርሱ ደጋፊዎች ለሆኑ ብቻ ሲይመቻች ኖረ። ዳላስ በሚኖሩ የኢትዮጵያ ተወላጆች ላይ መረጃ እየሰበሰበ ለኢትዮጵያ መንግስት አቅራቢ ሆነ። ኒያላ ኢንሹራንስ ለተባለው በዚህ ሀገር ፈቃድ ለሌለውና ባለቤትነቱ የመሀሙድ አላሙዲን የተባለው ቱጃርና የጠቅላይ ሚኒስትር መለሰ ባለቤት አዜብ መስፍን ሲሆን ከሶስቱም የአሜሪካን ሀገር ወኪሎቻቸው የቀረው የናንተው ተፈራወርቅ ብቻ ነው። በመረዳጃው ማህበር በኩል የሚተዋወቃቸውን ሁሉ ኢትዮጵያ ላላቸው ንብረትና ዘመድ ጨምሮ የንብረትና የህይወት መድህን ሲሸጥ፤ በተመሳሳይ የመረጃ ስራውንም አብሮ ያካሂዳል።

ምንም እንኳን ባለፉት ጊዜያት ስለዚሁ መረዳጃ ማህበር ብዙ ስንጥፍና እርሱም ከአመራር ቢለይም፤ የወያኔን ሥራ ለመስራትና ቀጣይነት በሚኖረው መንገድ የሚገባውን መሰረት የጣለና ለወያኔ የ፭፪ ገጽ አራማጆችን ስግስጎ ከውጭ የሚመራቸው መሆኑን በማስረጃ የተደገፈ ነው። በመረዳጃው ማህበር ስር የተቋቋመው እድርም ቢሆን የእርሱና የጥቅም አጋሮቹ የሆኑት የነበትሩ እስትራቴጂ ነው። ድርጅት ማፍረስና ማቋቋም የተካኑ ቡድኖች የታጀበው ተፈራወርቅ ይህንን እድር በከፍትኛ ገንዝብ እያስከፈለ ቦታ ካስያዘና በቂ ቁጥር ላይ ሲደርስ ወደ ቀብር መድህንነት በማሸጋገር ከፍተኛ የመጦሪያ ገቢ ለማግኘት ነው። እንደሚባለው በአባል የ፵ ዶላር ከእድር አባላት የተሰበሰበው ገንዘብ ወደተባለው አላማ አለመግባቱንና እንዲያውም ለአባላቱ የጃንጥላ መድህን ገዝቷልና ሰው በሞተ ቁጥር ገንዘብ ይበላበታል የሚባል ሲሆን መረጃውን እንዳገኘን እንደ አግባቡ እናካፍላችኃለን።

ከዚሁ ሳንወጣ ደግሞ በመረዳጃ ማህበሩ ማህተም ምን አይነት ወንጀልና ሰዎችን የማስተላለፍ ሕገ ወጥ ተግባር በእርሱ መሪነት እንደሚደረግ  በሚቀጥለው ጥሁፋችን እናካፍላችኃለን፣ እስከዚያው በሰላም ቆዩን።
  

Monday, October 18, 2010

ከደረቁም ደረቅ፣ ከእርጥቡም እርጥብና ከበሰበሰውም ብስብስ መሆን ይቻላልን?

የርሶ ብዕር አስተያየት ተሳትፎ ሕብረተሰባችንን ይጠቅማል ያሉትን አይንፈጉን ገንቢነቱ ቦታ ይኖረዋልና!

ማሳሰቢያ፡ ይህ ገጽ የተዘጋጀው የተለያዩ የኅብረተሰባችንን ሀሳብ ለመለዋወጫ እንጂ ለሚሰጡት ማንኛውም አስታየቶች በማንኛውም መንገድ ተጠያቂ አይደለም። ጉግል ድርጅትም ኃላፊነት አይወስድም። ኃላፊነቱ በሙሉ የአስታየት ሰጪው ብቻ ነው።


ከደረቁም ደረቅ፣ ከእርጥቡም እርጥብና ከበሰበሰውም ብስብስ መሆን ይቻላልን?

ለዚህ ጥሁፍ ከላይ መንደርደሪያ ያደረግነው  የተለያዩ ሒደቶችን በመዳሰስና በዚሁ ዙሪያ የጨበጥነውን ይዘን በመነሳት ለመቋጨትና ጭብጥ ለማስያዝ ይሆን ዘንድ ለማስገንዘብ ነው። የተወደዳችሁ የዚህ ገጽ ተከታታዮች ሰላምታችን በያላችሁበት ይድረሳችሁ። ለዚህ ሰአትም ፈቃዱ ሆኖ ላደረሰን አምላክ ክብርና ምስጋና ለእርሱ ይሁን። አሜን።

ውድ አንባቢያን ሆይ በጃችን የገባውን የሚቀጥለውን አዲስ ጦማር በመከፈቱ ደስታችን ከፍ ያለ ነው  ሌሎችም እንዲሁ እንዲሳተፉ ለብዙ ጊዜ ስንማጸን ነበር፣እኛ ስለዳላስ ብዙ ስላልኖርንበትና ከብዙ ወገኖቻችንም ሳንቀላቅል በስራ ምክንያት ርቀን ብንሄድም የናንተን መልካምና ሰላምን ዘውትር የምንጸልይ እንዲሁም የምንናፍቃችሁ ነን። ይህን አዲስ ገጽ የጀመሩትን ግለሰብ ገና ከመድረሳቸው  እንደ ድፍረት ባይቆጠርብንም አንዳንድ ስሞች በማር ወይም በወርቅ የቀቧቸው ላይ ልዩነታችን የሰፋ ነውና እርሳቸው ያላቸውም መረጃ ሳናቃልል እኛ ዘንድ የያዝናቸውን መርጃዋችን እንደ ወቅቱ አስገዳጅነት የምንለቀው ሲሆን፣ ያገትነው  በክፋት ሳይሆን ያለውን የጥሩና የመሻሻል አዝማሚዎችን እንዳያደናቅፍ ሲሆን፤ ሰላምና ፍቅር ሲሰፍን ግን ከማንም ሳናካፍል ከኛ ጋር ወደ መቃብር እንዲወርድ ብቻ ነው። ለገጹም አዘጋጅ ሙሉ ጤናና ኃይል እንዲሰጣቸው እየተመኘን ግለስቦችን አስቀድመው ከማወደስ ወደ ተበላሸውና እየተለወጠ ወደ ሚገኘው  የወቅቱ ጉዳይ ላይ በማተኮር ለወደፊቱ ተተኪ ትውልድ እንቅፋቶችን ማጽዳቱ ላይ ማተኮሩን፣  በሀቅና በመረጃ የተደገፉ መሆናቸው ላይ ጥንቃቄን መውሰዱን ስናሳስብ ለብልህ አይመክሩምና ማንነቶን ባይጦምሩት ደስ ባለን። በኛ ገጽም ስሞን እንዳልቀቡ እንግዲህ አደባባይ ኖትና እርም አውጪዎችም ሀዘን ቤት ይግቡ። ለማንኛውም  አድራሻው የሚከተለው ነው፡-
http://www.dfwethiopiancommunity.blogspot.com/

እናንተ በምትኖሩበት በዳላስ ቴክሳስ በጋርላንድ ከተማ ውስጥ የሚገኘውና በኢትዮጵያን ተወላጆችና ወዳጆች ትብብር ተመስርቶ የተቋቋመው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ደብረ ምህረት ቅዱስ ሚካኤል ካቴድራል ደብር ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ያጋጠመው ኦርቶዶክሳዊ ፈተና ቸል የማይባል ቢሆኑም በእውነተኛ የኦርቶዶክስ ልጆች በጾም፣ በፀሎት፣ በምህላና አስፈላጊው በሆነው መንግድ ጭምር የመጣውን ፈተና እየተቋቋሙና እየተወጡት ይገኛል። በአለም ዙሪያ የሚገኙት የኦርቶዶክስ ልጆችም በጾምና በፀሎት ጭምር አብረዋቸው እየተሳተፉ እንደሚገኙ ከሚደርሱን አስተያየቶችና ለደብሩም ከሚያደርጉት ድጋፍ ለመረዳት በቅተናል።ለነዚህ ወንድሞችና እሀቶች በያሉበት ቅዱስ ሚካኤል ይማለዳቸው፣ ድካማቸውንም ይቀበላቸው እንላለን።

ወደ ጥቅሳችን ስንገባ፤ ወቅቱ ባላፈው አመት ማገባደጃ ላይ በዳላስ ከተማ ኮይት መንግድና ፮፻፫፭ አውራ ጎዳና ላይ በሚገኝ አንድ ሆቴል ውስጥ በደብሩ ላይ ያነጣጠረ በጥቂት ግለሰቦች ተቀነባብሮ በዕለተ ቀዳሚት ከሰአት በኃላ የተጠራ ስብሰባ ነበር። ግንባር ቀደም አቀናባሪዎች የነበሩት ስማቸውን መጥቀስ ካስፈለገ፡- ኃይሉ እጅጉ(ቀዩ ሰይጣን) እንደዚሁም ሙሉጌታ ወራሽ (ቀዳዳው) የሚል ተቀጥያ ስም በምግባራቸው ያተረፉት ሲሆኑ፤ አጃቢዎቻቸውም የነሱ ቢጤ አጽራረ ቤተ ክርስትያን ይገኙበታል። ከፍተኛ ዘመቻ አድርገው የጠሩት ስብሰባ እነርሱንም ጨምሮ በአሀዝ ከ፪፭ የማይበልጥ ግለሰቦች ነበሩ።

በዚህ ስብሰባ ማንኛውም አይነት የድምጽም ሆነ የምስል መቅረጫ ተሰብሳቢው የተከለከ ሲሆን ከአዘጋጆቹ አንዱ የሆነው መስፍን ወልደየስ የተባለው  ማህበረ ቅዱሳን እየተባለ ለሚጠራው ቡድን አባል፣ክፍሉ ታደሰ ለተባለው የወያኔ ወኪልያደረና የሱን መጽሄት “ዜጋ“ ለተባለው  እንደዚሁም የእርሱ ወንድም የሆነ ብርሀነማርቆስ ታደስ ሎሌ፣ ከሚካኤል ደብር የበጎ አድራጎት ገንዘብ ምዝበራ ቡድን አባልና እስካሁን ማወራረድ አቅቶት በሕግም እንዳይጠየቅ ደብሩን ለማበጣበጥና ለማፍረስ የሚንቀዠቀዥ ግለሰብ ብቻ የሚካሄድው ስብሰባ በምስልና በድምጽ ሲቀረጽ ማምሸቱ የታወቀ ቢሆንም፤ ሌላ ምስልና ድምጽ ቅርጽ የያዘ በሌላ ሰው በስውር የተቀረጸ ነው አሊያም ከመስፍን ላይ የተቀዳ ዳላስ በነበርንበት ወቅት ከወዳጃችን እጅ ላይ ለመመልከት በቅተናል።

የእለቱን ስብሰባ በፀሎት እንዲከፍት ይጠበቅ የነበረው ቀደም ሲል በቅስና በሚካኤል ደብር ሲያገለግል የነበረውና ከምዕመናት ከፍተኛ ተቃውሞ እየበዛበት መጥቶ የነበረው ታደሰ የተባለው ግለሰብ ነበር። ይህ ሰው እንዲለቅ ጫና የመጣበት በጥላቻ ሳይሆን በግል ሕይወቱ መዛባት ስንል፤በመጀመሪያ ባለቤቱ በትዳሯ ባደረገችው ግድፈት፣ ተከትሎም ዕምነቷን ጥላ ወደ ጴንጤ (ፕሮቴስታንት) መሄዷን በማወቃቸው ብሎም ተለያይቶ ቆይቶ አብረው መኖር በመጀመራቸው፤ የወሰደውን ክህነት አጥፍቶታልና ካሕናችን ሊሆን የተገባ አይደለም የሚል እንቅስቃሴና እሮሮ እያደር በመብዛቱ ፤ እርሱም ወኔ ተስኖት ሁሉን እርግፍ አድርጎ መመንኮስን ስላልቻለ፣ በፈቃዱ የለቀቀና በዚያም ቂም ይዞ ደብሩን ከሚወጉ ጋር እየወገነ የነሱን ስብስብ እየተገኘ ፀላይና ባራኪ የሆነ ፤ እንደምንሰማው የርሱ ቢጤዎችና የሱ ጎሳ ቋንቋ ተናጋሪዎች እንደዚሁም ለአባ ጳውሎስ ባደሩ አጫፋሪነት የግሉ የሆነ ቤተ ክርስትያን መክፈቱን ቢሆንም፤ በሰአቱ ደርሶ ግን የእለቱን ስብሰባ ለመክፈት ባይበቃም መደምደሚያውን በፀሎት ሲዘጋ የነዚህን አጽራረ ቤተ ክርስትያን መሰሪ ሥራ እንዲገፉበትና እንዲጠነክሩ ማበረታቻ ሰጥቷል።

በታደሰ አለመገኘት ምክንያት ስብሰባቸውን በወቅቱ የከፈተው ቅደም ሲል የዲያቆንና የቄስ እጥረት በነበረበት ወቅት ቅዳሴ ፀሎቱን በመቻላቸው ብቻ ነገር ግን መቅደስ ውስጥ ገብተው ለመሳተፍ የስርዐቱ ብቃት የጎደላቸውንና ያፈረሱ በነበሩበት የደቆነውን አረአያ የተባለውና በአሁኑ ሰአት የነዚሁ አጽራረ ቤተ ክርስትያን በደነቀሩት ኮሚቴ ውስጥ የሀይማኖት አማካሪ የሆነው ግለሰብ ነበር። ከነካካን አይቀር በወቅቱስ የመጀመሪያዋ ከሳሽ ባል የሆነው ኪዳኔ ምስክርስ እንደ ካህን መስቀል ይዞ አሳልሟል አይደል? ከዚሁ ስብሰባ ተካፋዮች ውስጥ አብዛኛው ከአስተያየት የታቀበ ሲሆን በተለይም  በሁለት ግለሰቦች ክርስትያናዊ ያልሆነ ንግግር እጅጉን የተደናገጠ ይመስል ነበር።
፩ኛው ግለሰብ እንደ ጀብዱ የተናገረው ውስጥ “ እኔ ለሚካኤል ቤተ ክርስትያን ሰዎች ወርሐዊ ክፍያቸውን እንዳያደርጉ፣ በማንኛውም ነገር የሚሰጡትን እንዲያቆሙ ከፍተኛ ዘመቻ እያደረኩኝ ነኝ“ ብሎ የተደመጠው ተኮላ (ተኩላው) መኮንን ነው።
፪ኛው ግለሰብ ደግሞ “እኔ ሚካኤል የምሄደው ለመታዘብ ነው ለፀሎትማ ሌላ ቦታ ነው“ ያለው ጸሀይጽድቅ ቤተማርያም የተባለው ሲሆን እነዚህ ሁለቱም የደብሩ አባል ያልሆኑ፣ ደብሩን በሀሰት የከሰሱ ናቸው።

ውድ አንባቢያን ሆይ! እነዚህ የኦርቶዶክስ ልጆች ናቸውን? በዚህ አለም ለመዝናኛም ሆነ ለትምህርት ወደምንገባበት ሁሉ የነጻ ግልጋሎት የለም፣ አገልግሎት ለመስጠት ወጪ  አለውና። አመኑም አላመኑም  መጥተው  ከመገልገል አልፈው  ሆዳቸውንም ሞልተው  ተዝናንተው  የሚወጡበት የሚካኤል ቤት አይደለምን? ባስተናገደና በመገበ ውልታው እንዲህ ነውን? አባል ሁነው  መብትና ግዴታቸውን ተወጥተው  ጥያቄም  ቢኖራቸው  በደንቡ  መሰረት በስርዐቱ መስተናገድ ሲችሉ ምን የሚሉት ክስ ነው መንፈሳዊውን አግባብ ባለው መንፈሳዊ መንገድ የማይፈታ? በባዕድ ምድር በባዕድ ሕግ ሊፈታ እንዴት ይቻላል? እንግዲህ እነዚህ ከሳሾች መሰረተ ቢስ ክሳቸውን ለምን ያደርጋሉ የሚለውን ለመመለስ ከየት ወዴት የሚለውን መንደርደሪያ በመንተራስ ጭብጡን ለመዳሰስ እንሞክራለን።

ፀሀይ ጽድቅ ወይም እስስት የመባል ተቀጥያ ስም  የወጣለት ለዛዛና ሽኮኮ ወደዘመመበት አጎንባሽ በዘመነ ደርግ አቀላማጭ ሱሪውን የፈታ ሆዳም መሆኑ ብቻ ሳይሆንጌቶቹን ተማምኖ የጨዋ ቤተሰብ ሴት ልጅ በሕገ ወጥ አስገድዶ  ደፍሮናጠልፎ  አንግቶ ይዞ ልጆች አስወልዶ በመጨረሻም ደርግ ሲወድቅ ወደአሜሪካ በመምጣት የሀሰት ፖለቲካ ጥገኛ የጠየቀ፣ የልጅቷም ቤተሰቦች የርሱን ለደርግ ያደረ በመሆኑና ባላቸው  የደርግ ፍራቻ ወደ ሕግ ሳይወስዱት የቀሩ። ይህቺን በሕገወጥነት ያነገታትን ሴት ወደአሜሪካን ሀገር የመኖሪያ ፈቃድ ከነልጆቿ ቢያወጣና ቢያስመጣትም ከአንተ ጋርማ ኑሮ ከደርግ ጋር አክትሟል ብላ መሄዷ ምን ማለት እንደሆነ ላንባቢ ትተን፣ ትላንት ጸረ ወያኔ ነኝ ያለና በሀሰት የፖለቲካ ጥገኛና ሞት ለወያኔ ያለ ዛሬ ተገልብጦ ለወያኔ የ፭፪ቱ ገጽ ተገዢ መሆኑ ማንነቱን በግልጽ ያስቀምጣል። ካለፈው ቦርድ ላደኩበት ቤተክርስትያን ብሎ የተሰጠውን ገንዘብ ወስዶ ለአባ ጳውሎስ እጅ መንሻና መሬት መቀባያ ያደረገ፣ በእጅ መንሻውና እርክብክቡን ጨምሮ በወቅቱ አዲስ አበባ ላይ የታተመው ጋዜጣ ላይ የወጣው ዘገባና ምስል ሲያረጋግጥ፥ ዳላስም ሲመለስ ለታባለው ደብር ያስገባበትን ደረሰኝ ያላወራረደ ተራ ዋልጌና አጭበርባሪ ነው። ለወያኔ ሞት ይመኝ የነበረ ከአዲስ አበባ ሲመለስ ለጠላው  ወያኔ የሺህ ዶላር ስጦታ የገባ ነገር ግን ለሚኖርብት ሀገር መንግስት ዛሬም እየዋሸና የሚገባውን የገቢ ግብር የማይከፍል ብቻ ሳይሆን ከመንግስትም  በሀስት እየተደጎመ የሚኖርበት ቤት ምስክር በማስረጃ ያለ ሲሆን እኛ በሀቅ ሰርተንና የገቢ ግብራችንን የምንከፍለውን ገንዘብ በሀሰት የሚዘርፍና የሚያዘርፍ ፤ ተግባሩም የተጋለጠ ዕለት ሁላችንንም የኢትዮጵያ ተወላጆችን አንገት የሚያስደፋ ነውረኛ ስለሆነ የአካባቢው ነዋሪ የኢትዮጵያ ተወላጅ የሆነ ሁሉ ይህንን ለሚመለከተው አካል የማስታወቅ የሕግ ግዴታ አለበት። እንደተረዳነው አከራዩም የኢትዮጵያ ተወላጅ መሆኑን ስለሆነ የምታውቁት ካላችሁ ማስገንዘቡ መልካም ነው እንላለን። የማታ ማታ ግን እኛም በሕግ ግዴታ አለብንና የጨበጥነውን ወደሚመለከተው ማስተላለፋችን አይቀሬ ነው።  

የዚሁ እኩይ የሆነው ሌላው  ተኮላ መኮንን(ተኩላው) ደግሞ የሚያመሳስላቸው፤በወቅቱ የደርግ ከዳተኛ በኃላም ጸረ ወያኔ የነበረ፣ በታክሲና የሻትል የግል ተዳዳሪ ሆኖ ለመንግስት የሚገባውን የገቢ ግብር የሚሰርቅ፣ በሀሰት ለረዥም ጊዜ በመንግስት የሚደጎም ቤት ኪራይ ውስጥ በመኖር መንግሥታችንና ሀገራችንን ሲመዘብር የኖረ፣ በተመሳሳይ የገቢ ምንጭ  የቤት ባለቤት የሆነ ግንዛቤውን ለአንባቢ ትተን፣ ቤተ ክርስትያኑ ተመስርቶ ከአበበ ብኃላ በ፭ ብር የወራዊ ክፍያ በአባልነት ለአጭር ጊዜ ተመዝግቦ የነበረ ለመሆኑ አረጋግጠናል። በወቅቱ የነበረው አስተዳደር የደብሩ መተዳደሪያ የሚሻሻልበት አስተያየት እንዲጠና በሰየመው ቡድን ውስጥ የቀለምም ሆነ የሀይማኖቱ የጠለቀ ዕውቀት ሳይኖረው ባፈጮሌነት የተሰየመ ግለሰብ ሆኖ እናገኝዋለን። እዚህ ቡድን ውስጥ የተሰባሰቡትና የከበቡዋቸው  ውስጥ ማንኛቸውም በአሜሪካን የሀይማኖትና የሕግን ስርዐት እውቀትም ሆነ ስለ ኦርቶዶክስ ዕምነትና የሕግ ስርዕት አስረግጦ ያለውን መስፈርት የማያሟሉ በመሆናቸው፤ በውስጣቸው ጮሌ ሆኖ የተገኘውም ግርማችው አድማሴ የተባለው ከአዲስ አበባ ከአባ ጳውሎስ ቢሮ በሚሰጠው መሪነት ቡድኑን ውስጥ ከታቀፉት መካከል ፍጽም መጨበጫውና መልቀቂያው ያልገባቸውን ዐይናቸውን በመሸበብና ህሊናቸውንም በመጋረድ ፤ ማሻሺያ የሚለውን መመሪያ በሙሉ የተጻረረ አዲስና ፍጹም የተለየ መተዳደሪያ ሕግና ደንብ አርቅቀው ካቀረቡት ውስጥ አንዱ የነበረ ነው። ይህ የታቀደው ሕግ በዚያን ዕለት አባላቱ ተቀብለው ቢፀድቅ፣ከመቅጽበት በስውር ያዘጋጅዋቸውን እነ….. የተባሉትን በአስተዳደር ላይ ማስቀመጥ ነበር። የቅዱስ ሚካኤል ፈቃዱ ባለመሆኑ በዚያው የስብሰባ ወቅት ነበር የአርቃቂው ቡድን የተባለው የልፋቱን ፍሬ ሳያቀርብ እርስ በርሱ የተናከሰውና እራሱንም የአርቃቂ ቡድን አፍርሶ የሞተው። የዚህ ቡድን አባል ሆኖ ለመስራት በዕምነቱ የጠነከረና በጾም በፀሎት እየተረዳ እንደዚሁም የሀይማኖቱንና የሀገሩንም ሕግ እውቀትን የሚጠይቅ ነው። እነተኩላው  ግን ይህንኑ ቀርቶ በቂ የቀለሙም ትምህርት የሌላቸው በመሆኑ የማመዛዘንና የመገንዘብ አድማሳቸው ጠባብ ስለነበር፤ ቃል የገቡለት ይኑር ወይም የስራ ፍሬያቸውን ማጣት አይታወቅም በሚካኤል ደብር ላይ የጥላቻ መንፈስ ከነሱ መውጣት የጀመረው። ገሚሱ የአርቃቂው ቡድን ከነሱ ሲለይ፣ እንርሱ ግን የሙጥኝ ብለው ስለቀሩ ዛሬ እንደነሱ አጽራረ ቤተ ክርስትያን ከሆኑ ጋር ቦድነው   ከፈጣሪያቸውና ከታቦት ጋር ጦርነት የገቡ።

የኦርቶዶክስ ዕምነት የሚጠይቀውን ሥርዐትና ትምህርት አውቀውና ንቀው ወይንም እንደ አርዮን ለመለየት፣ አልያም ልቦናቸውንም ሆነ ዕሊናቸውን ለዲያብሎስ ማደሪያ ወይንም ባለማወቅ የሚፈጽሙት ፀፀት እንዚህን አጽራረ ቤተ ክርስትያን የሚመሩና በተለያየ መንገድ ከሚደግፉት ውስጥም ለምሳሌ ቀዳዳው ወይም ሙሉጌታ ወራሽ የተባለው  በእርሱ ደንቆሮ መሀይም ጭንቅላት የሚመሩት የሚመስሉት ከሳሾች ከእጅ የማይሻሉ ዶማ ናቸው። በዋሾነት የሚኖርና በሀሰት ያለ ሕጋዊ ፈቃድ በህብረተሰቡ ውስጥ እየተሽሎከለክና ተንኮል እየፈጠረ ለፍተውና ደክመው ያጠራቀሙትን ገንዘባቸውን ከግብር አበሮቹ ጋር በመመሳጠር የሚያከስር የንግድ ቤት ውስጥ እንዲገቡና በአጭር ጊዜ ውስጥ ከስረው እንዲወጡ  ያደረጋቸውን ቤቱ ይቁጠረው። የዚሁ ሰላባ የሆኑትም ቢሆኑ ያላአግባብ ያፈሩት ገንዘብ፣ በአጭር ጊዜ ውስጥ ለመክበር በሚያደርጉት ስግብግብነትና ከጠረቤዛ ስር የሚደረግ የሀሰት መዋዋል የሚያካትት ሲሆን፤ ሌላው ግን የዕውቀት ደርጃቸው ነው። በማንኛውም መስክ ያጠራቀሙትን ጥሪት ለእንደዚ አይነቱ ሌባ ጋር ከመደርራደር ይልቅ፣ በምንኖርበት አካባቢ ከብሔራዊ መንግሥት ስር ካሉ እንደ ስሞል ቢዝነስ አስተዳደር፣አይ አር ኤስ፣ ከተለያዩ የሀይማኖት ና መንግሥታዊ ካልሆኑ ድርጅቶች የነጻ ግልጋሎቶችን ማግኘት የሚቻል ሲሆን ባንኮችና ቼምበር ኦፍ ኮሜርስም ይረዳሉ። ከዚህም በተጨማሪ እንደ ንግድ ድርጅቱ መጠን የሕግና የንግድ አማካሪ ድርጅቶች በክፍያ የሚሰጡትም አገልግሎት ከብዙ ጸጸትና ከነቀዳዳው  አይነት ሌቦች እንድትጠበቁ በዚህ አጋጣሚ  እየጠቆምን የቀዳዳው ሰለባ የሆናችሁ ሁሉ የሕግ አዋቂዎችን በቶሎ ብታማክሩ ወይንም ጉድዩ በተፈጸመበት ክልል ወደሚገኘው አቃቤ ሕግ ወይንም ዲኤ መስሪያቤትና የፖሊስ ክፍል ወይንም ከሁለቱም መስሪያቤቶች አቤቱታ ማቅረብ ትችላላችሁ። የቋንቋም ችግር ቢኖርባችሁም በራሳችሁ በሚገባችሁ የሚያስተረጉሙ   ሙያተኞች የማግኘት ችግር የላቸውምና።በዚሁ አጋጣሚ አንዳንድ ወንጀሎች በኢትዮጵያን ተወላጆች መካከል በየቦታው እየተፈጸመ ወደ ሕግ እንዳይቀርብ በኮሚኒቲው  ውስጥ ተደብቆ እንደሚቀርና የኮሚኒቲውም ከሕግ አስከባሪው ጋር ግንኙነት ያልፈጠረ ዝግ ከሚባሉት የኢምግራት ኮሚኒቲ የሚቆጠር በመሆኑ፣ ለምሳሌ ያህል ለመጥቀስ ከአመታት በፊት በከተማችሁ ውስጥ ሕይወቷ በባሏ ቤተሰቦች ያለፈችው ወጣትናየጨቅላ ህጻን እናት ደም ዛሬም ይጮኃል። ባደረግነው  ሙ ከራ እንኳን ራሷን ልትገል መሳሪያ ነክታም የማታውቅ ቅን የዋህ ከድኃ ቤተሰብ የወጣች እንዲሁም ዘመድ የሌላት ምስኪን ደም በሁላችሁም የዳላስ ነዋሪ እጅ ያለ ነው። በተለይም የመረዳጃ ማህበር ነኝ ባዩ ድርጅትም ሆነ ጎረቤት የነበረው ተፈራወርቅ ይህንን የመሰለ የግፍ ግድያን መሸፋፈን በሕግም በሀይማኖት ያስጠይቃል።የሴቶች ማህበር የተባለውስ የከተማችሁ ድርጅት የተለያዩ አሉታን አያመጣም? የተወደዳችሁ አንባቢያን በተቻላችሁ ሁሉ ከዚህ ኃላ ቀር አመለካከት መለወጥ ይገባናል።ወደድንም ጠላን በምንኖርበት ሀገር እንደሀገሩ ሕጉንና ባሕሉን ጠብቀን የመኖር ግዴታችን ሲሆን ከነቀዳዳው አይነት ጩ ልሌም እንጠበቃለን።

ቀዳዳው በያዘው አጽራረ ቤተክርስትያን መንፈስ ማንነቱን ለመዳሰስ ከባድ አይደለም። በየስብሰባው በግልጥ እኔ ነኝ ጠበቃ ያመጣሁትም በገንዘብም የምረዳ እያለ እንደ ጀብዱ የሚናገር፣ አምላክና ታቦት የደፈረ ፣ በሚስቱ ላይ ሌላ ያስቀመጠ ፣ ፈፅሞ ኦርቶዶክሳዊነት የሌለውና ወያኔ ላወጣው ባለ፭፪ ገጽ መመሪያ ለማስፈጸምና ለወያኔ ታማኝ ሆኖ ለመገኘት ቤተ ክርስትያናችሁን ለገጸ በረከት ለማቅረብ ከሚሽቀዳደሙት አንዱ የሆነ፣ የሜይ 2ቱን የደብራችሁን ሁከት ጠንሻሽና በኃላም በዕለቱ ድርጊት አፈጻጸም ላይ የተሳተፈ፣በዚህም ድርጊቱ ከሚጠጣበት የጽዋ ማህበርና እቁብ የተባረረ ነው። ሰሞኑንም እንደ ተጨማሪ አድርጎ የያዘው የተባረረበትን እቁብ ማጥፋት ባለመቻሉ በከተማችሁ ከሚገኘው የግዮን ምግብ ቤት ባለቤት ጋር በመመሳጠር ቅጥረኛ እየላከ እቁቡን ለማስበጥበት ላለፈው ሁለት ሳምንት ገጠመኝ የደረሰንን ስንገልጥ እቁበተኞችም ሆኑ እቁቡ የሚካሄድበት ድርጅት ሳትደናገጡ  ከላይ እንደገለጽነው  እየመጣ ሰላማችሁንና ነጻነታችሁን ለሚነካ ባለጌ ቅጥረኛ ወደ ፖሊስ ማመልከትና እርምጃ በዛ እንዲወሰድበት ማድረግ እንዲሁም  ለግዮኑም ሰውዬ ሥርእት ካልያዘ እንደ ወዳጁ ቀዳዳው  ባስቸኳይ መገለል ነው።

ውድ አንባቢዎች በሚቀጥለው ተከታዩን ይዘን እስክንገናኝ በሰላም ቆዩን!

Friday, October 15, 2010

በዕውነት ሀይማኖት አለኝን?

የርሶ ብዕር አስተያየት ተሳትፎ ሕብረተሰባችንን ይጠቅማል ያሉትን አይንፈጉን ገንቢነቱ ቦታ ይኖረዋልና!

ማሳሰቢያ፡ ይህ ገጽ የተዘጋጀው የተለያዩ የኅብረተሰባችንን ሀሳብ ለመለዋወጫ እንጂ ለሚሰጡት ማንኛውም አስታየቶች በማንኛውም መንገድ ተጠያቂ አይደለም። ጉግል ድርጅትም ኃላፊነት አይወስድም። ኃላፊነቱ በሙሉ የአስታየት ሰጪው ብቻ ነው።


በዕውነት ሀይማኖት አለኝን?

ሀይማኖት ምንድን ነው የሚለውን ጥያቄ በአጭሩ መንፈሳዊ እምነት፣ ይኸውም ከአምስቱ ህዋሳታችን ማለትም ማየት፣ መስማት፣ ማሽተት፣ ማጣጣምና መዳሰስ ውጭ የሆነና በእንግሊዘኛው አጠር ያለ ትርጉም ደግሞ የሚቀጥለውን የሚያካትት ሆኖ ተዘግቧል፡-
 (re·li·gion [ri líjjən](plural re·li·gions)
n
1. beliefs and worship: people's beliefs and opinions concerning the existence, nature, and worship of a deity or deities, and divine involvement in the universe and human life
2. system: an institutionalized or personal system of beliefs and practices relating to the divine
3. personal beliefs or values: a set of strongly-held beliefs, values, and attitudes that somebody lives by

የተወደዳችሁ የገጻችን ተከታታዮች እንደምን አላችሁልን? ደግሞና ደጋግሞ ክብሩና ኃይሉ የማያልቅበትና የሚመሰገነው ልዑል እግዚሀብሔር፣ አሁንም ለክቡር ስሙ  ምስጋና ለእርሱ ይሁን።

ለዛሬ ይዘንላቹህ የቀረብነው  እያንዳንዳችን ጊዜን ወስደን ራሳችንን እንድንመረምር፣ የክርስትና ሕይወታችንን እንድናውቅ ይረዳን ዘንድና ምን ያህልስ ለያዝነው የክርስትና እምነት መተገብርና እንክብካቤን እናደርጋለን የሚለውን እንድንዳስስ ስለሆነ ከዚህ በታች የቀረበውን ጥሁፍ በጥሞና እንድትከታተሉ እናሳስባለን።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ተቀብለናል የምንል ሁሉ፤ ከእምነቱ የሚጠበቅብንን ሁሉ መፈጸም የግድ ነውና። ምክንያቱም ከሌላው የክርስትና እምነት የሚለየን ብዙ ነጥቦች ቢኖሩም የኛ ግን መሰረቱና መመራያው “ሀይማኖት ምግባር ነው“ የሚል ነው። ስለዚህም ሳይነጣጠል ሀይማኖትና ምግባር አብሮ የሚሄድ መሆኑን ማንኛውም የእምነቱ ተከታይ በሚገባ ጠንቅቆ የማያውቅ ካለ እርሱ/እርሷ ሀይማኖታቸውን አያውቁምና ከዜሮ መጀመር ይገባል።

ያለፉት አባቶቻችን ጦር ክተት የሚል አዋጅ ሲመታ ለሀገራቸውና ለሀይማኖታቸው ቀናኢ ሆነው ሲነሱ ካህንም ታቦት ይዞ ወጥቷል። እንደእኛ ዘመን የተሻለ እውቀት ሳይኖራቸው ጥያቄም ሳያደርጉ ለሀይማኖታቸውና ለሀገር ፍቅር በመቃጠል ቀፎው እንደ ተደፈረበት ንብ በመቆጨትና በቁጣ እንደወጣ ታሪኩ በማስረጃ ተደግፎ  ይገኛል። እኛስ ሀይማኖታችን ከውስጥም ሆነ ከውጭ ሲደፈርብን ያንን ያህል ቁጭት ይዘን በቁርጠኝነት እንፋለማለን?

በወቅቱ ከፍተኛውን የክህነት ሥልጣን ይዘው የነበሩት ኢትዮጵያዊው አቡነ ጴጥሮስ ለሀገርና ለሀይማኖታቸው ሲሉ ማንኛውንም ድለላ ብሎም ማስፈራሪያ አሻፈረኝ በማለት ደረታቸውን ለጥይት የሰጡ ቆራጥና ጀግና የሀይማኖት መሪ እንደነበሩ ለማንም የማይካድ ነው። ስለዚህ ይህ ሰማዕትነታቸው ከትውልድ ትውልድ የሚኖርና ሌላው የሀይማኖት ምግባራዊነት ታላቅ ተምሳሌት ናቸው። እኛስ ሌላው ጴጥሮሳዊ ነንን? ወይስ የስም ኦርቶዶክሳዊ ብቻ?

ኦርቶድክስ እምነት የተቀበልን ሁሉ ወይንም እምነቱን ተከታይ ነን የምንል ሁሉ ተግባራዊ እስካላደረግን ድረስ የስም ነጋጆች እንጂ ሀይማኖቱ የለንም አሊያም አናውቀውም ማለት ነው። ያመነ ሁሉ እምነቱን መንከባከብና የመጠበቅ ግዴታ አለበትና። ላመነበትም መስዋዕትን ጨምሮ መክፈልም ይገባዋልና። ለዚህም ነው የዘመኑ ኦርቶዶክስ ሀይማኖት ተከታዮች ነን ባዮች ከውስጥም ሆነ ከውጪ ለሚሰነዘርባቸው ጥቃቶችም ሆነ አጽራረ ቤተክርስትያን ወገኖች ጆሮ ዳባ ልበስ ወይንም አይተው እንዳላዩ ሆነው እንደሚገኙም እሙን ነው። እንግዲህ እምነቱን ከነምግባሩ ካልያዝነውና እምነታችንና ቤተ ክርስትያናችንን ተንከባክበን ካልጠበቅን ፤ ለሚተናኮሉም ካልተቋቋምን፤ ያለፉት አባቶቻችን የተውልንን የመስዋዕት አርያነት ካልተከተልን ኦርቶዶክሳዊነታችንን ከጥያቄ ነው የምንዶለው።

በተለይም በምዕራቡ አህጉር ውስጥ የሚገኙ ቤተ ክርስትያኖች አካባቢ ምዕመን ነን እያሉ ራሳቸውን የሚመጻደቁ ወገኖቻችን አውቀውም ሆነ ሳያውቁ ፣ ቤተ ክርስትያን ስለገቡና ስለወጡ ብቻ የእምነቱ ተከታይ አድርገው እራሳቸውን የሚቆጥሩ ፣ ረፈድ አድርገው በመግባት በአዳራሹ በቅዳሴና በትምህርት ሰአት ሌላ የሚከውኑ፣ ወይንም በሳምንት አንዴ ብቻ ብቅ በማለት ከወዳጅና ጓደኛ ፍለጋ ብሎም ወሬና ነገር ለመቃረም ፣ ወዘተ…የሚያደርጉ፣ የእግዚሀብሔርን ለእግዚሀብሔር የሚለውን አስራትና ሙዳየ ምጽዋት የማያደርጉ የመሳሰሉት የሀስት ኦርቶዶክሳዊያን ቁጥራቸው እየጨመረ መጥቷል። ከእነዚህ ኣይነቶችም ውስጥ አጽራረ ቤተ ክርስትያኖች የሆኑ ይደመሩባቸዋል። በየደብሩ እንደዚ አይነቶቹ የሀሰት ኦርቶዶክሲያኖች የሚቀሰቀሰው ኦርቶዶክሳዊ ያልሆነ የቤተክርስትያንን ሰላም ማደፍረስ ችግሮች በየቦታው እየተከሰተ ይገኛል። ለዚህ እርኩስ መንፈስ ተግባር የሆኑ የበግ ለምድ ለብሰው ከበጎች የተቀላቀሉትን አጽራረ ቤተ ክርስትያን እውነተኛ የኦርቶዶክስ ልጆችና እውነተኛ ካህናቶች የሆኑ ሁሉ ለሀይማኖታቸው ሲሉ ሊመነጥሩዋቸውና ሊያጠፋቸው ይገባል። የሀይማኖቱ እምነት አለኝ የሚል ኦርቶዶክሳዊ ሁሉ ከሁሉም በላይ ለፈጠረው አንድ አምላኩና እምነቱ ቀናዊ ካልሆነ፤ በወዳጅና ጓደኛ፣በጋብቻ ወይንም በስጋ ዝምድና፣ በማህበር ወይንም በድርጅት አባልነት፣ ጠለቅ ባለ እውቀት ወይንም አብሮ መኖር አሊያም በውለታ ብሎ ሀይማኖቱን ወይንም እምነቴ ብሎ የተቀበለውን በተለያየ መንገድ ሲቃወሙ  ሆነ ሲተናኮሉ ማሳለፍ ወይንም እምነቱን ሲፈታተኑበት በዝምታ ወይንም በይሉኝታ ማለፍ ወይንም ማሳለፍ በፍጹም ኦርቶዶክሳዊነት አይደለም።

ለዚህም በምሳሌነት በመውሰድ የምንጠቅሰው ከዚሁ የምዕራቡ ክፍለ አህጉር ውስጥ የናንተ የዳላሱ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ደብረ ምህረት ቅዱስ ሚካኢል ካቴድራል ደብር ቢሆንም ሌሎችም በአህጉሩ ውስጥ በተመሳሳይ ፈተና ያለፉ እንዳሉ ግልጽ ነው። ከሌሎች ተመክሮ እንዳገኘነው፤ እውነተኛ የኦርቶዶክስ ልጆች አንድ ሆነው ከስራቸው የፈለቁባቸውን አጽራረ ቤተ ክርስትያን ቡድን መምታት ብቻ ሳይሆን ከቤተ ክርስትያናቸው አጥፍተዋቸዋል፤ ወደ ፊትም ተመሳሳይ ፈተና እንዳይገጥማቸው ጠንቅቀው እየጠበቁ ይገኛሉ። እናንተም ዳላሶች እውነተኛ የኦርቶዶክስ ልጆች የሆናችሁ ሁሉ በእምነታችሁና በደብራችሁ ላይ የተነሱባችሁ እነዚሁ እምነቱ የሌላቸውና የደብራችሁ ጠላቶች ምን ቢቦድኑ፤ የሀሰት አሉባልታን በመካከላችሁ ቢያሰራጩ፣፣ በዘር፣ በጎሳ፣ በጋብቻና በስጋ ዝምድና፣ በጓደኝነትና ወዳጅነት፣ በጥቅማጥቅም በመደለል፣  በፖለቲካ ሊለያዩዋችሁ ቢሞክሩ፣ በአለም ፍርድ ቤት ላይ ቢያቆሟችሁ፣ በመተዳደሪያው ደንብ የመረጧችኃቸውን አስተዳዳሪዎችን የተመረጡበትን ሀላፊነት በቅንነት ስለተወጡና ለነሱ መጥፎ ተግባር አሻፈረኝ ስላሉ፣ የቤተ ክርስትያናችሁን መተዳደሪያ ሥርዐት ለመናድ ሲያውኳችሁ፣ ምእመናን የሚገባቸውን የቤተ ክርስትያን የንዋይ ስጦታና መባ እንደዚሁም በአባልነት የተመዘገቡት የአባልነት ክፍያቸውን  እንዳያገቡ ሲያሳድሙባችሁ፣ በአደባባይና በስብሰባቸው እኛ ሚካኤል የምንሄደው ለፀሎት አይደለም ነገር ግን የምንሄደው ለመታዘብና ነገር ለመፈለግ ነው ብለው የሚናገሩ፣ ፍጹም የኦርቶዶክስ እምነት የሌላቸው አዋኪያን፣  ወዘተ…… የከፈቱባችሁን አጽራረ ቤተ ክርስትያንና ጸረ እምነታችሁን  ምሽግ የምታፈርሱት እናንተው እውነተኛዎቹና በዳላሱ የቅዱስ ሚካኤል ደብር ያላችሁ የኦርቶዶክስ ልጆች ብቻ ናችሁ።

ዛሬም እንደትላንቱ አባቶቻችን በመስዋዕትነት ያቆዩልንን ይቺን ብቸኛና ብርቅዬ የሆነች የተዋህዶ ኦርቶዶክስ እምነታችሁን ለተተኪዎቻችን ለማቆየት የታሪክ ብቻ ሳይሆን የእምነቱም ግዴታና ሀላፊነት በናንተ ላይ ብቻ ነውና ይህን የቃቱባችሁንና የተነሱባችሁን ጠላቶች፤ በአመራር ላይ በተመረጡት የቦርድ አባሎቻችሁ መሪነት (እስካሁን ቦርዳችሁ እየከፈለ ያለው ተገቢ መስዋዕት ስለሆነ) በመታቀፍ፤ በሌሎች ከተማ ውስጥ ለተመሳሳይ ፈተና እንደተገበረው ሁሉ እናንተም የኦርቶዶክሳዊ ግዴታችሁን መወጣት ዛሬ ወይንም ነገ የማይባል የወቅቱ ግዴታችሁ ነው። ይህንን ግዴታችሁን ሳትወጡ ወይም ችላ ብትሉ፤ “መምጫዬን ማንም አያውቀውም“ ተብሎ እንደተጻፈው ሁሉ፤ በእምነታችሁ ለመጣ ፈተና በእምነታችሁ ጸንታችሁ አለመገኘት ሆኖ እንዳይቆጠርባችሁ፤ በጾም በፀሎት ጠንክራችሁና ሀይማኖታችሁን በምግባር ገልጻችሁ ፣ ደብራችሁን ተንከባክባችሁ በመጠበቅ፣  የጌታችንና መድህናችን የሆነው ኢየሱስ ክርስቶስ ለኛ ሲል የከፈለውን እንደዚሁም አባቶቻችንና እናቶቻችን የከፈሉትን መስዋዕት በማስታወስ ፤ በማንኛውም መንገድ ተዝጋጅታችሁ መክፈል ያለባችሁን ተገብራችሁ ለዘላለማዊው መንግስቱ ትበቁ ዘንድ የተዘጋጃችሁ ሁኑ። ለዚሁም ልዑል እግዚሀብሔር የበቃችሁ ያድርጋችሁ። አሜን።


እርሶስ ምን ይላሉ?      

Tuesday, October 12, 2010

እንደ ሊዲያ ልባችንን ይክፈትልን!

የርሶ ብዕር አስተያየት ተሳትፎ ሕብረተሰባችንን ይጠቅማል ያሉትን አይንፈጉን ገንቢነቱ ቦታ ይኖረዋልና!

ማሳሰቢያ፡ ይህ ገጽ የተዘጋጀው የተለያዩ የኅብረተሰባችንን ሀሳብ ለመለዋወጫ እንጂ ለሚሰጡት ማንኛውም አስታየቶች በማንኛውም መንገድ ተጠያቂ አይደለም። ጉግል ድርጅትም ኃላፊነት አይወስድም። ኃላፊነቱ በሙሉ የአስታየት ሰጪው ብቻ ነው።


እንደ ሊዲያ ልባችንን ይክፈትልን!

ልቤን ክፈተው፣ ልቤን ክፈተው፣
የልዲያን ልብ እንደከፈትከው።

ይኸን ጥቅስ የወሰድነው ለምን ወደ ቤተ ክርስትያን እንደምንሄድና በዚያም የሚሰጠውን የመንፈሳዊ ትምህርት በሚገባ ተረድተን መንፈሳችንን እንድናድስ እንደዚሁም እንባረክበት ዘንድ ለልዑል እግዚሀብሔር የምናቀርበው ፀሎታዊ የመዝሙር ጥያቄ ነው። የተወደዳችሁ የገጻችን አንባቢዎች እንደምን አላችሁ? እኛ የፈጣሪያችን ፈቃድ ሁኖ ደግሞ ለዚህን ሰአት በዚች ጦማር መልሶ እንድንገናኝ ላደረገልን ክብርና ምስጋና ለርሱ ይሁንልን። አሜን።

ባሳለፍነው  ዕለተ ሰንበት ወደ አሉን የዳላስ ወዳጆቻችንና የሚካኤል ሠይፍ ተወካይ ጋር በስልክ ባደረግነው እንደምን አላችሁ? በሚለው ጥያቄ ከተከፈተው ውይይት የተረዳነውን እውነታ መሰረት በማድረግ ነው።

የዳላሱ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ደብረ ምህረት ቅዱስ ሚካኤል ካቴድርል ደብር ካሳለፍነው  እሁድ ጀምሮ በየዕለቱ ቅዳሴ ያለፉትን ብፁህ አቡነ ይስሀቅ ለደብሩ በሰጡትና ለእምነቱ ባደረጉት አስተዋጾ፣ የደብሩ አስተዳደር ከመንፈሳዊ አባቶች ተመክሮ በማስገባት ፣ ስማቸውን በፀሎት እንዲታሰብ መደረጉን የአስተዳደሩ ጠሀፊ ከቅዳሴ በኃላ ማስታወቁ፤ በቤተ ክርስትያን ውስጥ የተገኘው ምዕመን በሙሉ በጭበጨባ ተቀብሎ የደገፈው መሆኑን ስንረዳ አሁንም የደብሩን ገለልተኛ አቋም እንደሚደገፍ ግንዛቤን አስጨብጦናል። ጠሀፊውም በደብሩ ላይ ተከፍቶ ስለ አለው ክስ ሂደት ጎረፍ አድርጎት እንዳለፈ ጭምርም ተረድተናል። እንደዚሁም ደብሩ በቅርቡ ስለቀጠራቸውም መንፈሳዊ አባትና ታዳጊዎችንም በተመለከተ የተቀጠረውን መምህር  አስመልክቶም አጭር መግለጫ የሰጠ መሆኑን ተረድተናል።

ለጥቆም ትምህርቱን የሰጡት አባት ጠሀፊው በሰጠው የክስ ጉዳይ በጣሙን የተነኩ በመሆናቸው ፣ ለዕለቱ ያዘጋጁትን ትምህርትም በፍጹም የቀየሩና በዚሁ ዙሪያ በወቅቱ ፈጣሪ ያቀበላቸውን ብቻ የሰጡ መሆናቸውን በምዕመናኑ ዘንድ ዕምነትን አሳድሮባቸዋል። በወቅቱ ቅዳሴ ከተጀመረ በኃላና ብሎም በማብቂያው ላይ ከተገኙት ውስጥ ከሳሽ፣ አስከሳሽና አካሳሽ የሆኑት ግለሰቦችን ይጨምራል። እኝህ አባት ትምህርታቸውን ከመጀመራቸው በፊት ከላይ ባስቀመጥነው የመዝሙር ፀሎት ሲሆን፣ ትምህርታቸው የነጣጠረው በሙሉ ጠሀፊው ባስደመጠው የክስ ጉዳይ ዙሪያ ሆኖ እንዳረፈደ ነበር።

ክፉኛ በክሱ የቆሰሉ የሚመስሉት አባት፤ ከሳሾቹንና ቢጤዎቻቸውን በውል የማያውቋቸው ሲሆን በዚያ ስለመገኘታቸውም ምንም የሚያውቁት ነገር እንዴሌለ ነው። ስጋወደሙ በሚፈተትበት ቦታ እንዴት ስለ ክሱ ይነገራል?

ቤተ ክርስትያን የጠብ ወይንም የክስ ቦታ አይደለችም ብለው የተቃጠሉት አባት ከዚህ በፊት ሲያደርጉ እንደነበረው በበለጠ ሁኔታን ከመጽሀፍ ቅዱስ በማያያዝ ከሚገባው በላይ አስተምረዋል።

እንግዲህ እንደ ልዲያ ልባቸውን እንዲከፍትላቸው የሁላችንም ፀሎት መሆኑን ለማንም ግልጽ ነው። ይህንን ካልተረዱ ፣ ከድርጊታቸውም ባስቸኳይ ካልተገዱ፣ በሰውና በሀይማኖት አባቶች ትምህርትና ተግሣጽ ካልተቀበሉ፤ ምን መሆን አለበት ትላላችሁ? የሚለውን ጥያቄ ነበር ከየአቅጣጫው የተቀበልነው። የኛ የዚህ ገጽ አዘጋጆች መልሳችንን እንደሚከተለው ስናቀርብ እነዚህ ወገኖቻችን እንደኛው ሰዎች ናቸውና በደካማነት እየፈጸሙ ያለው ጥፋት መሆኑንን ደጋግመን ልናስገነዝባቸው መሞከራችንን ገጻችንና እናንተን ዋቢ አድርገን ነው። አሁንም ከዚያ ከመድረሳችን በፊት በታናሽነትና በትንሽነት ከግራቸው በታች ወድቀን፤ በጌታችንና በመድሀኒታችን በእየሱስ ክርስቶስ ሥም ነገራችሁን ከራሳችሁ ለዩ፤ እንደ ሊዲያ ልባችሁን ክፈቱ፣ ይህንን ሥራ እንደያዛችሁ ብትጠሩስ? መምጫውን ማንኛችንም ፈጽመን አናውቀውምና።

እንግዲህ ሁላችንም ወደ ቤተክርስያን የምንሄደው ለአንድ እምነትና ለአንድ ሀይማኖት ብቻ ከሆነ ፣ እርሱንም በሙሉ ልባችን አምነን ከተቀበልን ፣ ምን የሚሉት ልዩነት ንሮ ነው በመንፈሳዊው መንገድ የማይፈታው? መንፈሳዊ ካለመሆን ከዕምነቱ ውጪ በዐለም ፍርድ ቤት ምንም የሆነ ችግር ማስወገጃ መፍትሄ የለምና በከንቱ ሌላውንና ደብሩን ማመስ ራሱን የቻለ ሀጢያት ነው።
በከተማችሁም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ዕምነት መሰረት በዕውቀትም ሆነ በክህነቱ ከፍ ያለውን ዕውቀትና ሥልጣንን የተቀበሉ አባት የተደጋገመ ትምህርትን በሚገባ የሰጡ ሲሆን መስቀል ይዘው ተንበርክከው ለምነዋል። እኚህ ቆመስ የጉዳዩን እልባት ቁልፍም እንደያዙ የዘነጉ ካሉ ተሳስተዋል። ደጋግመው መክረውና አስተምረው ያልተቀበላቸውን ከእምነቱ መለየትና ማውገዝ የሥልጣናቸውን መብት ስለሆነ፤ ይህንን የፈጸሙ ዕለት የዐለም ሕግ ከሳሾች የተመኩበት ሁሉ ፈራሽ መሆኑን አውቀውታልን? እኝ አባት ድንግላዊ ያልሆነ የቤተክርስትያናችን ካህን ሊሰጠው የሚችለው የመጨረሻውና ከፍተኛው ማዕረግ ያላቸው ሲሆኑ፤ የእርሳቸውን ግዝት ለመፍታት ለማንኛውም ጳጳስ እጅጉን ከባድ ነውና። ምክንያቱንም የሚገባውን ትምህርት ሰጥተዋልና። ፍርድ ቤቱም ቢሆን ሀይማኖቱ ውስጥ የመግባት መብቱና ሥልጣኑ የተወሰነ በመሆኑ፤ የተከሳሹ ደብር ጠበቆች ይህንን ግዝት ከተፈፀመ ያላቸውን ማስረጃ ለፍርድ ቤቱ ካስገቡ የክሱ እልባት ያገኛል የሚል መልስ ነው ያለን።

እርሶስ ምን ይላሉ?  

Friday, October 8, 2010

አይ ጋሽ (ተኮላ መኮንን) ተኩላው፨፡-

የርሶ ብዕር አስተያየት ተሳትፎ ሕብረተሰባችንን ይጠቅማል ያሉትን አይንፈጉን ገንቢነቱ ቦታ ይኖረዋልና!

ማሳሰቢያ፡ ይህ ገጽ የተዘጋጀው የተለያዩ የኅብረተሰባችንን ሀሳብ ለመለዋወጫ እንጂ ለሚሰጡት ማንኛውም አስታየቶች በማንኛውም መንገድ ተጠያቂ አይደለም። ጉግል ድርጅትም ኃላፊነት አይወስድም። ኃላፊነቱ በሙሉ የአስታየት ሰጪው ብቻ ነው።


አይ ጋሽ (ተኮላ መኮንን) ተኩላው፨፡-

ኽረ የፍርድ ቤት ጉዳይ እንዳለብህ ሳንሰማልህ አመሻሽተህ እንደ ቡችላ የኛን ዱካ ያሸተትህ ይመስል በገጽህ ለጠፍክ። እኛ ንቀን ከዛሬ ነገ የተጠናወተህ ወይ ምሮህ ቢሻልህ ብለን ዝምታን መርጠን ተውንህ፣ አንተ ግን እንደ አምናው እያገረሸብህ ካልገደለ የማይለቅ ልክፍት ፣ ዘመን የማሽረው በሽታ የተጠናወተህ ሆኖ እያሰቃየህ ነው ያለህ። እሱ ምህረቱን ይላክልህ እንጂ ተመክሮ የማይገባህ ከአመት አመት የማትለወጥ ነባራዊ ሁኔታ የማያስተምርህ ያኔ በልጅነትህ የለከፈህ ጋኔል ዛሬም ከመታዘዝ አላሰለስክም። ወይ በዘመኑ ሕክምና ካለህበት ማጥ ለመውጣት ቤተሰብ፣ ጓደኛ ወይንም ዘመድ የጨከነብህ መስለህ ተገኘህ፤ ለሁላችንም ፀፀት እንዳትሆንብን ላንተ ከመፀለይ አልቦዘንምና መልሱን ከመጠበቅም ተስፋችን አይቆምም።

እኛ የጣጣፍነው ሁሉ ላንተ ስድብ ይመስልህ ይሆን? የነባራዊ ነጸብራቅ ውጤት መሆኑንና ያሳለፍነውን አልፈን በወቅቱና በውደፊቱ ሂደቶች እያተኮርን፣ ካለፈውም እየተማርን የምንቀጥል መሆናችንን አእምሮህ ማመዛዘን ካቃተው ከለከፈህ አጋንንት ዕድሜ እኩያ እያስቆጠረ ኖሯል። ስለዚህም ነው ንቀትን ያተረፍህ። እኛን ዋሾ ብትለን ሌላም ጨምርበት ፣ ለራስህ እስካመንክበት በራስህ ላይ ብቻ እንጂ ያወቀብህ ሁሉ ደምድሞ ጨርሳል፤ አሁን አዝነው ላንተ የሚፀልዩልህ ሁሉ እያዘኑብህ እየተውት ይገኛሉ። አይዞህ ባዮችህ እውነቱን እየተረዱ በራቁህ ቁጥርና ወደ እውነተኛው መንገድ በተመለሱ ቁጥር፣ ዛሬ አንተ የረፈደበት ብልጠት ይዘህ ከንስሀ መንገዳቸው ልታደናቅፍ እኛን ለመቀባት የማትሞክረው የቀለም አይነት የለም። ካዋጣህ በርታበት።

በዛሬውም ጥሁፍህ የኮነንካቸውን ባናውቅም ስለስርቆት ብዙ ብለሀል። አትስረቅ የሚለውን የተላለፉ አርገህ ቀብተሀል። እኛም ስርቆትን ሀጢያት ብለን ነው የምንኮንን። ሌላውን ከመኮነናችንና ስለድርጊታቸው ከመጣፋችን በፈት እራሳችንን ንጹህ መሆን ማረጋገጥ ተገቢ ነው። ስርቆት አይነቱ የሚቆጠር ቢሆንም የራስ ያልሆነን በተለያየ መንገድ በግልጽም ሆነ በስውር መያዝ መውሰድ መደበቅ ሆነም ጉዳት ማድረስን የመሳሰሉትን ሲያቅፍ፣ የእግዚሀብሔርንም አስራት አለማግባትም ሆነ የመንግስትን ቀረጥ አለመክፈልንም ይጨምራል። ስለዚህም እንግዲህ አንተስ በቂ ገቢ እየሰራህ በህሰት የመንግሥትን ቀረጥ በሕጉ መሰረት አለመክፈል፣ በሀሰት ገቢ በመንግሥት ድጎማ የቤት ኪራይ ውስጥ ለአመታት መኖር ወይንም የአቶ ፍንክሊን ( የሎ ሻትልን) የሚገባ ገንዘብ ባለመክፈል የተጣለብህን ዕምነት አፍርሰህ ያንተ ያልሆነውን ገንዘብ ወስደህ መባረር ከስርቆት አይቆጠርምን?

አባል ባልሆንክበት አንተና ጓደኛህ፤ መብት ብለህ ቤተ ክርስትያን በሀሰት የከሰስክ ብቻ ሳትሆን ስርዐቱን በሀስት ለመናድ የምትንቀዠቀዥ እራስህን ብትመረምር ፤ መብት የሚባለው ከግዴታ ጋር መሆኑን በዚህ ዕድሜህ እንዴት ይሳትሀል? ሁላችንም ወደ ቤተ ክርስትያን የምንሄደው ለአንድና ለአንድ ምክንያት ብቻ መሆኑን ታውቀዋለህን? ምንም ጭማሪ ወይንም ቅናሽ የለውም። አንድ ሀይማኖት አንድ ዕምነት ብቻ ነው። አንተ ግን ምን ከዚህ እንደለየህ ታውቃለህን? እንግዲህ የተለየህ ከሆንክ የተለየ እየተገበርክ ነውና አንተ ፈጽመህ የተለየህ ትሆናለህ ማለት ነው። በዚህ ደግሞ ካልተስማማህ ልብስ መጣል የቀረህ ከፍተኛ የአእምሮ ችግር አለብህና በመጀመሪያ በዛ መስክ አገልግሎት ወደሚሰጡት የዘመኑ ሕክምና አዋቂዎች፣ ዕጣ አውጥተህ ወደ ጠበል አሊያም እንዲጸለይልህ ወደ ካህናት አባቶች መሄዱን እንመክራለን። መጀመራያ የራስህን ተወጣ።

ስለ ፍርድ ቤቱ ውሎህ አንተ በገጽህ እንደለጠፍከው ሙሉ በሙሉ እንዳልሆን ጥሁፍህ ራሱ ይመሰክራል። ምንም እርቀን ብንኖርም ቅዝምዝም ወደዛ እንዲሉ ቀጥተኛ የሆነ ያልተበርዘ ቢሆን መልካም ነበር።ከሚካኤል ስይፍ እንደደረሰን በጠበቃችሁ የጠየቃችሁት የማስርጃ ይሰጠን ጥያቄን ብቻ የተመለከተ ችሎት ነበር። ዳኛው ግን ጉዳያችሁ ሀሰት መሆኑን የተረዳው ይመስል ያልጠበቃችሁትን የቂጥ ዋንጫ አውልቆ ነበር ያስቀመጣችሁ።
አንደኛ/ አባል አለመሆናችሁን ተረድቶ የማይገባችሁ የመርጃ ጥያቄን ነፈጋችሁ።
ሁለተኛ/ ያልጠበቃችሁትን መራራ ጽዋ ያቀመሳችሁ፤ ጉዳዩን እርሱ ለማየት ያልፈለገውና ክሳችሁ የሕግ ነጥብ የሌለው መሆኑ በመገንዝብ ከመዝጋት ይልቅ በተመሳሳይ ጉዳይ በነ ጥሩአየር ላይ ወደ ፈረደው ዳኛ ይፍረድባችሁ በማለትና ከጉዳይ ጋር ተለምዶ አለው የሚለውን ግምት በማስገባት፣ እንደዚሁም የተከሳሽን ጥያቄ ጨምሮ በማስተናገድ መሆኑን ነው። እናንት ከሳሾች አመዳችሁ ቦኖ ጠበቃችሁም ከውሳኔ በኃላ ስለማስረጃው ጥያቄ ቢማጸንም ዳኛው ጥፋ ከፊቴ በሚል በመዶሻው (ጋበን) ጠረቤዛውን የመታበትና አቅሎ ያስወጣችሁ ስለተባለ ይቺንስ ቅመም ለምን ዘለልክ?  

ጛሽ ተኩላው፡- እስቲ በንጹህ ልቦና በገጽህ የጣፍከውን መልሰህ ለራስህ ደጋግመህ አንበው አሊያም ከየትም ያልወገነ የተረፈ ወዳጅ ካለህ እንዲያስረዳህ ልቦና ይስጥህ። ትላንትም፣ ዛሪም ሆነ ወደፊትም ራስህን መርምር። ከፈጣሪህ ለመታረቅና ቂም በቀል ከመያዝ ተወገድ። በመጀመሪያ ፈሪያ እግዚሀብሔርን እወቅ፣ እሱን ከልብህ ከያዝህና አንተ ማረኝ ብለህ ከልብህ ከጠየክ እርሱ ያበራልሀል፣ ህሊናህንም ከፍቶ ማስተዋልን ይሰጥሀል። እርሱን ከተላበስክ እራስህን መመርመር ያስችልሀል ከዚያም ወደ ምንጩ ይመርሀል።

እርሶስ ስለ ተኩላው ምን ይላሉ?

Wednesday, October 6, 2010

በጥሩ ሥነ-ምግባር ስለመታነጽ፡-

የርሶ ብዕር አስተያየት ተሳትፎ ሕብረተሰባችንን ይጠቅማል ያሉትን አይንፈጉን ገንቢነቱ ቦታ ይኖረዋልና!

ማሳሰቢያ፡ ይህ ገጽ የተዘጋጀው የተለያዩ የኅብረተሰባችንን ሀሳብ ለመለዋወጫ እንጂ ለሚሰጡት ማንኛውም አስታየቶች በማንኛውም መንገድ ተጠያቂ አይደለም። ጉግል ድርጅትም ኃላፊነት አይወስድም። ኃላፊነቱ በሙሉ የአስታየት ሰጪው ብቻ ነው።


በጥሩ ሥነ-ምግባር ስለመታነጽ፡-

ስለልጆቻችሁ በጥሩ ስነ-ምግባር ታንጸውና የወላጆቻቸውን እምነት ተቀብለው ጥሩ ዜጋ ለመሆን እንዲያስችላቸው የናንተ ወላጆች ቀና አመለካከት እጅጉን ወሳኝ ነው። በዚች ጦማር አማካኝነት ግንኙነታችን እየዳበረ የመጣው ውድ የዚች ገጽ አንባቢዎች እንደም አላችሁ? ልዑል እግዚሀብሔር ሁላችንንም ይጠብቀን፣ ለገናና ስሙም ምስጋና ይሁን።

እኛም ሆን በታዳሚዎቻችን የሚቀርቡትን መጣጥፍ ውስጥ በሀሳብ የምትስማሙበትና የማትስማሙባቸው እንደተጠበቀ ሆኖ፤ ስለልጆቻችን ግን ከፍተኛ የሆነ አቀራረብ የማድረግ ከእያንዳንዱ ወላጅ የሚጠበቅ ነው። በተለይም የከፍተኛ ትምህርት እድል ያላገኙት ወላጆች ልጆቻቸው ከነሱ የተሻለ እድልን እንዲጎናጸፉ የሚጥሩትን ጥረት በከፍተኛ ደረጃ የሚደነቅ ነው። ለዚህም የከፈሉትና እየከፈሉ ያሉትን መስዋዕት ለሌሎች በአርያነት ሊጠቀሱ የሚገባቸው ናቸው። በአንጻሩም ከአንድ በላይ ወይንም ለረዥም ሰአታት ሥራ የሚሰሩትና፤ በተቻላቸው ሁሉ ጊዜ ወስደው የልጆቻቸውን ትምህርትም ሆነ ከትምህርት ጊዜ ውጭ ባላቸው ማንኛውም ተሳትፎ ሁሉ ካጠገባቸው ሳይለዩ ያሳደጉና የሚያሳድጉ ሁሉ የመጨረሻውን የልጆቻቸውን የተሳካ ፍሬን ሲያዩ ምንኛ የተደሰቱና የታደሉ ይሆኑ ። ይህ በዚህ እያለ ከታዘብነው ውስጥ ብዙ ወላጆች በልጆቻቸው ትምህርት ስኬታማነት እንደሚጥሩ ሁሉ በልጆቻቸው ትምህርት ቤት ውስጥ የወላጅ (ፒቲኤ) ማለት የወላጅና የመምህራን ኮሚቴ ውስጥ የመሳተፍ ከፍተኛ ክፍተት ይገኛል። በተለይም በዚሁ ሀገር ከከፍተኛ የትምህርት ተቋም የወጡት ወላጆች ተሳትፎ የጎደለ ሆኖ ነው የሚገኘው። ይኸው ቸልተኝነትም በየቤተ ክርስትያኖቻችንም ውስጥ ጎልቶ የሚታይና ቤተ ክርስትያኖችም አስፈላጊውን መሻሻል እንዳያደርጉ አሉታን ጥሎባቸው ይገኛል።

ቤተ ክርስትያኖቻችን ከእናት ሀገር ውጭ በባዕድ ምድር በየአቅጣጫው በመከፈት ቁጥራቸው እየበዛ እንደመምጣቱ ሁሉ አብዛኞቹ ያተኮሩት ክርስትና ተነስቶና እምነቱን የተቀበለውን የአዋቂውን ዕድሜ ክልል ውስጥ ያለውን ምዕመን ጎረቤትና አንድ አይነት እምነት ካለው ቤተ ክርስትያን ለመቀራመትና በዚያው ልክ ገቢያቸውን ከፍ ለማድረግ ብቻ የታለመ ሆኖ ይታያል። ቤተ ክርስትያን አስተዳዳሪዎችም የነሱ ዕድሜ የተወሰነና የቤተክርስትያኑም ዕድሜ ውስን እንደሚሆን የተረዱት አይመስልም ወይንም እኔ ከሞትኩ እንደሚባለው አዝማሚያ እየተጓዙ ያሉ አስመስሏቸው ይገኛል፤ የቤተ ክርስቷኗን ቀጣይ መሆኑን እንዴት እንደሚያዩት ግልጽ አይደለም ወይንም ያወጡት የረዥም ጊዜ ዕቅድ የለም። የሚቀጥሯቸው ካህናትም ሆነ ወይንም በግላቸው ቤተ ክርስትያን የከፈቱት ካህናት ከምንኖርበት ሀገር አኗኗርም ሆነ ባህል ጋር የማይጣጣሙ መሆናቸው ፣ የቋንቋ እውቀት ማነስ ፣ የክርስትናውን እምነት የሌላቸውና እንደዚሁም ከኛ ትውልድ ሀገር ውጭ ለሆኑት ጨምሮ የማዳረስ ከፍተኛ ክፍተት የሞላባቸው ሆነው ነው የሚገኙት። በውጪው አለም ጨምሮ ከፍተኛ የመንፈሳዊ ትምህርቱን ያገኙት ታላላቅ የሀይማኖት አባቶችና ሊቃውንቶች ያላት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያናችን በጎ ፈቃድና የሚመቻች መርሀ ግብር በምዕራቡ አህጉር ለምንገኝ ምዕመናንና ልጆቻችን ማቀናጀት ቅድሚያ የሚሰጡት አበይት ተግባር ነውና ጥሪያችንን በዚሁ አጋጣሚ ልናቀርብላቸው እንገደዳለን። ከዚሁ ጋር ተያይዞ በቋንቋውም ጭምር በቂ የሆኑ ካህናትን ማቅረቡም የዚሁ አካል ተጨማሪ ነው።

እናንተ በምትኖርበት በዳላስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ካቴድራል ደብር በቅርቡ ከቀጠራቸው መነኩሴ አባት በዕውቀታቸውም ሆነ ባላቸው የክሕነት ማዕረግ በከተማችሁ አቻ የሌላቸውና በሚሰጡትም አገልግሎት በዕድሜ ከፍ ያለው ምዕመን እጅጉን እየረካና እየተባረከ እንደሚገኝ ከሚደርሱን መረጃዎች በጥልቁ ለመገንዘብ በቅተናል። ከሰንበት ቅዳሴ ፀሎት በኃላ ከሚሰጡት መንፈሳዊ ትምህርት ውጭ፤ ዘወትር አርብ ምሽት ከአንድ ሰአት (7 ፒኤም) ጀምሮ በሰዐቱ ተጀምሮ በፕሮግራሙ መሰረት በሰዐቱ የሚጠናቀቅ የመጽሀፍ ቅዱስ ጥናት ወይም ጉባኤን ይሰጣሉ። የዚሁ የምሽት ጉባኤ ተሳታፊዎችም ዕምነታቸውን ተንተርሶ ብዙ ግንዛቤውችን እየጨበጡና በትምህርቱም እይተባረኩ የሚገኙ መሆናቸውን ተረድተናል።

በሌላ በኩል ለልጆች ተብሎ አዲስ የተቀጠረውም ወጣት መምህር ከልጆቹ ባሻገር ለሁሉም ዕድሜ የሚስማማ የተለያየ ፕሮግራሞችን ይቀርጻል የሚል ከፍተኛ እምነት ብቻ ሳይሆን ተስፋም አሳድሮብናል። በተለይም የሰንበት ትምህርት ቤትን በተመለከተ የመጀመሪያ ዲግሪውን የያዘው ይኽው ወጣት መምህር ለደብራችሁ በዚሁ ዙርያ መሰረት ይጥላል ብለን እናምናለን። ለወገኖቹ አስቦ ይሁን ባናውቅም ከሶስት እጅ የሚበልጥ ክፍያን በዩኒቨርስቲ መምህርነት  የቀረበለትን ዕድል ትቶ ወደናንተ መምጣቱ ወይ የቅዱስ ሚካኤል ተአምራዊ ስራ እንጂ ሌላ የምንለው ባይኖርም፤ እርሱም በቅርቡ የዶክሪት ማዕረግ የሚያስጨብጥ ዲግሪውን ለማከል የሚያስችለውን ትምህርቱን እያጠናቀቀ መሆኑን ተረድተናል። ነገር ግን ይህን ወጣት የተቀጠረበትን ፍሬ ለማየት የእርሱ ብቻ ጥረት በአጭሩ ውጤት ያስጨብጣል ከማለት በፊት፤ የወላጆች ከፍተኛ ተሳትፎን ይጠይቃል። ልጆቻችሁ ከቀለም ትምህርት ቤት ውጪ በሀይማኖታቸውም ታንጸው መውጣት (ኤ ፕላስ) እጅጉን ተመራጭ ነው። በቤተክርስትያናቸው ውስጥ የወጣቶችና የታዳጊዎች ተሳትፎ ከመጥፎ ልማድና መንገድ ብቻ ሳይሆን የሚወግዳቸው፤ ከቤተሰቦቻቸውም ሆነ በኮሚኒታቸው ውስጥ በጥሩ ስነ-ምግባር ታንጸው እንዲወጡ እንደሚያመቻች በበቂ ማስረጃ የተደገፈ ነው። የሚያደርጉትም ተሳትፎ በአንዳንድ ትምህርት ቤቶች ውስጥም እንደ ነጥብ የሚወሰድ ሲሆን ለከፍተኛ ትምህርትም የመመረጥ ብቻ ሳይሆን እስከ ነጻ ትምህርትም ዕድል ለማግኘትም በር ይከፍታል።

እንግዲህ የወላጆችም ተሳትፎ ከፍተኛ ብቻ ሳይሆን በተለይ ከከፍተኛ ትምህርት ተቋም የወጡ ወላጆች አስተዋጾ በከፍተኛ ደረጃ ተፈላጊ ነው። የደብራችሁ አባል ብቻ ሳይሆን ማንኛውም ምዕመን የሆነ ሁሉ በትምህርቱም ሆነ በችሎታው ከዚህ ወጣት መንፈሳዊ መምህር ጋር የተሳሰረ ትብብር እንዲያደርጉ ጥሪ እያቀረብን ፣ መምህሩ ብቻውን የሚፈይደው የተወሰነ እንዳይሆን ከውዲሁ ማሳሰብ የግድ ነውና። ለዚህም ነው ልጆቻችሁንና የናንተም ተሳትፎ የተፈለገውን ውጤት በአጭር ጊዜ ውስጥ ለመጭበጥ እንዲቻል ፣ እንደዚሁም የቤተክርስትያናችሁን ቀጣይነትና የነሱ ተረካቢነት መሰረት መጣል የሚጀመረው ዛሬ ነውና። በዚህ ዝመን ፣ ቀንና ሰአት ላይ ያልተገበርነውን፣ እንዴትስ ብለን ነው ስለ ሀይማኖታችን ቀጣይነት ተረካቢ ሳናዘጋግጅ መርሀ ግብሩን ሳንነድፍ የምናልፈው? ለዚህም የሁላችንም ተሳትፎ ዛሬውን ተጀምሮ፣ ቅዱስ ሚካኤል የሰጣችሁን መምህር በወቅቱ መጠቀም የሚገባ።

እርሶስ ምን ይላሉ?   +

Sunday, October 3, 2010

ቼኩን ማን ይጣፈው?

የርሶ ብዕር አስተያየት ተሳትፎ ሕብረተሰባችንን ይጠቅማል ያሉትን አይንፈጉን ገንቢነቱ ቦታ ይኖረዋልና!

ማሳሰቢያ፡ ይህ ገጽ የተዘጋጀው የተለያዩ የኅብረተሰባችንን ሀሳብ ለመለዋወጫ እንጂ ለሚሰጡት ማንኛውም አስታየቶች በማንኛውም መንገድ ተጠያቂ አይደለም። ጉግል ድርጅትም ኃላፊነት አይወስድም። ኃላፊነቱ በሙሉ የአስታየት ሰጪው ብቻ ነው።


ቼኩን ማን ይጣፈው?

እንግዲህ በምንኖርበት ሀገር በተለያየ መስክ የሕግ የበላይነት በሕጉ አንጻር ይስተናገዳል። ወደ ፍርድ ቤቶች ከሚቀርቡ ወይንም ከሚከፈቱ የተለያዩ የክስ አይነቶች ውስጥ አንዳንዶቹ ከመዝገብ ቤቱ አያልፉም። ሌሎችም ችሎት ተሰይመውባቸው ከሳሽና ተከሳሽ ልዩነታቸውን በበጎ ፈቃድና በስምምነት ያልቃል።  ከዚህ ያለፈውም ችሎት ተሰይሞበት ሁለቱም ወገን ከፍተኛ ጊዜና ንዋይ የሚያፈሱበት ረዘም ያለ ክርክር የሚያሳዩበት ሙግት ያካሂዳሉ። ይህ አይነቱ ሙግት እንደሁኔታው በዝግ ወይንም በክፍት ችሎት ሲሆን ፤ ወሳኝ ሆኖ የተቀመጠው አንድ ዳኛ ወይንም ከዚያ በላይ ሲሆን፤ ከዚህ ውጭም ለፈራጅነት አስተያየት እንዲሰጡበት ከጉዳዩ ጋር ግንኙነት የሌላቸውን ያካባቢው ነዋሪዎች ሸንጎ (ጁሪ) ይሳተፉበታል። የተወደዳችሁ አንባቢዎቻችን እንደምን አላችሁ? በሱ ፈቃድ ዳግም እንድንገናኝ ፈቃዱ ለሆነውና ለተመሰገነው ልዑል እግዚሀብሔር ክብር ምስጋና ይሁን። አሜን!

ለብዙ ጊዜ ሲጠበቅ የነበረውና ለአመታት ብዙ ትግል የከፈላችሁበትን የልጆቻችሁን መንፈሳዊ ትምህርት በተመለከተ ፤ ያሳሰባችሁን ጨምሮ የዳላሱ የቅዱስ ሚካኤል ካቴድራል ደብር አዲስ የቀጠረውን መምህር ሥራውን ለመጀመር ወደናንተ ወደ ዳላስ መግባቱን በመስማታችን በጣሙን ደስ ብሎናል። ዳላስ በነበርንበት ወቅት እንደተገነዘብነው ለልጆቻችሁ የሚመጣጠን አስተማሪ ክፍተት እንደነበር ሲሆን ባለፈውም ጥሁፋችን ለማስረገጥ እንዳሸን ሁሉ፣ ዛሬ የቀጠራችሁት መምህር በጥራቱም ሆነ በብቃቱ የልባችሁን የሚያደርስና የልዑል እግዚሀብሔር መጠቀሚያ እንዲሆን አጥብቀን መጸለይ የሁላችንም ግዴታ መሆኑን ልናስገነዝብ እንወዳለን።

እንዳረጋገጥነው የታዳጊ ልጆቻችሁን  ጉዳይ እንዲያስተናግድ ተብሎ በጀት ተይዞለት የተቀጠረውን ሰራተኛ ለተቀጠረበት ተግባር ባለመዋሉ፣ የወላጅ ኮሚቴ ከአስተዳደሩ ጋር ብዙ አለመግባባት ያደረሰ አንዱ ታላቅ የውስጥ ችግር ነበር። ለዚህም ነበር የወላጅ ኮሚቴ ተቀጣሪው የሰራውን ማወቅና መገምገም ስላልቻለ ለተቀጣሪው ለራሱ የግምገማ ፎርም የሰጠውና እርሱም በተቀጠረበት መሰረት የተገበረው ባለመኖሩ አምኖ ባዶውን የመለሰው። ይህ በዚህ እያለ አስተዳደር ቦርዱ በማወቅ ይሁን ባለማወቅ አሊያም ብቁ የቦርድ አባል ጠፍቶ ይሁን ይህንኑ ለቦርድ ያልተመረጠ ተቀጣሪ የቦርዱ ቃለ ጉባኤ ወይንም ጠሀፊ ያደረጉት። በዚህም ምክንያት በማንኛውም የአስተዳደር ቦርድ ስብሰባ የሚቀርቡ ጉዳዮችን አጀንዳ አቅራቢና አስፈጻሚ በመሆን እራሱን ማኅበረ ቅዱሳን ብሎ ለሚጠራው ድርጅት ከፍ ያለ የገንዘብ ድጋፍ እንዲያገኝ ታላቅ ሚና የተጫወተና እስካሁን ያልተወራረደ ከፍተኛ ገንዘብ በእንጥልጥል ያለ ነው። ከዚሁ የቤተክርስትያን ምዕመን የሆናችሁና ሀገር ቤት ውስጥ ላሉ ቤተ ክርስትያን እርዳታ ጠይቃችሁ የተሳካላችሁ ምን ያህል አቤቱታ እንዳደረጋችሁ ወይም ጭራሹን ያልተፈቀደላችሁ መልሱን ለናንተ ስንተው ፣ ለነ ማኅበረ ቅዱሳን ግን እንዴት እንደነበር ያደባባይ ምስጢር ነውና በዚሁ እንቋጨው።

ስለ ገንዘብ ካነሳን ደግሞ ያልተወራረደው የገንዘብ ጉዳይስ ከምን ደረሰ የሚለውን ለመዳሰስ ካስፈለገ፣ ይህንኑ ጉዳይ እልባት እንዳይኖረው ከውስጥም ሆነ ከውጪ ድንቅፋት እየሆኑ ያስቸገሩ እንዳሉ በግልጽ ይታያል። ምክንያቱም እየተደረገ ያለው ወከባ ቦርዱን በሆነ ባልሆነ ምክንያት በሕግ የተያዘውን ጉዳይ ሁሉ እንሸምግል ባዩ፣ ከሕግ አማካሪዎች በሚቀርቡ ጥያቄዎች መልስን በማስተናገድ፣ አንዳንድ አስቸኻይ ጉዳዮችን መንገድ በማስያዝ የቦርዱ የስብሰባ ግዜ በማጣበብ መሆኑንን ብንርዳም፤ ቦርዶቹ ያለምንም የንዋይ ካሳ ሳያገኙና ከመተዳደሪያ ሥራቸውና ከቤተሰብ ጊዜ ወስደው መሆኑን እንገነዘባለን። ይሁንና በገንዘብ ጉድለት ወይንም ምዝበራ ሀላፊነት አለባቸው የሚባሉትም ከመጠየቅ ለማምለጥ ሲሉ የቦደኑት ከከሳሽ ጎራ ብቻ ሳይሆን የኮሚቴ አባል ሆነው ከውጪ የሚተናኮሉ ናቸው። ከነሱም የቦደኑ ከነሱ የማይሻሉ ቢሆኑም እውነትና ንጋት እያደር ይወጣል እንዲሉ የአምላክን ንዋይ የትም አይቀርምና ከተንኮል እርቆ ጥፋትም ካለ በስርዐት እልባት መፈለግ እንጂ አስቀድሞ በመተናኮል ከውርደት ማምለጥ እንደሌለ ማስተዋሉ የሚበጅ ነው።

ወደ እርዕሳችን ስንመለስ ቼኩን ማን ይጣፈው ? ለሚለው መነሻ ያደረግነው በዳላስ የኢትዮጵያ ኦር ዶክስ ተዋኅዶ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ካቴድራል ደብር ላይ በአይነት አንድ፣ ነገር ግን በተለያዩ ግለሰቦች ሶስት የተለያዩ ክሶች ተመስርተው ይገኛሉ። የመጀመሪያው ክስ ከሳሾች በከሰሱት ጉዳይ ተረተው ለይግባኝ የበቁት መልሳቸውን በቅርቡ እንደሚያገኙ ሲታወቅ፤ ሁለተኛ ከሳሾች ደግሞ የደብሩ አባላት ሳይሆኑ ከሀይማኖቱ ጠላትነት የተነሳ ሌላው ሀሰታዊ ክስ ሲሆን፣ እንሱንም ከኃላ ያጀቡትና እርዳታን የሚያደርጉትና የማንን አጸያፊ ሥራ እንደሚሰሩ ለማንኛችንም ዕሙን ነው። የሶስተኛ ከሳሿም ብትሆን አባል ያልሆነችና ክርስትናው የሌላት የንዚሁ ጥቂት ግለስቦች አባሪ፣ የደብሩን ስርዐትና አመራር ልትንድ የመጣችና የሕግ አስከባሪ ትዕዛዝን አሻፈረኝ ያለች ሕገ ወጥ ግለሰብ፤ ጭራሹንም ክርስትና ምን እንደሆነ የማታውቅ ነች። የርሳንም ጉዳይ የካሳ ጥያቄ በመሆኑ ወደ ደብሩ የመድህን ድርጅት ተመርቶ በዛ የሚስተናግድ ነው። የሚገርመው የመጨረሻዎቹን ሁለት ክስ ከሳሽን ወክሎ የከሰሰው አንድ ጠበቃ ሲሆን፣ ስለታሪኩ ትንሽ ብንጠቅስ ግለሰቡ ቀደም ሲል በሥርዐት እክል ገጥሞት ከዳኝነት የተወገደ ሲሆን ጥብቅናው የጥብቅናን ሥነ-ምግባር የማይከተል ለመሆኑ ሁላችንም የምግባሩ ምስክሮች ነን። ከክሱ መሰሚያ ዋዜማ ምሽት በቴሌቪዥን ቀርቦ እኛን ፣ ትውልድ ሀገራችንን፣ ሀይማኖታችንን ፣ማንነታችንን በዐለም የሕዝብ ሸንጎ የኮነነና ያዋረደ እንደዚሁም ይህንኑ በማግስቱ ከጉዳዩ ጋር በማይገናኝ በፍርድ ቤት ውስጥ አቅርቦ የደገመ የለየለት……….. ሲሆን ይህንኑ ግለሰብ ለዚህ አሳፋርና አዋራጅ ምግባር ያመጣው ግለሰብ (ቀዳዳው) የተባለው እንድሰማነው የግል ጠበቃው ሲሆን፣ በገንዘብ የተሳተፉትና እንዲወክላቸው የቀጠሩት እንደዚሁም አብረው ቦድነው የሚያቃልጡ ሁሉ እስቲ ራሳቸውን ይመርምሩ? እንርሱ በርግጥ ሀይማኖታቸውን ያውቁታልን? እራሳቸውንስ እውነት የኢትዮጵያ ተወላጅና ተቆርቋሪ ነን ብለው ይቆጥሩ ይሆን? ኸረ የሀይማኖት ያለህ!
ኸረ ያገር ያለህ!  ምኑን ነው ወይስ ዘመን ገባን? ሀገርን ፣ ሀይማኖትን፣ ባሕልን፣ ወገንን አንገት ያስደፉ? ኽረ ፈጣሪ ልቅሶና ጸሎታችንን ስማ! ለቅሶቻችንን ታብስልን ጸሎታችንንም ትቀበል ዝንድ በአንዱ ልጅህ ለኛ ደህንነት በፈሰሰው ደሙ የነሱንም ስህተት የኛንም ግድፈት እጠብልን? ለማይልቅብህ ምሕረትህ ክብርና ምስጋና ይግባህ። አሜን!

እንግዲህ እርሱን ደፍሮ መንፈሱንም ረግጦ ወደ አለማዊው ፍርድ ቤት ሀይማኖትን ከሶ በዚህም ሀገርን፣ ሕዝብን፤ ሀይማኖትንና ባሕልንም አስደፍሮ፤ የራስን ማንነትም አዋርዶ በእንግዳ ሀገር ፍርድ ቤትም ተደርሶ ፤ የማታ ማታ አይቀሪ ነውና ከአንድ መርጋቱ። እኛ እንደምንገመግመው ከሆነ ከሳሾቹ ምንም የሕግ ነጥብ እንደሌላቸው ሲሆን ፤ የረባም ንዋይ እንደሌላቸው ነው። እስካሁን ድረስ የቅዱስ ሚካኤል ደብር የባንኩን ቼክ ሲጥፈው እንደነበር ሁሉ ያን የማስመለስ የግድ ነውና፤ ከኃላ ሆናችሁ እኔ ወይም እኛ ያላችሁ፣
ሁሉ ማንነታችሁ በሚገባ ተዘግቦ በማስረጃ ያለ ስለሆን አሁን ማምሻው ሰአት ደርሳልና፣ የጠበቅነውና የጠበቃችሁትና የተመጻደቃችሁበት የፍርድ ሰአት መጥቷልና ፌዝና ሳቁ አልቋልና አሁን ተረኛው እየለየ ነውና ማን ቼኩን ይጣፈው? በጊዜም ድርድር ለመግባት የሞከሩ እንዳሉም እየሰማን መሆኑ ባይደንቀንም የደብሩ ወጪ ግን መተካቱ አይቀሪ ነውና በሰፈሩበት መሰፈርም ይኸው ነውና እንግዲህ መክሰስ ብቻ ሳይሆን ግልባጫ እንዳለው ቀድሞን መገንዘብ መልካም ነበር።

እርሶስ ምን ይላሉ?