Saturday, August 27, 2011

የርሶ ብዕር አስተያየት ተሳትፎ ሕብረተሰባችንን ይጠቅማል ያሉትን አይንፈጉን ገንቢነቱ ቦታ ይኖረዋልና!

ማሳሰቢያ፡ ይህ ገጽ የተዘጋጀው የተለያዩ የኅብረተሰባችንን ሀሳብ ለመለዋወጫ እንጂ ለሚሰጡት ማንኛውም አስታየቶች በማንኛውም መንገድ ተጠያቂ አይደለም። ጉግል ድርጅትም ኃላፊነት አይወስድም።


የተወደደዳችሁ የዚህ ገጽ ተከታታዮች በያላችሁበት፡  እንኳን በሰላምና በጤና ለቡሄ በአል አደረሳችሁ! የፍልሰታን ፆም በሰላም ለመፍታት አበቃችሁ! ልዑል እግዜብሔርም ያቀረብነውን ፆም፣ ፀሎት፣ ምህላና ሱባኤን ይቀበልልን። ፈቃዱም ሆኖ መልሰን በዚች ገጽ ዳግም ለመገናኘት ስለፈቀደልን ለክቡር ስሙ የማያልቅ ክብርና ምስጋና ይሁንልን። በአንድ ቤተ ክርስትያን ስር በአባቶች እንዲሁም በወንድማሞችና እህትማሞች መካከል ፍቅርና አንድነትን ይስጥልን። በትውልድ ሀገር ኢትዮጵያና በአካባቢው ያለውን የአየር መዛባትንና የፈጠረውን የረሀብ ችግር ያስወግድልን። በዚህ በምንኖርበት ሀገረ አሜሪካ በምስራቀ የባሕረ ሰላጤ እየደረሰ ያለውን ሄርኬን አይረን ፈጣሪ ጥበቃና ከለላውን ያድርግልንን፣ መአቱን ይመልስልን። ወገኖቻችንን ለሚያስተዳድሩ ሁሉ ቅን ልቦናንና ፈሪያ እግዜብሔርን ይስጥልን፣ ይታደግልን። የምንኖርበትንም ሀገር እርሱ ይጠብቅልን። የኛንም ሕይወትና ኑሮ ባርኮ ቅን መንፈስን ይስጠን። አሜን።

ለተሳትፎ መጣጥፎቻችሁና ተሳትፎዎቻችሁ ሁሉ ልባዊ ምስጋና ይድረሳችሁ በማለት የፍልሰታን ጾም ምክንያት በማድረግ ገጿ አፈግፍጋ መክረሟን በቅድሚያ ታስገነዝባለች። ነገር ግን ከመስመር የወጡና እራሳቸውን የቤተክርስትያን ብቸኛ ልጅና ተቆርቋሪ አርገው በመቀባት የቆሙት ወንድሞችና እህቶች ሀሰታዊና ከክርስትናው መንገድ የተጻረረ መጣጥፍ በገጾቻቸው መለጠፋቸው የሚታወቅ ነው። ችግሮች እንኳን ቢኖሩ በፍልሰታ ወቅት ወደ ፈጣሪ ልመናና ፀሎት እንጂ ባገልጋዮች ላይ የሚያቀርቡት መስመር ዘለልና ነቀፈታዊ የሀሰት መጣጥፍ ኢ ክርስትያናዊ መሆናቸውን ዳግም አረጋገጠ እንጂ ያመጣው ውጤት የለም። እነዚህ ጥቂት ግለሰቦች ደብር በጥባጮች በመሆን መሰሪነትን የሚመሩ ናቸው። ንጹሀንን በማሳሳት ደብር እንዲከሱ ማድረግና አንድነትን ለመናድ የሚያደርጉት እንቅስቃሴ ሁሌም እንደከሸፈባቸው ነው። ከለቀቁት ደብር ውጪ ሆነው የሚያካሂዱት በዕምነት ላልጠነከሩት ምክንያት እንዳይሆኑ ያሳስባል ወይንም ወደ ሌላ ዕምነት እንዲነጉዱ መንገድን ያመቻቻል። ስለዚህም ምግባር በአጽራረ ቤተክርስትያንነት ያስፈርጃቸዋል። ምሳሌ በማድረግም ከምንጠቅሰው ውስጥ የዳላሱን ቅዱስ ሚካኤል ደብር በአባልነት ካሉ ተባባሪዎቿቿው አማካኝነት በፍልሰታ መጀመሪያ ዋዜማ ያስጠሩት የአባላት ጠቅላል ስብሰባ ኮረም አልሞላም በማለት ቢሰረዝም ፤ እንደ ክርስታዊነት ለጾም መዘጋጀት በተገባ ነበር። ከነዚህ ተሰብሳቢዎች መካከል ከደብሩ አባላትነታቸውን ያለቀቁ ነገር ግን ወደ ሌላ ቤተክርስትያን የተቀላቀሉና የአዋኪና የከሳሽ ቡድን ደጋፊዎችና ተባባሪዎች ናቸው። ቤተክርስትያን ማለት ምን ማለት እንደሆነና ዕምነትስ ምን እንደሆነ ፈጣሪ ይምከራቸው በማለት ገጿ ታሰምራለች።

የሚካኤል ሠይፍ ተወካይም ተመሳሳይ ያለው አመለካከት ቢሆንም በቅርቡ የተጠራውን ጠቅላላ ስብሰባ በጥቂት እባጮች የተመራ መሆኑን አልሸሸገም ። ከጠራቸው ስሞችም ውስጥ ዛሬም በነበትሩ ገ/እግዜአብሔር ፣ ኪዳኔ አለማየሁ፣ ጌታቸው ትርፌና እነኤዮኤል(ክፈተው) ነጋ በመሳሰሉት ነው። እኛም እንደምንረዳው፤ በትሩና ኪዳኔ ማንኛውንም ድርጅት ቀርበው በመንጠቅና በመዘበር፣ በማፈራረስና ለትግሬ ነጻ አውጪ በማሳለፍ የታወቁ ናቸው። ጌታቸው ትርፌ የተባለና ትምህርት የሌለው ጎንደር የተወለደና በዘሩ ኤርትራዊ፣ አማርኛና ትግርኛ በመቻሉ ብቻ የስደተኛ ረዴት ድርጅት የተቀጠረና፤ ሳቦታጅ በማድረግ ከእርሱ ያልተባበሩትን ሌሎች ኢትዮጵያዊያንን እንዲባረሩ የሚያደርግ፣ በሚስቱ የመለሰ ሚስት አክስት በመሆኗ ደብሩን ለትግሪ መንግሥት ተመሪ ለመስጠት የሚሯሯጥና በቅርቡም በደብሩ ውስጥ በመስተንግዶ ኮሚቴ የሚያገለግሉትን እንዲተዉ ሳቦታጅ ስለሚሰራባቸውና ቦርዱም እርምጃ ስላልወሰደ፤ በተለይም ቦርዱን ወክሎ የመሰተንግዶ ኮሚቴን የሚመራው ሊቀ መንበሩ የጊታቸው ቤተኛ በምሆኑ ጨምሮና እርምጃ መውሰድ ስላልተቻለ በመልቀቃቸው፤ የደብሩ አስተዳደር ያላወቀውንና ያልተቀበለውን ፤ የመረዳጃ ማህበሩ ቦርድ አባልና አንዴ ለቅቄ አለሁ በማለት በሀሰት ነገር ግን መርዳጃውን ከሚያፈርሱት የነበትሩ ሎሌ፣ በትምህርት ያላገኘውን የዶክተርነት ማዕረግ የሚሞካሽበት አምሀ የተባለውን ቢጤ አፍራሹን ለአጋርነት ያስገባና ለወደፊትም የቦርድ ምርጫ የሚያዘጋጀው ሎሌው፤ ነገረ ስራው ሁሉ አጽራረ ቤተክርስትያን እንጂ ከቆረበ ኦርቶዶክስ የማይጠበቅ። ክፈተው / ኤዮኤልም ቤሆን ለረዥም ጊዜ የደብሩ ተመራጭ ሆኖ ላደረሰው ምዝበራና በደል ገና ለገና እጠየቃለሁ በማለት ዛሬ ደብሩን ከሚከሱና ከሚያፈርሱ ወገን ግምባር ቀደምት ቦታን የያዘና ፣ ተመረጭ በነበርበት አጋጣሚ ከሚያውቀው በመነሳት የደብሩን ስስ ጎኖችና ሰነዶችን በማካፈል የሚጎዳና በግልጽ ከምዕመናን ጠቅላላ ስብሰባ ላይ የተጣለበትን የተመራጭ ሀላፊነት ጥሎ የለቀቀ ፤ ለምንም የማይሆን ማፈሪያ ነው። በእርሱም ጌዜ የቦርዱ ጠሀፊ የነበረው ሀይሉ የተባለውና የኔጊታቸው ዘመድም እስከ ዛሬ በእጁ ያለውን የደብሩን ሰነድ አላስረክብም ብሎ የያዘ ነውና ገጻችን በሕግ መጠየቅ አለበት ነው የምትለው።
   
‘ቅዱስ ሲኖዶስ የብፁህ አቡነ ዜና ማርቆስን ውግዘት አንስቶ ሥርዐተ ቀብራቸው በኢትዮጵያ እንዲፈፀም ፣ አስከሬናቸውም ለጵጵስናቸው በሚገባ ክብር ፣ አበው ጳጳሳት በሚያርፉበት በመ/ፀ/ቅ/ሥላሴ ቤተ ክርስትያን እንዲያርፍ ወስኗል።‘ይህ መግለጫ መንበሩን በኢትዮጵያ ያደረገው ሲኖዶስ የብፁነታቸውን ማረፍ አስመልክቶ የሰጠውን ፤ ገጻችን እርሶስ ምን ይላሉ? በሚለው ከተወረወረልን ያገኘነውን አርፍደን ብናካፍላችሁም ነገሩ አስቂኝ ነው። ምክንያቱም በቤተ ክርስትያን የውስጥ አስተዳደር ምክንያት የተነጠለ የክርስትና መብቱም አብሮ የሚገፈፍበት አልፎም ወደ ትውልድ ሀገሩ በሕይወት ብቻ ሳይሆን ኮርብሱም ወደ ትውልድ ሀገሩ እንዳይመለስ የሚያግድ የቤተክርስትያኒቱ ሆነ የሀገሪቱም ሕገ መንግሥት መኖሩን ገጻችን ስለማታውቅና የጠየቅናቸውም የሕጉ ባለሙያዎች ጨምሮ እንደማያውቁት ሲሆን አለ የምትሉ ጀባ በሉን። ሲኖዶሱ ሕግን ጥሶ የቀደሙትን ጳጳስ በአካል ሳይመረምር በላያቸው ላይ አዲስ መሾሙ ያመጣው ውዝግብ በአባቶች መካከል መከፋፈልን ብቻ ሳይሆን በምዕራቡ አለም ላለነው የቤተክርስትያኒቷ ልጆችም በትውልድ ሀገር አጽማችንን ለማሳረፍ የአዲስ አበባውን ሲኖዶስ ፈቃድ ሊያስፈልገን ይሆን? ብፁእነታቸው በሕይወት ለምን ተወግዘው ፣ ሲያርፍ ለምንስ ውግዘቱ ተነሳ ለሚለው ጥያቄ የእርሶ መልስ ምን ይሆን? ገጻችን በሕይወት የተወገዙበትንና ሲያልፉ የተነሳላቸውን ምክንያት ውግዘቱም ሆነ ሽረቱ በራሱ ለራሱ መልስ ነው። ውግዘቱ ሀቅን ለመሸፈንና ለማሳደድ እንዲመች ሲሆን፣ ሽረቱ ደግሞ አሁን በምድር በሕይወት የሉምና እውነታቸውን ይዘው ስላለፉ ፤ በዕምነታቸውም ተሰደው በመፅናታቸው ፤ በመንግሥቱ ፊት በፈጸምነው በደል እንዳያሳቅቁን ብለው ይሆን?

ጳጳስ መሰደድ አዲስ ነገር አይደለም። ከግብጦችም ተምረናል። በቅርቡም በትረ ሥልጣኑን እመራለው የሚሉት ሊቀ ጳጳስ ዘ ኢትዮጵያ አባ ጳውሎስ በዚሁ በምዕራቡ አለም በዲሲና ካልፎርኒያ የፖለቲካ ስደተኛ ሆነው አገልግሎት ሰጥተውናል። በእጃቸው መባረክ ብቻ ሳይሆን ወዳጅነትንም በወቅቱ አትርፈናል። ዛሬ ደግሞ ተለያይተናል ነገር ግን እኛም ሆን እርሳቸው የቤተክርስትያኒቱ ልጆችነታችን እሙን ነው። ምንም ሁላችንም ዜግነታችንን ብንለውጥም ቀደም ባለው ታሪካችን ከግብጥ ሊቀ ጳጳስ ይሾምልን እንደነበር ማስመር እንወዳለን።

 ባለው የቤተክርስትያኒቱ ሕግ መጣስ ምክንያት የአባቶች መለያየት ፤ ዛሬ ተሰደው በሰሜን አሜሪካ የሚገኙት አባቶች የተጣለባቸውን የአባትነት ግዴታ በተቀናጀ መልኩ በሚገባ እንዲወጡ በማሰብ የራሳቸውን ጉባኤ በማድረግ ሲኖዶስ መስርተው ምዕመኑን በማገልገልና በትውልድ ሀገር ላሉትም ቤተክርስትያንና አገልጋዮች ጨምረው በፀሎት እየተጉ ይገኛሉ። ሕግ አይጣስ ፣ አንድ ዕምነትና ሀይማኖት ፀንቶ ይኑር፣ ስህተት ይታረም ከማለት ውጪ ቤተ ክርስትያኗ እንድትከፋፈል ፈፅመው እንደማይፈልጉ ዘወትር በግልጽ በአፅኖ ይመሰክራሉ። አንዳንድ አካባቢ እንደምናስተውለው አንዳንድ ከፋፋይ ግለሰቦችን በመከተል የተሳሳተ መስመር ላይ የሚከተሉትን ወገኖቻችንን ስናይና በዚህ ዙርያ ሁከትና መከፋፈልን በምዕራቡ ሀገር ቤተክርስትያን የሚያስፋፉ ታዝበናል፣ ስለእነርሱም ዘወትር እንጸልያለን።

ማን ነው የትኛውን? የውጪውን ወይንም የሀገር ቤቱን አንዱን ብቻ ሲኖዶስ በመከተል የእግዜብሔርን መንግሥት የሚወረሰው ብሎ የሚነግረን? ማንም እንደሌለና መዳንም ሆነ መንግሥቱን መውረስ የሚቻል በኢየሱስ ክርስቶስ አምኖ፣ በእርሱ ስም ተጠምቆ፣ ስጋ ወደሙን ተቀብሎና በቅዱስ መፅሀፍ እንደተጣፈው ሲኖር ብቻ መሆኑ የታመነ እንጂ በሲኖዶስ የሚተካ አይደለም። በዚህ ወይንም በዚያ ሲኖዶስ መመራት ሳይሆን፣ ወይንም የአንደኛው ወገን የሆነውን አገልጋይ ግልጋሎትን መሻት አይደለም። አንዳንዶች በመጣጥፋቸው ወገናዊነትን ያሳያሉ። የሌላውንም አባላትንና አገልጋዮችን ሲኮንኑ ይስተዋላሉ። የቤተክርስትያኒቱንም ልጅነታቸውን ለመቀማት ያዳዳቸዋል። እነርሱ የክርስትና ልጅነታቸውንም ለመቀማት ይችሉ ይመስል የማይቀቡት የላቸውም። ሀይማኖቱ እንዳይሰፋና በዕምነታቸው የቀጨጩትን እንዲጠፉ ፣ ዕምነቱን ለመቀበል የሚዳዱትንም እንዲሸሹ ፣ በተለይም በምዕራቡ አህጉር ለተወለዱትና ለሚወለዱትም የመሸሻ ምክንያት እየሆኑ ይታያሉ። እውቅ መምህራን እንዳያስተምሩ እንከን ይፈጥራሉ። ወይ እነርሱ አውቀው አያስተምሩም። ለማወቅም የማይፈልጉ ዝጎችና ቤተክርስትያኒቷን ጎጂ ምግባርን ብቻ ያካሂዳሉ። እነርሱ አመራሩን ካልጨበጡና ካልመዘበሩ ሌላው ቤተክርስትያን አይመስላቸውም። ለምሳሌ የዳላሱን ደብረ ምህረት ቅዱስ ሚካኤል ካቴድራል ደብርን ብንወስድ፡ ለብዙ አመታት ማህበረ ቅዱሳን / ማቅ የተባለው የቤተክርስትያናችን በቀል ቡድን ተሰሚነትን አግኝቶና አመራሩን ተቆጣጥሮ የእርሱን ወገንና አባላቱ የሆኑትን መምህራንን ብቻ ሲያስመጣ ነበር። ምዕመኑ በተለያየ ወቅት ሌላም መምህር ከዚህ ቡድን ውጪ ቢጠይቅ ፣ አልፎም ፊርማ አሰባስቦ ቢያቀርብም ሰሚ አጥቶ ነበር።
በቅርቡ ደግሞ አንድ የሀገር ቤቱን ሲኖዶስ ተከታይ መምህር ለ3 ጊዜ ሌላም እንደዚሁ መጥተው ቃሉን ሲያስተምሩ ምንም አይነት ተቃውሞ ከማቅና ከመሰሎቹ አልተሰማም። በቅርቡ ደግሞ ከሰሜን አሜሪካው ሲኖዶስ በተገኘ መምህር ሊያፏጩ ይዳዳሉ። ገጻችን የምትል ሁሉም የቤተክርስትያን ልጆችና ለአገልግሎት የበቁ ስለሆነ ምዕመኑ ከማንኛውም ወገን የሚገኙትን አገልጋዮች በእኩል የሚያይና የሚገመግም መሆኑን መረዳት እንዴት ተሳናቸው? መንፈሳዊ ቅናት ቢሆን እንኳ ለአባቶች አንድነት አጥብቆ መፀለይና አንድ ወጥ አመራር የሚመጣበትን መተለምና መሳተፍ ከቅንነት አልፎ ዋጋን ከፈጣሪ የሚያስገኝ መሆኑን እንዴት መለየት ያዳግታል። የሚያውካቸው ከሆነ ደግሞ ይህ ከቅዱስ መንፈስ ውጪ ነውና ሁላችንም ለተሳሳቱት መፀለይ ይገባናል። የአባቶች ልዩነት የፈጠረውን ዋና ምክንያት የሆነውን ቀነኖ በመገንዘብ አንድነትን እንዲፈጥሩ ምዕመናን የሚገባውን ጾምና ፀሎት ከማድረግ አልፎ በመካከሉ ልዩነት እንዳይኖርና አባቶችም አንድ እንዲሆኑ የተቻለውን ሁሉ በማድረግ ማሳሰብ ይጠበቅበታል።

በሌላ በኩል ለምሳሌ እንደ ዳላሱ ቅዱስ ሚካኤል ገለልተኛ የሚባለው አይነት አካሄድ እስከ መቼ ድረስ ይዘለቃል? ቀደም ሲል ብፁእ አቡነ ይስሐቅ (ፈጣሪ ለነፍሳቸው ማደሪያ ይስጥልንና) ነገሩ በቶሎ የሚቋጭ መስሏቸው ይሁን ወይም ሌላ በገለልተኛነት መቆየትን መርጠው ነበር። ከማለፋቸው በፊት የወደፊቱን እጣ ያስቀመጡትን ገጻችን ባታውቅም የአባት አስፈላጊነቱ እሙን ነውና በተመሳሳይ መስመር ያሉትም ጊዜው ከማለፉና ችግር ከመባባሱ በፊት መቋጫ ከወዲሁ ማጤን ይገባል። ገፃችን ካላት ግንዛቤ ልታካፍል የምትወደው ቢኖር እንደሚከተለው ነው። ገለልተኛ የሆኑ ሁሉ አመራሮቹ ያለምንም ወገንተኛነት ከሁለቱም ሲኖዶሶች ምሁራንን እየጋበዙ ስለቤተክርስትያናችን ሕግና ስርዐት ፣ በሁለቱም ሲኖዶሶች ላይ ጥልቅ ግንዛቤን በማድረግና በተረጋጋ መንፈስ እርስ በእርስ በመመካከር በአባሎቻቸው ምዕመናን በጎ ፈቃድ ላይ የተመሰረተና መንፈሳዊ የሆነ ምላሽ እንዲሰጡ ነው። የዳላሱን ቅዱስ ሚካኤልን በተመለከተ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ይህች ገጽ ነቀፊታ፣ ማበረተቻና የግሏን አስተያየት ስትወረውር መቆየቷ የሚታወስ ነው። ነገር ግን የትኛውን ሲኖዶስ ይከተል የሚል አቋም ወስዳ አታውቅም። ውሳኔው ሁሉ የደብሩ አባላት ብቻ እንጂ የማህበረ ቅዱሳን /ማቅ ወይንም የውጪ ጥቅማ ጥቅም ፈላጊዎች አሊያም የወገኑ ድብቅ አላማ ያላቸው ጫና መሆን የለበትም። ለዚሁ ምእመኑ የራሱን ግንዛቤ እንዳይጨብጥና የጠለቀ ዕውቀትን እንዳይኖረው በተቀጠሩና በተጋበዙ መምህራን ላይ በማያገባቸውና ከመንፈሳዊ መንገድ ውጪ የቀደምት ሁከታቸው፣ ክስ ከሳሽና አስተባባሪነታቸው አልፎ ወሳኝ ከሳሽና  ዳኛ እንዲሁም ፍርድ አስፈፃሚ ሆነው ዛሬም ሰይጣናዊ ከፋፋይ ምግባር ላይ  ይታያሉ። እግዜብሔር ምህረትን ይስጣቸው ፣ ልቦናቸውንም ለውጦ ቀና መንገዱንም ያስይዛቸው። እነርሱም ዋሻ ያደረገውና በቅርቡ የተከፈተው እንዲሁም በአዲስ አበባ ሥር ያለው የዳላሱ ተክላይማኖት አቡነ አረጋዊ ቢሆንም በመከፈቱ ገጻችን አልተቃወመችም እንደውም ምርጫ ለምዕመኑ በዛ እንጂ፤ እዛ በካሕንነት ከሚያገለግለው አንዱ ከፈጣሪ የተቀበለውን የጠባቂነትን ሀላፊነት ከፑልፒት ላይ ‘ባትሪዬን ጨርሻለሁ “ ብሎ ሲኮበልል፣ ብሎም ከሚካኤል አጥር ስር ሆኖ ኢ ክርስትያንዊ ምግባርን ሲያከናውንና መጥፎ መጣጥፍን በብሎግ ሲለቅ የነበረው መቼ ንስሀ ወስዶ ነው ከዚያ የሚቀድስም ሆነ የሚያስተምር። ሌላውም ጎጠኛ ብቻ ሳይሆን ሚሽቱ ስትማግጥና ማህተሟን ስታፈርስ በቤተ ክርስትያኗ ህግ መሰረት ፈትቶ መመንኮስ እንጂ አብሮ መኖር የማይገባው በመሆኑ ፤ ከነሱ የመንፈሳዊ አመራር ምን ይጠበቃል? ለዚህም ነው ዛሬ ኢ ክርስትና መዶለቻና መጠንሰሻ ጎራ በማድረግ በምዕመናን ላይ በሚያደርሱት ከፈጣሪ የሚያገኙትን ዋጋ ከፋዩ እርሱ ነውና ለእርሱ እንተወው።

ከዚህ ፈቀቅ ብለን ደግሞ በዚያው በዳላስ ወገኖቻችን መካከል ያለውን ወቅታዊ ሁኔታን ስንቃኝ፤ የመረዳጃው ማህበር በቅርቡ ከመረጣቸው አመራርና ካቀፈው 9 የቦርድ አባላት ውስጥ 6 የሚሆኑት በፈቃዳቸው ከሀላፊነት መልቀቃቸው በሕግ አመለካከት አመራሩ ፈርሷል። ለመረጣቸው ሕዝብ መልሶ ለማስረከብና ሕጋዊ በሆነ ምንገድ ሀላፊነትን ለማስተላለፍ ያልቻሉበት ወይንም ያሰጋቸው መክንያት ምን እንደሆነ እስካሁን በግልጽ የቀረበ ሁኔታን በእጃችን እስካሁን የገባ ስለሌለ ለመተቸት ቢያስቸግረንም፣ ሀላፊነትን ጥሎ መኮብለል ከክህደት እንዳይቆጠርባቸው መላ መፈለጉንና ለዚህ ያበቃቸውን ለመረጣቸው ማሳወቅ የግድ ሆኖ ለሕይወታቸው የሚያሰጋ ሁኔታም ካላቸው ፤ ለሕግ ማሳወቅና አስፈላጊውን ጥበቃ እንዲደረግላቸው የመጠየቅ መብታቸውን እንዲገነዘቡ ገጻችን ታስገነዝባለች።ከዚህ ጋር
በማያያዝ ማንኛውም የድርጅቱ እንቅስቃሴ አብሮ በዚህ ሀገር ህጋዊ አባባል ድስስት ያደርጋል። ባስቸኳይ አጠቃላይ ስብሰባ መጥራት የግድ ነው። እንደምንሰማው ከሆነ ሸሪኮቻቸውን በጣት በመጥራት ያዋቀሩት አመራር ሕጋዊ ስላልሆነ በሕግ ያስጠይቃል።

በእርግጥም በመረዳጃው ማህበር ውስጥና በሥሩ ባቀፋቸው ድርጅቶች ውስጥ ከሕግ ተጻራሪ የሆኑ የተለያዩ ፍሮድ ይሉታል በሀገሩ እንደሚካሄዱ በየጊዜው የሚደርሱን መረጃዎችን ዋቢ በማድረግ ዘግበናል።  ገጿ ባለባት ወገናዊ ሀላፊነት ገሀድ ላለማውጣትና እርስ በእርስ በመተራረም እንዲያልፍ ስትጥር ቆይታ ነበር። አሁን ግን ከማንኛውም ጊዜ በበለጠ መልኩ የሕዝቡን ጥሪትና መብት ብቻ ሳይሆን ሕገወጥ ምግባሩ በከፋ ሁኔታ ቀጥሎ በመታየቱ እንዳመቺነቱ መርጃዎቹን ለመልቀቅ ተገዳለች። ከሚመለከታቸውም የሕግ አስከባሪ ክፍሎችም ጋር ለመተባበርና ጉዳዩ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ እንዲጠራና አጥፊና ተባባሪ ሆነው በሚገኙት ላይም ለሚወሰደው እርምጃ ምንም አይነት ቅሪታን በማንኛውም መንገድ በማንም ዘንድ እንደማትጸርስ በማመን ነው። በተለይም በመረዳጃው ማህበር አማካኝነት በኢትዮጵያ ቀን ዝግጅት ቀደም ባለውና አሁንም በሚሽቀዳደሙበት ትርዒት ከጀርባ ያለው ጉድ የሰፋ ነውና፤ ንጹአን ወገንን እናገልግል ብላችሁ የምትሳተፉ ውድ ወንድሞችና እህቶች ልታጤኑትና ልታስተውሉት የሚገባ ከጀርባ ያለውን ጉድ በቀላሉ የምትገነዘቡት ስለማይሆን ቀደም ሲል የጣጣፍናቸውን መመርመሩና የጎደሉትን የመስመር ነጥቦችን (ዶቶችን) ማገናኘት ብልህነት ብቻ ሳይሆን በሕግ አብሮ ከተጠያቂነትን ያድናል ብላ ገጿ ታሳስባለች።  በአማርኛ “ለብልህ ………ምን አይሉ“ እንደሚሉ።

ሌላው የመረዳጃው አካል ነኝ ባዩና ሀሰተኛው እድር ተብዬው መረዳጃ ማህበሩን የሕገወጥ ምግባር መሸፈኛ ብቻ ሳይሆን ፤ ከሥሩ መሆኑ ቀርቶ ዛሬ እንደሚታየው ከበላይ ተቆጣጣሪ ሆኖ ብዙ ምዝበራና የወንጀል ፋብሪካ ሆኖ ነው ያገኘነው። እራሱን እንዲያጠራና እርምት እንዲያደርግ የተደጋገመ የዚች ገጽ ትችትና ማሳሰቢያ ጥረት ሁሉ ተቀባይ ባለማግኘቱና የተደጋገም ክህደትን ሳይቀርና ኩነናን በሚቆጣጠሩት የወገን ሬዲዮ ስርጭት ሁሉ ሰንዝረውባታል። ይሁንና ዛሬ ባደባባይ የማይክዱትን ወንጀል የመልቀቅ ወቅቱ ስለሆነ በእጃችን ካሉን መርጃዎች አንዱን ብቻ ጀባ እንላችኃለንና ግንዛቤው የናንተ ሲሆን ፣ እንደለመዱት ክህደት የወንጀለኞች ነው። ገቢያቸውን መደበቅ የሚፈልጉና የታክስ ግዴታቸውን ላለሟሟላት ነገር ግን ለጥቅም የመጀመሪያ ለመሆን የሚቸኩሉ ግለሰቦች ግን በጥሬ ገንዘብ ለዚህ እድር አባልነት የከፈሉበትን ደረስኝ እንኳን በመረጃነት የያዙ ስለማይኖሩ ለምዝበራ ያመቹ ናቸው። በቼክ ከከፈሉትም አንዳንዶች ለመረጃ በተባባሪዎቻችን ቢጠየቁም ፈቃደኛ ሆነው እንዳልተገኙ ከዳላስ ምንጮቻችን ብንጋራም፤ መረዳጃውም ሆነ እድሩ የባንክ ሂሳብ ቁጥራቸው የሚገኘው ከባንክ ኦፍ አሜሪካ ብቻ ነው። ወደ ሂሳቡ የሚገቡት ቼኮች ሁሉ ከጀርባቸው የባለ ሂሳቡ የባንክ ሂሳብ ቁጥሩና ስሙ ማህተም ኢንዶርስ ወይንም በእጅ ተሞልቶበት እንደሚገባ የባንክ የተለመደ አሰራር ነው። በእጃችን የገቡት ግን ከዚህ ተጻራሪና በሌላ ባንክ ውስጥ በሕገወጥ መንግድ በሶስተኛ ወገን በጥሬ ገንዘብ የተወሰደ ስርቆትን ያሳያል። ከዚህ በታች ያለውም መረጃ ቀጥታ ከባንክ የተገኘና፤ ጉዳዩ የሚመለከተው ባንኩም የራሱን የውስጥ ምርመራ በማካሄድ ከቻለ በጥሬ ገንዘብ የወሰደውን ማንነቱን እንዲገልጽ ካልሆነም የውስጥ ተባባሪ ካለ አስፈላጊውን እንዲፈጽም፣ ከዚሁ ጋር ተያይዞ ያለውን ማንኛውንም ሪከርድ የኤሊክትሮኒክ መርጃዎችና የሰው ምስሎችንም ሁሉ የጨመረ መርረጃዎችን እንዲያቀርብ ሕጋዊ ጥያቄ ሰሞኑን ደርሶታል የሚል ፍንጭ ለምርመራው ቅርበት ያላቸው ምንጮቻችን ያዳዳቸውን እያካፈልን ጀባ ባልናችሁ በሚቀጥለው መረጃ ላይ የባለቤቱንና የሂሳቡን ቁጥር በማጥቆር ማንነታቸውን ለመደበቅ ግዴታ ስላለብን መሆኑን አስቀድመን ማሳወቅ እንፈልጋለን።

       
በመጀመሪያ መረባረብ መርዳጃ ማህበሩን መልሶ ማቋቋም ሲገባ ለኢትዮጵያ ቀን በዐል ብሎ መሯሯጥ እራሱን የቻለ ጥያቄና ለዝርፊያ ጥድፊያ አስመስሎታል። ከዚህ በላይ የተለጠፈውም ቺክ ይህንንኑ ያስረግጣል።

እርሶስ ምን ይላሉ?

Saturday, August 6, 2011

እንድምን ከረሙ?

የርሶ ብዕር አስተያየት ተሳትፎ ሕብረተሰባችንን ይጠቅማል ያሉትን አይንፈጉን ገንቢነቱ ቦታ ይኖረዋልና! ማሳሰቢያ፡ ይህ ገጽ የተዘጋጀው የተለያዩ የኅብረተሰባችንን ሀሳብ ለመለዋወጫ እንጂ ለሚሰጡት ማንኛውም አስታየቶች በማንኛውም መንገድ ተጠያቂ አይደለም። ጉግል ድርጅትም ኃላፊነት አይወስድም።


እንድምን ከረሙ?

ለተወደዳችሁ የዚህ ገጽ ተከታታዮች፡ እንደምን ሰነበታችሁ? ሁላችንንም በአንድነትና በሰላም ጠብቆ ለዚህ ላደረሰን ለልዑል እግዜአብሔር አሁንም ከሁሉ በላይ ክብርና ምስጋና ይሁንልን። ፀጋ፣ፍቅሩ፣ በረከቱና ጥበቃው አሁንም አይለየን። በመካከላችን ያለውን ልዩነትን ሁሉ አጥፍቶ በመካከላችን መተሳሰብና አንድነትን ይሰጠን ዘንድ ፈቃዱ ይሁንልን። አሜን።

ባለፈው ጥሁፍ እንዳመለከትነው ሁሉ ፤ የሚጣፍ እንዳለን ነበር። እርሱን ለጊዜው በመዝለል በ08/06/2011 በዳላስ ደብረ ምህረት ካቴድራል ደብር ስለተጠራው የአባላት ስብሰባ ከሚካኤል ሠይፍ የተወረወረልንን በማስቀደም ይሆናል። ይህንን በግምባር ቀደም ተወካይ ያደረጉት ልዕል ሰገድ አበሻው የተባለውን ነው። ለስለስ ያለ የሚመስል ነገር ግን ተመራጭ በነበረበት ወቅት ሆነም ከዚያ በኃላ የስውር አመራሩን በቀደሙት ተመራጮ ላይ ጫና ያደረገና እንደለመደው በአሁኖቹም ላይ ሊያደርግ ያሰበውን ስውር አመራር ባለማግኘቱ በትግሬ ነጻ አውጪ ምንደኞች ቡድን በመደባለቅ ከነ ጌታቸው ትርፌ ፣ ከነ ኪዳኔ አለማየሁ፣ ከነ በትሩና ከመሳሰሉት ጋር በመሆን ቢችሉ አመራሩን ለመገልበጥ ካልቻሉ ደግሞ የተጀመረውን የደብሩን የመሻሻልና የእድገት አቅጣጫ መግታት ብለውም መቀልበስ መሆኑንን አስረድቶናል። እነዚህ የትግሬ ነጻ አውጪ ምንደኞች አመራሩ ደብሩን ለውጪው ሲኖዶስ ሊሰጥብን ነው እያሉ በሬ ወለደ እያወሩ መሆኑንና ቅስቀሳቸው ምናልባት ኮረም ያስሞላልናል በማለት ለሁከት የተነሱ መሆናቸውን ነው። በዚህ ስብሰባም አብዛኛው አባል እንደማይገኝና እንዳለፈው ሁሉ እንደሚበተን ከወዲሁ ግምት አምጥቷል። ማን ነው በደብሩ ውስጥ ከነዚህ ነገረኞች ጋር ተቀምጦ ስብሰባ የሚያደርግ። ሁሌም እነርሱ አመራሩን ካልያዙና እንደፈለጉት ካላደርጉ ሌላው እንደማያውቅና መጥፎ አድርገው መቀባት ምግባራቸው ነው። በነእርሱ መሪነትና አማካሪነት የመጣውን ውድቀት ባለፉት ጥቂት አመታት የሁሉም ግንዛቤ ነው። በተለይ ቆራቢ ነኝ እየተባለ በፀሎት እንደመጠንከር ፊት አውራሪ ሆኖ ሁከትን መቀስቀስ ስይጣናዊ ምግባር መሆኑንን መቼ ይሆን የሚረዱት በማለት ደምድሞልናል።

ገጻችን ከታዘበችው ውስጥም በኢትዮጵያ ካለው ሲኖዶስ ስር ካሉት ጳጳሳትና ከህን ደብሩ ደጋግሞ ጋብዞ በኛ ሥር ካልሆናችሁ ምንም አይነት ግልጋሎት አንሰጥም በማለት አሻፈረኝ ያለው ወገን ሂዱና አስተምሩ ሲል ኢየሱስ ለግልጋሎታችሁ ካሳ ከምትሰጡት ተቀበሉ የሚል በመጽሀፍ አላየንም። አንድ አይነት እምነት ያለውን ወገናቸውን አናገለግል ያሉትና ፖለቲከኛ የሆነ አቋም የወሰደ ሲኖዶስ ያስፈልጋልን? የሚለውን ጥያቄ ለአንባቢያን በመተው፤ እኛ እራሳችንን በዋቢነት አድርገን የምንሰጠው ነጥብ ቢኖር የተሰደደው ወገናችን ለከፈለው ሁሉ እሰከዛሬ ድረስ ሲኖዶሱም ሆነ ቤተ ክህነት እንኳን ሕይወታቸው ላለፉት ቀርቶ በሕወት ላለነውም ዝምታን በመምረጥ የወሰደው አቋም ከክርስትና መንገድ የወጣ ነው። ቤተክርስትያን ስንከፍትም እንኳን ሊባርኩ ወይንም ካህን ሊሰጡ አንድ ጧፍ ጀባ ያላሉ ዛሬ ግን በግልፅና በስውር ለዘረፋና ለቅሚያ የሚያደርጉት የዶላር ሩጫ ነው። በሀገር ውስጥ ያሉትንም እያደኸዩና እንዲዘጉ እያደረጉ የሚገኙ፤ ከእምነቱ ይልቅ ለፓለቲካ ያደሩ ለመሆናቸው በተግባር እያሳዩን ነው። ሌላው ያሳደጉት ተኩላቸው ደግሞ ማህበረ ቅዱሳን / ማቅ የሚሉት ከልትም ካጀማመሩ የሀሰት ካባ ለብሶ ቤተክህነቱን ሲያተራምስ፤ ዛሬ መሪያቸው በግልጽ እንዳስቀመጠው “አባሎቻቸው የኢሀዴግ አባላት መሆናቸውን“ ነው። ከላይ መሪያቸው የትግሬ ነጻ አውጪ ማለት ነው።

በኛ አስተሳሰብ አባላቱ የፈለገውን ሲኖዶስ የመምረጥም ሆነ ገለልተኛ የመሆን መብቱን እንጠብቃለን። ነገር ግን ለእምነቱ ሲባልና ለተተኪው የኢትዮጵያ ተወላጅ እንዲሁም እምነቱን ላልያዙ ለሌላው ወገኖች የሚጠቅሙና ብቃት ያላቸውን ካህናትን ያቀፈው በሰሜን አሜሪካ የሚገኘው ሲኖዶስ ነው። በተለያዩ ደብሮች ካየነው ልምድ በቂ እምነትና ስረዐትን የሚከተሉ ተከታዮችን እያሰፉ ያሉትን ፣ ለሚሰጡትም አገልግሎት ንጹህና ምንም አይነት ስውር ተለጣፊ ምክንያትን የሌላቸው ሆነው አግኝተናቸዋል። በሀገር ቤትም ሆነ በውጪ ከፍተኛ ትምህርት ያላቸው እነዚህ አገልጋዮች፤ ሰሜን አሜሪካን እንደሀገራችን ለምናየው ሁሉ እጅግ በጣም ተስማሚዎች መሆናቸውን ነው። በየትኛውም ጊዜ ለአገልግሎት ቢጠየቁ በቅርብ ሊገኙ የሚችሉ የተትረፈረፈ የሰው ሀይል ያላቸ ሆነው ነው የሚታዩት። ስለዚህ የትኛውንም ሲኖዶስ መከተል ወይንም ገለልተኝ መሆን መንግሥቱን አያወርሰንም፣ ነገር ግን እምነትና ምግባሩን መጠበቅ ነው ።  በመጀመሪያ የውስጥ የውጪ በማለት ለመከፋፈል ምክንያትን ከማዳነቅነት፤ ለተለያዩት አባቶች አንድነትና መግባባትን አጥብቀን መጸለይን ማዘውተርና የሀገር ቤቱም ሆነ የውጪው ተከታይ እንደሚመቸው እያመለከ እንጂ ለማንንም ተጽእኖ ማደር የለበትም በማለት ገጿ ታስገነዝባለች።

ይህን ጥሁፍ ከመለጠፋችን በፊት ዘግይቶ በደረሰን ዘገባ መሰረት፤ ሚስትና ባል በመሆን ላስጠሩት የአባላት ስብሰባ በቅዱስ ሚካኤል ደብር ዛሬም ኮረም ባለሞምላቱ መበተኑን ነበር። ነገር ግን እንወያይ በማለት ሰይፉ ይገዙ የተባለውን እንዲመራቸው አድርገው የመጨረሻ እስትንፋሳቸውን እየተነፈሱ መሆናቸውን ነው። ሰይፉ የተባለውም ግለሰብ በሁለት ቢላዋ ለመብላት እየተንቀሳቀሰ እንዳለ አስምሮበታል። በሌላ በኩል ደግሞ ኢዮኤል (ክፈተው) ነጋ የተባለውና ላለፉት ችግሮች መሪ ብቻ ሳይሆን አሁንም በከሳሽነት ከስብሰባ የተባረረው ሀይሉ (ቀዩ ሰይጣን) እጅጉና የትግሬ ነጻ አውጪ ቅጥረኛ ከሆኑት ጋር ደስታ በተባለው ምግቤት ሲዶልትና መመሪያ ሲቀበል ቆይቶ ወደስብሰባው ያመራው። እንግዲህ ይህቺ ጥለናት ለምንሄድ አለም ይህን ያህል በዕምነት ስፍራ መባላትና አፍራሽ መሆንን ከፈጣሪ እስኪያገኙትና እርሱ እስኪመክራቸው መታገሱ ሳያሻ አይቀርም። የታደለማ  ነገር ሳይሆን በፍልሰታ ዋዜማ ለሱባኤ ይዘጋጃል እንጂ የቤተክርስትያንን ሰላም ለማወክ አይሰበሰብም። ቆራቢ ነን የሚሉትስ ምን ይመልሱ?

ከዚህ ደግሞ ፈቀቅ ስንል ወደ መረዳጃ ማህበራችሁ ትንሽ የምንለው አለን። አንዳንድ ጊዜ ቃላትን ባለማወቅ ወይንም ከመሀል አንድን ቃላት ብቻ ወስዶ የራስን ትርጓሜን መስጠት አላግባብ እጅጉን ጎጂ ነው። ከጥቂት ሳምንት በፊት የዳላስ የኢትዮጵያ መረዳጃ ማህበር ሬዲዮ ስርጭት ካለንበት ሆነን በኢንተርኔት ስንከታታተል አቅራቢዎቹ ከሪዲዮ ጣቢያው ሀላፊ ጋር ያደርጉትን ስምተናል። ዲ መጋዘን የተባለውንም ቃኝተነዋል። የተጣፈው ስለሬዲዮ ጣቢያው ምግባር ሲሆን ከሚሸፍናቸው የህብረተሰብ ክፍሎቹ በማነጻፀር ዝቅ ብሎና አናሳ ከሆኑትና በከተማው ውስጥ በአስተዋጾ ደርጃ እውቅና ያላስመዘገቡትንም በምሳሌ አድርጎ ወገኖቻችንን ጠቀሰ እንጂ ሌላ አይደለም።

2ኛ/ በቅርቡ መረዳጃ ማህበሩ በጠራው ስብሰባ ላይ ይኽው ግለሰብ አንዲቷ እህት ተመራጭ ካሉት አረፍተ ነገር ውስጥ በእንግሊዘኛ ካሉት ውስጥ ብቻ አንድን ቃል በመውሰድ ሕዝቡን እንዲ ብላ ሰደበች ብሎ ያለውን በዲኤፍ ደብልዩ አማርኛ ገፅ በማንበብ ላደረግነው መከታታተል አሁንም ዳግም ስህተት አግኝተንበታል። ሴት እህታችን ያሉት “እኔ የምሰራውን የማላውቅ ደደብ መሰልኩህን “ የሚል ጥያቄን ያዘለ መልስን እንደነበር ነው። በዚሁም ወቅት ግለሰቡ በእታችን ላይ ያሳየው ሁለንተናዊ ባሕርይ ወደ አካል ግጭት የሚያስገባ እንደነበር ከስፍራው የደረሰን ዘገባ ያስረዳል።

እንግዲህ ዘውገ (ዝንጀሮ) በስውር የትግሬ ነጻ አውጪ ቅጥረኛና የሬዲዮ ተስፈኛ በነጻ ማገልገል ሲገባው፣ እርሱ ግን ለጥቅም ያደረ በመሆኑ በማስታወቂያ ስም ለሚገኘው ገቢ እንጂየነጻ አገልጋይ አለመሆኑን። መረዳጃው ግን እያስተባበር የአየር ሰዐቱን የሚሸፍንለት፣ በቂ እውቀትና ስልጠና የሌለው ነው። ለዚህም ነው እንዲገባው ሙያ አድርጎ እንዲይዘው ከፈለገ የእንግሊዝ ቋንቋን 101 መውሰድና በሙያው አንዳንድ የማሻሻያ እውቀቶችን ቢገበይ የሚሻል ። በሬዲዮም እየወጣ መዋሸቱን ያቁም።

ሌላው ለረዥም ጊዜ ሲካድ የቆየው የመረዳጃ ማህበር ተዘግቶ የነበረበትን በዚህ ስብሰባ ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ ኮለኔል ሊበን የተባለው የቀድሞ አመራር አመነ። የጴንጤ እምነት ተከታይ ነኝ የሚልና ሲክድ አመታትን ያስቆጠርው ሊበን የዕምነቱን ተከታዮችን አንገት አስደፊና አሳፋሪ ሆኖ ለትዝብት በቅቷል። ይህንንም ሊያምን የተገደደው በኛ ገጽ ቀደም ብለን ያወጣነውን ማስርጃና በስብሰባውም ላይ ወ/ሮ የሐረር (የኢትዮጵያ) ወርቅ ጋሻው የተባሉትና የከተማችሁ የሰብዐዊ መብት ተሟጋችና ቀስቃሽ ተገኝተው ለአመራሩ ካስረከቧቸው መርጃዎች አባሪ ሆኖ በመቅረቡ ነበር። እንግዲህ በዚህ ወቅት መረዳጃው ሕጋዊ ሰውነቱን አብክነውና ጊዜው ሲደርስ እራሳቸው ስሙን ወስደው በስማቸው ፈቃድ በማውጣት ለማካሄድና ወገኖቻችንን ለመዝረፍ ነበር። በተለይም ከትግሬ ነጻ አውጪ ጋር ባላቸው ንኪኪ ለጥቅም ብለው አሳልፈው ይሸጡትም ነበር። ሌላው የመረዳጃ ማህበሩ በስሩ ያለውንም የሬዲዮ አየር ሰአትም ለነዝንጀሮ በግላቸው ሊሰጣቸው ሲል ደርሰው ያስጣሉት እኒህ ወ/ሮ መሆናቸው ፀሀይ የሞቀው ሀቅ ነው። ነገር ግን አንድም ወቅት የራዲዮኑን ስርጭት አስቁመዋል የሚል ምንም መረጃ እስከዛሬ የለም። መረዳጃውንም ከሳለች የተባለውም አፈታሪክ ሆኗል።  ግለሰቧ ሀቀኛና እውነትን ዳሳሽ በመሆናቸውና እራሳቸውን ለጥቅም ያላስገዙ በመሆናቸው በግለስቧ ላይ ዛሪም መተናፈሻ ያጡ ሕመምተኞች እየተወራጩ ይታያሉ። በተለይም መረዳጃው ፈርሶ እያለ በሕግ ወጥ መንገድ ያካሄዱት ውሳኔና ምግባር ብሎም በሌለ ድርጅት ስም ገንዘብ መሰብሰብ ከሕግ የተጻረረ ነው። ያስጠይቃልም።

ምሳሌ፡ ባለፈው ፍልብ ፍሎብ ያልነውና ቃል የገባውንም ገንዘብ ለመረዳጃው ያላስገባ ነገር ግን አንዴ ለቀኩኝ ሌላ ጊዜ አማልዱኝ አስታርቁኝ ባይና እንደሚጠፈጥፈው ቂጣ የሚገለባበጠው ፣ አሁንም በቃሉ የማይረጋና የአመራሩ ሊቀመንበር የሆነው ብርሀን (ማክ) መኮንን ወይንም ፍልብ ፍሎብ በግለሰቧ ላይ ዛሪም መሰሪ ምግባርን በመረዳጃው ማህበር ውስጥ እየሰራ ለመሆኑ የሚደርሱን ዘገባዎች ያትታሉ። ይህ ግለሰብ መረዳጃ ማህበር አመራር እውቀት የሌለውና ለመማርም ያልፈቀደ ዝግ ግለሰብ ብቻ ሳይሆን አደገኛ መርዝ ነው። ሊቀ መንበር ለቀረቡት ሀሳቦች ግራ ቀኙን በስርዐት እንዲካሄድ አድርጎ ለድምጽ ያቀርባል። እኩል ድምጽ ቤመጣ የመጨረሻ ድምጽ ሰጪ በመሆን ለውሳኔ ያበቃል። ውሳኔው እንዲተገበር ለፈጻሚ ወገን መድረሱን ያረጋግጣል። ከዚህ ውጬ ወጥቶ አሉባልታን ይዞ መርጃን ሳይጨብጡ ሊሎች የእርሱን አመለካከት እንዲደግፉለት ተጽእኖ ማድረግ ተገቢ አይደለምና ችሎታ ባለው መተካት አለበት። ባጠቃላይ ፍልብ ፍሎብ እየሰራ ያለው ከትግሬ ነጻ አውጪ ተቀጣሪዎች የታዘዘውን እንጂ ለዲኤፍ ደብልዩ ወገኖቻችን የሚበጅ አይደለም። ከዚህ በፊትም ወገኖቻችንን ለመከፋፈል የሞከረው ሲከሽፍበት መልሱኝ ምን አመጣው።
በመሪነቱ ብቃት እንደሌውና ከጎዳና መውጣቱን ለምን አደረገው?    

ባለፈው ጠቅላላ ስብሰባም የትግሬ ነጻ አውጪ አድርባይ ብቻ ነበር ሲደመጥ የነበረ። ከሁሉም በላይ የእያንዳንዱን ግለሰብ መረጃና ማንነትን የያዘው ኤሌክትሮኒክስ መረጃን አላስረክብም ብሎ የያዘውና የመረዳጃ ማህበሩን ድህረ ገጽ ያለአግባብ እየጠለፈ ያለው ዳንኤል የተባለው ግለሰብ ሕገወጥ ምግባር ነው። ይህ ግለሰብ የያዘው መረጃ ለ3ኛ ወገን አስተላልፎ ሰጥቶት ይሆን? ወይንስ ወደፊት ያደርገው? በተለይም ለትግራይ ነጻ አውጪ! እንግዲህ በመረዳጃውም ሆነ በእድሩ እስከ መለያ ቁጥራችሁ የሞላችሁት ቅጽ ካለ ከአሁኑ እርምጃ መውሰድ የናንተው ሀላፊነት ነው።

የትግራይ ነጻ አውጪ ወኪል የሆኑት በዚህ ስብሰባ ላይ ከሚሰጣቸው መድረክ አልፈው እስከ አመራሩ መድረክ ድረስ በመዝለቅ ሥርዐት አልበኝነታቸውን ያሳዩበት ስብሰባ ነበር። ኣንግዲህ እነዚህ ናቸው በዕምነት ማዕከልም ሆነ በሶሻሉም የሕብረተሰቡ ጠንቅና መርዘኛ። ለዛሬ በአብነት ከዚህ በታች ያለው ምስል በደርግ ውታደርነት በሩሲያ ተማረ የሚባለውና በኃላም ለትግሪ ነጻ አውጪ አገልጋይ፤ ለጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ሚስት የሽርክና ባለቤትነት የመድህን ድርጅት ያለሕጋዊ ፈቃድ በዳላስ የሚሰራና ያለሕዝብ ምርጫ የመረዳጃ ማህበር አመራር ይዞ የነበር፤ የቅዱስ ሚካኤልን ደብር ለሚከሱ አጽራረ ቤተክርስትያን ኮሚቴ አቋቁሞ የሚመራና ደብሩን ለአዲስ አበባው ጌቶቹ ለመስጠት የሚንቀሳቀስ ግለሰብ ተፈራወርቅ የተባለው ከጉባኤው መሪዎች መድረክ ድረስ በመሄድ ሲፎክር የሚያሳየውን ነው።



ለዛሬው በዚህ እየቋጨን መልካም የፍልሰታ ጊዜን እየተመኘን በቸር መልሶ ያገናኘን።

እርሶስ ምን ይላሉ?