Monday, May 30, 2011

ይድረስ ለአቶ አብርሃ በላይ/ኢትዮሚዲያ ገጽ

የርሶ ብዕር አስተያየት ተሳትፎ ሕብረተሰባችንን ይጠቅማል ያሉትን አይንፈጉን ገንቢነቱ ቦታ ይኖረዋልና!

ማሳሰቢያ፡ ይህ ገጽ የተዘጋጀው የተለያዩ የኅብረተሰባችንን ሀሳብ ለመለዋወጫ እንጂ ለሚሰጡት ማንኛውም አስታየቶች በማንኛውም መንገድ ተጠያቂ አይደለም። ጉግል ድርጅትም ኃላፊነት አይወስድም። ኃላፊነቱ በሙሉ የአስታየት ሰጪው ብቻ ነው።


ይድረስ ለአቶ አብርሃ በላይ/ኢትዮሚዲያ ገጽ

የተወደዳችሁ የገጻችን ታዳሚዎች እንኳን በሰላም ለሰማዕታት (ሜሞርያል) ቀን ሁላችንም ጠብቆ ለዚህ ላደረሰ ለልዑል እግዚሀብሔር ክብር ምስጋና ይሁን። በዚህ ሰማዕታት ቀን መጠለያ ብቻ ሳይሆን መመኪያና መኩሪያችን ፣ እኩልነትና ነጻነት የሞላበት ሀገራችን እንዲሆን በራቸውን ከፍተው በሙሉ ልብ ተቀብለው እንድንቀላቀላቸው ፈቃድ ላደረጉልንና ይኸው እንዲተገበር ውድ ሕይወታቸውን የከፈሉትና በመክፈል ላይ ላሉት የአሜሪካን የሲቭልና የጦር ኃይል አባላትን በመዘከር የምናስታውስበትና የምናመሰግንበት ዕለት በመሆኑ ይህንን ሀገር እግዚሀብሄር ይጠብቅልን። የትውልድ ሀገራችንን ኢትዮጵያንና ሕዝቧንም ያስብልን።

ሰሞኑን ከሀገር ወደ ሀገር በመዘዋወር በከፍተኛ ትምህርት እየተመረቁ ለሚገኙት ወጣቶች ልጆቻችንና የወዳጅና የዘመዶቻችንን ልጆች ተጠምደን ብንሰነብትም ለዚህ መሳካት የወጣቶቹ፣ የቤተሰቦቻቸውና በተቋማቱ ላሉት ሁሉ ላበረከቱት መሳካት፤ ሁሉንም እንኳን ደስ አላችሁ ስንል፤ ተተኪ በመሆን ከ2ኛ ደረጃ ለወጡትና ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋም ለሚገቡት፣ ከመጀመሪያ ዲግሪ አልፈው ወደ ድህረ ምረቃም ሆነ ለፒ ኤች ትምህርታቸው ለሚያቀኑት ሁሉ መልካም ምኞታችንን እየገለጽን ልዑል እግዚሀብሔር ያሳካላችሁ እንላለን።

የዳላስ ቅዱስ ሚካኤል ደብር አጠቃላይ የአባላት ስብሰባ አስፈላጊው ቁጥር ባለሞሙላቱ ሳይኬድ ቀርቶ ለ2 ሳምንት ለ05/28/2011 መቀጥሩን ሰምተናል። የ2ኛውም ጥሪ ለምን ምልዐተ ጉባኤው እንዳልሞላ ከሚካኤል ሠይፍ የደረሰን የተገኙት ወደ 40 ቀጥር ያላቸው ደብሩን አዋኪያን ስለሆኑ ከነእርሱ ጋር መቀመጥን አለማሻታቸውን ሲሆን ሁሉንም ለሚካኤል ፈቃድ መተዋቸውን ነበር። ታላቁ የቅዱስ ሚካኤልና የተዳበሉት ታቦቶችን ጨምሮ የሚሰሩትን ያልተገነዘቡ እነዚህ ጥቂት ግለሰቦችም ዛሬም ማስታወሉን እንዲሰጣቸውና ከታቦት ጋር የሚደርጉት ግጭት እንጂ ከግለሰብ እንዳልሆነ ሊረዱት ይገባል። የነዚሁ ቡድን ገፅ የሆነው ከስብሰባ ስለታገዱት አባሪዎቻቸውና ከሳሾች ቢያለቅስም ቦርዱ የተመረጠበትንና የሚተዳደርበትን መተዳደሪያ ደንብ አክባሪነቱን በማረጋገጥ ከሳሾቹን ለየ ፣ በሕጉ መሰረት 2ኛ ስብሰባውንም ጠራ። ሌላው ሥርዐቱን ለመናድ ካልሆነ በስተቀር ከንቱ ጩኸት እንለዋለን። ሌላው የኛን ገጽ ለማፈን በሚደረገው የሕግ ጎዳና ከጠንሳሽነቱ ጀምሮ አባሪ መሆኑንም ከለጠፈው ስንረዳ የመጻፍ መብታችንን ከሚያደናቅፉ በመሰለፉ በደብሩ ውስጥ መብት ተነካ የሚለውን የሀሰት ለቅሶውን አጋለጠ እንለዋለን። በሌላ በኩል እኛ ተከሰስን ብለን ለጥፈን አናውቅም ነገር ግን በሕግ ልሳናችንን ለመግታት በትግሬ ነጻ አውጪ ቅጥረኛና ምናምንቴዎች በተለያየ መልኩ እየተፈተንን ቢሆንም የመናገርና የመጻፍ መብታችንን መቀማት እንደማይቻል የሀገራችን ኮንስትቲይሽን በግልጽ አስቀምጦታል።

በዚህ 2 የደብሩ ስብሰባዎች መካከል የጠ/ሚ መለስ አምቼ ከቤ/ክ ከ60 በላይ የሚሆኑ ወንበሮችን ተከራይቶ ሲያጓጉዝ በየመንገዱ ሲያንጠባጥበው የታዘቡ የደብሩ አባላትም መኖራቸውን ሲደርሰን ፣ ወንበሩን የተከራዩት ለምን እንደሆነና የት ቦታ እንዳጓጓዙት በመስማታችን አዝነናል። ቦርዱም የኛን የተጋራ ይመስል ከዚህ በኃላ ማንም ይሁን ምን አሁን ለመከራየት ከተመዘገቡት ውጭ ወደፊት ላለማከራየት ወስኗል የሚል ከሚካኤል ሠይፍ አብሮ የደረሰን መሆኑንን ስንገልጽ ሰንከፎው እስኪወልቅ የመጣውን መቀበል የግድ መሆኑን ከዚሁ መገንዘብ ያሻል። ሰሞኑን በፍቅረማሪያም የተደረገው ቅስቀሳ አልመስራቱን ቀጥሎም በቀድሞው ሊቀመንበር ኢዮኤል የአዋኪያን ቡድን አባል እየተካሄደ ያለውን የፊርማ ስብሰባም ስንሰማ መቼ ነው እርሱ በሕዝብ ድምፅ ያመነው? በርሱ ጊዜ ስንት አይነት የምዕመናን ቅሬታ ሲጎርፍ ከምንጣፍ ስር ሲቀርብ አልነበረምን? የሕዝብንስ አደራ በግል ጥቅሙ መነካት ነው ወይንም ለምን በቁልፍ ሰበብ?

ለዛሬው ጥሁፋችን መንደርደሪያ የሆነን በአቶ አብርሃ በላይ የኢትዮ ሚዲያ ድህረ ገጽ በቅርቡ ስለዳላስ ነዋሪ ግለሰቦች ያስነበበንን በእማኝነት አድርገን ለምን እኛ ሀቅ ከጨበጥነውና በአጋጣሚዎች ሁሉ ካስነበብነው ጭብጥ የወጣ ዘገባ ለምንና እንዴት የመሰለውን ለማስረገጥና ወገኖቻችን የራሳቸውን ግንዛቤ ይስሉ ዘንድ ነው። አቶ አብርሃን በአይነ ስጋ ባናውቀውም የትግሬ ነፃ አውጪ ጎራ የነበረና ሀገር አብሮ ያስቆራረጠ ለመሆኑ የአደባባይ ሚስጥር ነው። ከነእርሱም ተፋታው ብሎ በአሜሪካ ተቀምጦ በከፈተው ድህረ ገጽ ጥሩና ድንቅዬ ሥራዎቹን አቅርቦልናል ፣ ለዚህም እናመሰግነዋለን። በሌላ በኩል ደግሞ ከግል ጥቅም ጋር በተሳሰረ የሕዝብንና የሀገር አንድነት በሚጻረር ስነ ባሕሪን ተላብሶ እያደማ ይንቀሳቀሳል። ለዚህም እኩይ ምግባር የተሰለፉለትንም ባገኘው አጋጣሚ ይዘክራል። የሚቋቋሙትም ጥሁፎች ሲደርሱትም ያፍናል። ሰሞኑንም 2 የዳላስ ነዋሪ ስለሆኑ ግለሰቦች የለጠፈውንና ቀብቶ የካናቸውን ገጻችን ከአለመስማማት አልፋ በጽኑ ትኮንን ዘንድ አብቅቷታል። ተካሄደ የተባለው የኢሳት መዋጮ 25 ሺህ ዶላር አስገባን ያሉት ግለስቦች ከዚህ በፊት ለዳላስ የኢትዮጵያ መርዳጃ ማህበር እጅግ ብዙ ሺህ የሆነ ዶላር አስገኘን ብለው በሪዲዮን የደሰኮሩትን ያስታውሰናል። እስከ ዛሬ ሳንቲም አልታየም። ወራዳና ዋሾ ራከርድ ያላቸው ብለን ብቻ አናልፈውም!

1. በትሩ ገብረእግዚሐብሄር ማለት ቀደም ሲል ገፃችን ከቴኔሲ ፍርድ ቤት በእርሱና በባለቤቱ ስም የተሰራውን ማጭበርበር አስመልክቶ ሁላችንንም የኢትዮጵያ ተወላጆች አንገት ያስደፋውን ምግባር መለጠፏን ብቻ ሳይሆን የተለያየ የግብረሰናይ ድርጅት ስም እየመሰረተ መተዳደሪያው ያደረገና በሰፈረበት ሀገርና ከተማ ሁሉ ምግባሩ አስነዋሪ ብቻ የማይባል ሕግን የተላለፈ ጭምር ነው። ሰሞኑን ሕይወታቸው ያለፈውና የበትሩ ሰለባ ከሆኑት አንዷን ግለሰብ ማንሳትም ተገቢ ነው። ስማቸው ወ/ሮ አልማዝ የተባሉ በአዲስ አበባ የባናቱ ምግብ ቤት ባለቤትና ልጆቻቸውን ብቻቸውን የሚያሳድጉትን ሴት ለንግድ ማካሄጃ ብሎ ተማጽኖ አንድና ብቸኛ መኖሪያቸውን በማስያዝ ትልቅ ገንዘብ በመበደር ኢትዮጵያን ለቆ ወጣ። ከዚያም ወደ ሌላ አፍሪካ ሀገር ተመሳሳይ ድርጊት ፈጽሟልም ይባላል መረጃው ባይደርሰንም። ነገር ግን የወ/ሮ አልማዝ በዚህ ውስልትና በተፈጸመባቸውና በደረሰባቸው ኪሳራ ምክንያት የደረሰባቸው የጤና መታወክ ለብዙ አመታት ሲሰቃዩ ቆይተውና ልጆቻቸውና የልጅ ልጆቻቸውን ጨምሮ የገፈቱ ቀማሽ አድርጓቸዋል። እንግዲህ አለም አቀፍ አጭበርባሪና ለወገኖቹም ርህራሄ የሌለው ለግል ጥቅሙ ብቻ የቆመ ለትግ ሬ ነጻ አውጪ የስውር አርበኛቸው በዳላስም በ2 ቤላዋ የሚበላውን መኮፈስ ለአብርሃ ማንነት ጥያቄ ምልክት ነው።

2. ስለ ዘውገ ቃኘውም ቢሆን ብዙ ብለናል። በቅርቡም ስለ አባይ ግድብ ከትግሪ ነጻ አውጪ ተልከው ዳላስ ከገቡት ቡድን ጋር አብሮ የከረመና እራት የተቋደሰ መሆኑንን በዳላስ ነዋሪ የተረጋገጠ ነው። ከሰሜን አሜሪካ የኢትዮጵያ እስፖርት ተቋምም በየአመቱ የሚደረግለት የነጻ ጥቅም በመቅረቱ ወያኔ ያዘው ብሎ ስም ማጥፈት ዘመቻና እንዲፈርስ ከሚያውኩት ጋር መዳበሉ ለሁላችንም ግልጽ ነው። እርሱና የትግራይ ተውላጅ የሆነው የሬዲዮን ባልደረባው ስጦታው የተባለው በዳላስ የኮሚኒቲ ሬዲዮ ለትግሬ ነጻ አውጪ መሳሪያነታቸው እሙን ነው። ያለሙያ ብቃት የቆሙና ስደተኛውን መጠቀሚያ ያደረጉ መሆናቸውን እየታወቀ ያለ ነው። ከዚህ በታች ያለው እሮሮ ለአብርሃና ብጤዎቹ ድህረገጽ ተልኮ ያፈኑትን እነሆ አቅርበነዋል።

     





እንግዲህ ወደ ኃላ ያሉትን የለጠፍናቸውንም በመገንዘብ አቶ አብርሃ እርሶስ ምን ይላሉ? የሚለውን የተለመደውን ጥያቄያችንን እየተውን አንባቢያን በጥንድና በቡድን የሚተገበረውንና ወገኖች ላይ የሚካሄደውን ግምጋሜ ላይ አድርሶ ፍሬ ያስጨብጥ ዘንድ ያለንን ወርውረናል።

ለአንደኛ አመታችን ለደረሱን ግምገማዎች ተሳታፊዎቻችንን ሁሉ ከልብ እናመሰግናለን። ላበረታታችሁንና ለደገፋችሁን ፣ ያላችሁን መረጃዎች ላልነፈጋችሁን ፣ ሂስ ለሰነዘራችሁብን ና ለተቃወማችሁን ሁሉ ምስጋናችን የላቀ ነው። ወቀሳችንና ትችታችንን ተቀብላችሁ ለተመለሳችሁ አክብሮታችንን ስንገልጽ ላልተከፈተላቸውና በጨለማ ላሉት ወይንም ትቅማቸው የቀረባቸውና እልህ ይዞ ያለቀቃቸው፣ ስማችን ተነካ ብለው አምረረው እኛን ከመተንኮል ላላሰለሱት ጭምርና በሀይማኖትም ግዝት የጣሉብን ጨምሮ ለሁላችንም የምናስተውልበትን ህሊና ሰጥቶ መተቻቸትንና መነቃቀፍን ለመሻሻልና ለበጎ ምግባር አድርገን በመውሰድ በቅን ጎኑ በማየት የቀረ ሕይወታችንን ለጋራ ደህንነትና መደጋገፍ በማዋል በመካከላችን የሚሽሎከለኩትን አዋኪያን የራሳችንን ወገኖችን በራሳችን በመተናነጽ ለተተኪዎቻችን የተሻለ ለመከወን ልዑል እግዚሐብሄር መንፈሳችንን ያንጽልን።
አሜን።

እርሶስ ምን ይላሉ?      

Thursday, May 12, 2011

የርሶ ብዕር አስተያየት ተሳትፎ ሕብረተሰባችንን ይጠቅማል ያሉትን አይንፈጉን ገንቢነቱ ቦታ ይኖረዋልና!

ማሳሰቢያ፡ ይህ ገጽ የተዘጋጀው የተለያዩ የኅብረተሰባችንን ሀሳብ ለመለዋወጫ እንጂ ለሚሰጡት ማንኛውም አስታየቶች በማንኛውም መንገድ ተጠያቂ አይደለም። ጉግል ድርጅትም ኃላፊነት አይወስድም። ኃላፊነቱ በሙሉ የአስታየት ሰጪው ብቻ ነው።


የተወደዳችሁ የገጻችን ተከታታዮች እንደምን ከርማችኃል? ፈቃዱ ሆኖ ዳግም እንድንገናኝ ለወደደ ለእርሱ በቅዱስ ስሙ በእግዚሀብሔር ቸርነት ነውና ስሙ የተወደደ፣ የተከበረና የተመሰገነ ይሁንልን። ያለእርሱ ፈቃድ ምንም ምን ሊሆን አይችልምና ዛሬ ወደፊትም ሆነ እስከዘላለሙ ለእርሱ ክብርና ምስጋና ይሁንልን! አሜን።

የፊታችን ቀዳሚት የዳላሱ ቅዱስ ሚካኤል ደብር በ2010 ላይ ማቅረብ የነበረበትን የ2009 አመታዊ ዘገባ በአባላት ስብሰባ ላይ ያቀርባል ተብሎ ይጠበቃል። አንዳንድ ከአጽራረ ቤተክርስትያን የወገኑ ጥቂት ግለስቦች የ2010 አመታዊ ዘገባ እንጂ የ09 አመትን እንደማይፈልጉ ምልክቶች ቢኖሩም፤ በቅደም ተከተል መሄድ ያለበትና ለጣት ለሚቆጠር ግለስቦች መስማት ብቻ የሚፈልጉበት አካሄድ እንደሌለ ሊታወቅ ይገባል። የ09 ዘገባ ኮረም ባልሞምላት ምክንያት ሲተላለፍ ቢዘገይም በተለይ የቀደመው የወጪ ሂሳብ መርማሪ ቀደም ብለው ከቀጠሩት ግለሰቦች ትእዛዝ ባለመውጣትና ገለልተኛ ዘገባ ማቅረብ ባለመቻሉ ፣ ሰራ የተባለውንና በእጁ ያለውንም ዘገባ ለማቅረብ ፈቃደኛ ባለመሆኑ፤ በመጨረሻው የአስተዳደር ቦርድ አዲስ የውጪ ገለልተኛ የሆነ ሂሳብ መርማሪ አወዳድሮ በመኮናተር የተሰራ ዘገባ መሆኑን የሚካኤል ሠይፍ ተወካይ ገልጾልናል። የ2010 የሂሳብ ምርመራን በተመለከተ በቅርቡ ተጠናቆ እንዳለቀ ወደፊት እንደሚገለጽ ለመረዳት ችለናል። ከ2011 ጀምሮ አዲስ የገባውና በሥራ ላይ የሚገኘው ሶፍትዌር ከዚህ በፊት የነበረውና ለቁጥጥር የማይመቸውን መዝገብ አያያዝን በማስተካከል አሎታን ያጠፋል በሚል መልክ አያይዞ አስጨብጦናል።

ይህ አመታዊ ስብሰባ በመከባበር ፣ በመተሳሰብና ሙሉ ክርስትያናዊ ስነ-ምግባር የሚዘከርበት እንዲሁም በቤተክርስትያን ቅጥር ግቢ የሚከወን በመሆኑ ስፍራውንም ጭምር ሊከበር የሚገባው ነው። በሌላ በኩል በቀደመው ጥሁፍ ላይ ካሕኑን አንስተን በተዘገበው ላይ የቀረበልንን እንጂ ፈጥረን እንዳልሆነ ታውቆ፤ በሰንበቱ ትምህርታቸው ላይ ያቀረቡት፤ መልዕክቱ ደርሶናል። እኛ ብቻ ሳንሆን የሚያገለግሉበት ደብር አብዛኛው ምዕመን ከኛ ጋር የሚስማማው ፈጣሪ በሰጦት ክህነት ብቻ ሳይሆን ባካበቱት ዕውቀትና የትምህርት አሰጣጦ ጭምር የምነወድዶና የምናከብርዎ መሆናችንና ባለን ፍቅርና አክብሮት ስለምንሳሳሎት ከአዋኪያን እጅ ይጠበቁ ዘንድ መጎሻሸማችን ወደፊትም የማይቀር ነውና በሰይጣናዊ መንገድ ያለን ተደርጎ እንዳይታይብንና ትችታችንን ሁሉ በፍቅር መንገድ እንዲያስተውሉልን እንጠይቃለን። እንደ እርሶ በክህነቱ የሌሉበትን ፣ አልፈውም በአጽራረ ቤተክርስትያን ጎራ ያሉትንና ከክርስትናዊ ሕይወት ውጪ በመሆን ለሚያውኩ ወንድሞችና እህቶችም ላይ የምናቀርበው ትችት ሁሉ ክርስትናም ሆነ አለማዊ ሕይወታቸውን እንዲመረምሩና አብረው በሰላምና በፍቅር ከወገኖቻቸው ጋር እንዲኖሩ እንጂ፤ ይኸውም ይሆን ዘንድ ዘወትር ለሁሉም በጸሎታችን እንለምንላቸዋለን።

በተረፈ የትግራይ ነጻ አውጪ ድርጅት በከተማችሁ ተክሎትና ለብዙ አመታት ከናንተ ጋር አብሮ የኖረው፣ ቀደም ሲል ኤርትርያን ጌቶቹ ሲያስገነጥሉ ያዳመቀ፣ ብዙም ሳይቆይ የቅዱስ ሚካኤልን ደብር ከኤርትራዊያን ጋር በማበር በተደረገው የነጠቃ ሙከራ ውስጥ አንዱ የነበረ፤ በቅርቡ ከሚካኤል ወጥቶ በተክላይማኖት ስም ቤተክርስትያን ከከፈተው ጋር አብሮ የቆየውና ሰሞኑን ለነ አባ ጳውሎስ እጅ መንሻ ያስገባው ታደሰ ፀሀይ ከከተማችሁ ለቆ ወደ ካሊፎርንያ ለተመሳሳይ ተግባር የተዛወረ መሆኑንን የደረሰን ዘገባ ያስረዳል። እንግዲህ ታደሰ ቢሄድም ሌሎች ታደሰዎችን ተክቶ ነውና መዘናጋት አስፈላጊ አይደለም።

ባለፈው በካቶሊክ ቻርቲ ውስጥ እየተካሄደ ያለውን ሕገወጥ ሰው ማስተላለፍ በተመለከተ በዚህ ገጽ መውጣቱ ይታወቃል። ከእጃችን ከገቡት ውስጥ የግለሰቦቹን ማንነት በመሸፈን ቅጅውን እንደሚከተለው ስናወጣ የሚያሳዝነን ነገር ቢኖር እውነተኛ የተባሉት ስደተኞች በስደት ላይ እየተሰቃዩ ባሉበትና እድላቸውን ለሌሎች በቀጥታ ከሞቀ ቤታቸው ተነስተው ከነቤተሰቦቻቸው በሀሰት በተገዛ መረጃ ወደ አሜርካን ሀገር እንዲገቡ መደረጉ ብቻ ሳይሆን፤ ሀላፊነቱን የወሰዱት ቤተሰቦችም የአቅም ጉዳይ ሕጉን ያልተከተለ፤ ከገቡም በኃላ ያለአግባብ ጥቅማ ትቅም ከታክስ ገቢ ከመንግሥት ማግኘትና በሕክምና  እንደዚሁም የምግብ እርዳታ እንዲያገኙ የካቶሊኩ መስሪያ ቤት ሰራተኞች ማድረጋቸው፤ አንደኛዋ ግለስብ ሕክምናቸውን ከጨረሱ በኃላ ወደ ሀገራቸው መመለሳቸው ፤ ከመንግሥት ወጪ ተደርጎ የተጓጓዙበት ወጪ አለመከፈሉ፤ ወዘተርፈ……. ለሚሉት ጥያቄዋች ከዚህ በታች የቀረቡትን መረጃዎች ሀሳብን በሚገባ ያንሸራሽሩና ጭብጥ ያሲይዛሉ የሚል እምነት አለን።










ከዚህ በፊትም የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር አምቻ የደብረ ምህረት ቅዱስ ሚካኤል ቦርድ አባል በነበረችበት ወቅት፤ ዝይን የተባለች ምዕመን ጋር ይህንኑ በካቶሊክ ቻሪቲ ውስጥ በሚካሄደው ሕገወጥ ሙስና ምክንያት መጋጨታቸውን በወቅቱ ከቤተክርስትያኑ የነበሩ እማኞች በሚገባ  የሚያስታውሱት ሁኔታ ነው። ከዚህ ውጭም አንዳንድ ግለሰቦች በቤተክርስትያኑ ስም በሀሰት ሰዎችን አስመጡ የተባሉ እንዳሉም ይነገራል። በተመረጡበት ወንበር አማካኝነት ያለአግባብና በሕግ ወጥ መንገድ ተጠቃሚ የሆኑ እራሳቸውና ተጠቃሚ ግለስቦች የሚያውቁት ሀቅ ነው በማለት በዚሁ ስናልፈው እልባት ለማግኘትና ሀሜቱን ለማቆም አሁን ያሉት ተመራጮች ምርመራ ቢያደርጉበት ይበጃል እንላለን።  

እንግዲህ መናገርም ሆነ መጣፍ በትውልድ ሀገራችን ቢነፈግ እነአምቼዎችና ገጻችን የጎነተለቻቸው ሁሉ ግምባር ፈጥረው ይህ ሀገራችን አሜሪካ የሰጠንን የመናገርና የመጻፍ መብታችንን ለማፈንና በሕገ መንግሥታችን ላይ የተደነገገውን ለመናድ የማይፈነቅሉት ድንጋይ የለም። እኛ እንደ እነርሱ ስለማናስብ ፤ እነርሱ በግል ፣ በቡድን ፣ በገጾቻቸውና በመሀበሮቻቸው ሁሉ ያልሞከሩት የለም።
በእምነታቸው ጸንተው የቆረቡ ከሆነ ፣ ነገርንም ሆነ ሁኔታዎችን በምን አይነት ክርስትያናዊ ስነ ምግባር መያዝ እንዳለባቸውና የመንፈስ አባቶችም ካሉዋቸው አይሸሽጓቸውም ለማለት ያስደፍረናል። እኛ የምንተቻቸውን ሁሉ ወንድሞቻችንና እህቶቻችን ናቸው፣ ሁሉንም እንወዳቸዋለን። ማንንም ሰው አንጠላም ፣ የነእርሱንም ክፉ ማየት አንፈልግም። ችግራቸውም ሆነ ደስታቸው የጋራችን ነው። በሀሳብና በድርጊት መለያየትና በዚያም ላይ በያዝነው የልዩነት አቋም መከራከርና መተቻቸት አግባብ ነው። ልዩነቶች እንደ ሁኔታው ሁሉ ይጎላሉም ሆነ ያንሳሉ። ሲሆን ደግሞ ልዩነቶች እንደተጠበቁ ሆነው ወይንም አሳንሶ በመያዝና በመቻቻልም መቀጠል ይቻላል።
ገና ለገና ስሜ ተነሳና ተተቸ ብሎ ጉሮ ወሸባ ማለት ደግሞ የሀሳብ አመዛዛኝነትን አድማስ ያጠባል እንጂ ለአዲስ ሀሳብና ግኝት አያጎለምስም። ለዚህም ነው ገጻችን በአንድ በኩል ሲተችና  ሲኮነን በሌላ በኩል ደግሞ ያገኘውን ሲቸር፣ ሲሳሳትም ይቅርታ ሲጠይቅ፣ ከሚወዱትም ሆነ ከሚኮንኑት ሀሳባቸውን እንደ አመቺነቱ ሲያስተናግድ አመትን ያስቆጠረው። በዚህ ሲጠላ በዚያ ከበሪታ ሲያገኝ ሁሉም የየራሱን ስሜት እንደ አሻው አፈራርቆበታል።

ነገር ግን አንድ ማስጨበጥ የምንወደው ነገር ቢኖር ሀይማኖታችንን እንወዳለን እናከብረዋለን። የሌላውንም ሀይማኖት እንጠብቃለን። ሁሉም በነጻነት ማምለክ አለበት እንላለን። የፈለገ የሀገር ቤቱን ሲኖዶስ፣ ያልፈለገ የውጪውን ወይንም ገለልተኛ ሆኖ በመረጠው የመጓዝ መብቱን እንጠብቃለን። ዳላስ በቆየንበት አጭር ጊዜ ስለ ቅዱስ ሚካኤል ደብር የሚበቃንን ያህል ባይሆንም የምንችለውን ያህል ጨብጠናል። ነገር ግን ሀይማኖት ቤት መሆኑ ቀርቶ ጎጠኝነት የሰፈነበት፣ ለግል ፍላጎት ብቻ ያደሩ ፤ ደብሩን በኃይል ከገለልተኝነት መንገዱ ለማውጣት የተነሱና በፖለቲካው የታወሩት፣ ወይንም የራሳቸውን ድርጅትና አላማ ብቻ በማራመድና ሲጠቀሙ ጥገታቸው የደረቀችባቸው (የነጠፈችባቸው)፣ ወዘተ……. በመሆን ሕብረት ፈጥረው የከፈቱትን ሴራ ስለተገነዘብን በኦርቶዶክስ ልጅነታችን በመቆርቆርና ለደብሩ ባለን ፍቅር ጭምር በምንችለው ሁሉ እርሱ በሰጠንና በፈቀደው መሰረት የአቅማችንን እየወረወርን ነው።

የቀደሙትን ብቻ ሳይሆን አሁንም ያሉትን የቦርድ ተመራጮችንም አልተውናቸውም አንተዋቸውም። ከኛ ጆሮ እንዳይደርስ በማለት በሚካኤል ሠይፍ ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖና ቁጥጥር ያደርጉበታል። ለምን የኛን ገጽ ሁሉንም በእኩልና በገለልተኛነት ብትቀበልም ከደብሩ ጋር ያከረሩት ላይ ግን ጠንከር እንደምትል አትሸሽግም። ከግለስብና ድርጅት አልፎ በተከበሩት የሀገራችን መሪ ፕሬዝዳንት ብራክ ኦባማ ላይ ይህ ገጽ ባልተስማማበት ጉዳይ ትችትን ሰንዝሯል። ሁላችንም በእርሱ አምሳል ተፈጥረናልና እንደመልካችን ምግባራችን በመለያየቱ ከጥንት ጀምሮ የነበረ፣ አሁንም ያለና እየኖርነው ስለሆነ ሁላችንንም ፈጣሪ የቅን ልቦናን ከማስተዋል ጋር አክሎ ለተቀረው ጊዜአችን ሰላምና ፍቅሩን ሰጥቶን ለንስሀ ያብቃን። በመንግሥቱም ይሰብስበን። አሜን።

እርሶስ ምን ይላሉ?

Thursday, May 5, 2011

ትኩስ ዜና!

የርሶ ብዕር አስተያየት ተሳትፎ ሕብረተሰባችንን ይጠቅማል ያሉትን አይንፈጉን ገንቢነቱ ቦታ ይኖረዋልና!

ማሳሰቢያ፡ ይህ ገጽ የተዘጋጀው የተለያዩ የኅብረተሰባችንን ሀሳብ ለመለዋወጫ እንጂ ለሚሰጡት ማንኛውም አስታየቶች በማንኛውም መንገድ ተጠያቂ አይደለም። ጉግል ድርጅትም ኃላፊነት አይወስድም። ኃላፊነቱ በሙሉ የአስታየት ሰጪው ብቻ ነው።


ትኩስ ዜና!

እንደምን አላችሁ? የሚቀጥለውን ዜና ያገኘነው ከእናንተ ከተማ ከርማ የተመለሰችው አባላችን አዲስ ከተዋወቀቻቸው ወዳጆቿ ትላንት ማታ የደረሳትን ዜና ነበር። እንደሚታወቀው ሁሉና ደጋግሞ እንደተዘገበው እጃቸውን ይሰጣሉ ወይንም በቁጥጥር ሥር ይውላሉ የተባሉትን በትላንት ማምሻ መፈጸሙን ነበር።

ይህንን ዜና ከመቋጨታችን በፊት፣ ይህንን ገጽና ሰንበቴ የተባለውን ብሎግ ማንነት ለማወቅና ለመቅላት ጉግልን መረጃ እንዲሰጣት የፍርድ ቤት ትእዛዝ ያወጣችውን ግለሰብ ነገ ከእርሷ ቤሮ ኮምፕዩተር ወይንም ባሏ ከሚሰራበት ካቶሊክ ቻሪቲ ኮምፒዩተር ብንዝግብባት ምን ልትሆን ይሆን? እኛን ጸጥ ለማሰኘት ለይታ የተነሳችው ከማን ጎራ መሆኗን ስላስረገጠች የነተኩላው አጋርነቷን ይፋ አደርገች እንጂ ምንም አዲስ ነገር የለም። ሜይ 2 ያለፈው አመት ከተደራጁት አሸባሪዎች ጀርባ ከባሏ ጋር በመሆን ከሽብሩ በኃላ ስብሰባ በአዳራሹ በማድረግ ሥርዐቱን ለመናድና በአዲስ ተዋቅሮ ከውጪ ለሚጠብቀው የአባ ጳውሎስ ለላከው ጳጳስ ነኝ ተብዪ ለማስረከብ አልነበርምን? ትምህርት የሌላትና የሌሎች መጠቀሚያ ሆና የምትነዳው የመለስ ዜናዊ አምቻ ገንዘቡን ከየት አምጥታ ጠበቃ ቀጠረች? ከጠ/ሚኒስትሩ ፣ ከመንግሥት ወይስ ካቶሊክ ቻርቲ ውስጥ በሚደረገው የሕግ ወጥ ሰው ማስተላለፍ ንግድ ገቢ ይሆን? ስንቱ በስደት ሀገር ሲንገላታ የከፈለ ግን ከአዲስ አበባ በ3ኛ ሀገር አማካኝነት በሳምንቱ ዳላስ የገቡትን ስም እንዘርዝርና ትረፈው ይሆን? አሁን የነካሽ ሳይኖር ለምን የባልሽን የጡረታ መብት ልታስጠፊ ከሆነ ደሳለኝ እጅ ያገኘነው እንደዚሁም አሁንም እየደረሰን ያለው ብዙ ጉድ አለና አታስጨክኝን!

ገና ወር ያልሞላው የታደስ ተክላይማኖት የተባለው ቤተክርስትያንና ማስተዳደር ያቃተው የርእሰ ደብር ጊዮርጊስ ቤተክርስትያን ሰሞኑን ሲታሽ በከረመው ስብሰባ በትላንቱ እለት ለጳጳስ ተብዪው የጳውሎስ ቅጥርኛ እንዲያስረክቡና በእርሱ እንዲተዳደሩ ትእዛዝ ተሰጠ። ምሽቱን በህመም አለ የተባለው ታደሰም በጎ ማደሩን ባናውቅም ገና ሀኒሙኑን እንዳላስጨረሱት ከስብሰባው ተካፋዮች እህታችን ዘግባዋለች። ለጊዜው ወደ ሯሌት ከሰው ቤት ያረፈውም ጳጳስ ተብዬ ሥልጣነ ጵጵስናውን መንበር ወደ ዳላስ ለማዞር የቤት ኪራይ እየተፈለገለትወይንም ከህንጻው ውስጥ ቤሮና መኖሪያ ያደርግ ይሆናል የሚል ነውና ዳላሶች ተጠንቀቁ እንላለን።

ከዳላስ ሚካኤል ሠይፍም የደረሰን ለዚሁ እርክብክብ ዳላስ ከገቡት ውስጥ 2ቱ ባለፈው በሚካኤል ደብር የዳግማይ ትንሣኤን ካስቀደሱ በኃል እንደ እንግዳ ከምዕመናኑ ጋር ትውውቅ ሲያደርጉ ያረፉትም ከአዲሱ ካህን ቤት ሳይሆን እንዳልቀረ ተገምቷል። እንዚህን ግለሰቦች አጅበው ከመጡት 3 ግለሰቦች መካከል 1ኛው አደግድጎ ከመግቢያው በር ላይ 2ቱ ከምዕመናን ተደባልቀው ሲሰልሉ እንደነበርና በረኛውም በመጨረሻ እንግዳ ተብዬዎችን መቀላቀሉን አብሮ የደረሰን ዘገባ አመልክቷል። ይኽንኑ መሰሪያን ከመቼውም በላይ በመተባበር ደብራችሁን እንድትጠብቁ እያሳሰብን የተባበረና እውነተኛ አማኝ ከፈጣሪው ጋር ያሸንፋል። እንግዲህ ፖለቲከኛና ነጻነት የሚሹ ኃይሎችና ድህረ ገጾች ከጎናችሁ በመሆን የተደቀነባችሁን ፈተና እንድትወጡ ጥሪያችን ዳላስ ላይ ሳይወሰን ለሁሉም ወገናችን ጭምር ነው።
 
ሰፋ ያለ ዝርዝር ወደፊት ይቀርብበታል። ቸር እንሰንብት!

እርሶስ ምን ይላሉ?

Wednesday, May 4, 2011

ኮርት አለብኝ…….

የርሶ ብዕር አስተያየት ተሳትፎ ሕብረተሰባችንን ይጠቅማል ያሉትን አይንፈጉን ገንቢነቱ ቦታ ይኖረዋልና!

ማሳሰቢያ፡ ይህ ገጽ የተዘጋጀው የተለያዩ የኅብረተሰባችንን ሀሳብ ለመለዋወጫ እንጂ ለሚሰጡት ማንኛውም አስታየቶች በማንኛውም መንገድ ተጠያቂ አይደለም። ጉግል ድርጅትም ኃላፊነት አይወስድም። ኃላፊነቱ በሙሉ የአስታየት ሰጪው ብቻ ነው።


ኮርት አለብኝ…….

እንደምን ከርማችኃል? እኛ በፈጠረን በእግዚሀብሔር ችሮታ ለዚህ አብቅቶናልና ለቅዱስ ስሙ ክብርና ምስጋና ለዘላለም ይሁን። አሜን። ባለፈው እንዳስነበብናችሁ ሁሉ የዚህ ገፅ ዝግጅት አባል የሆነች እህታችን ከናንተ ዘንድ ከርማ ዛሬ ምሽቱን ስትለቅ፤ እንድትቆይ ካደረግንበት አንዱ ምክንያት የደብረምህርት ቅዱስ ሚካኤል በነጥሩአየር ተከሶ ከተፈረደለት በኃላ ከሳሾች የይግባኝ አቤቱታ በመጠየቃቸው፤ የይግባኝ ሰሚው ፍርድ ቤት የዛሬውን ችሎትን እንድትዘግብልን ነበር።

ከምሳ በኃላ የተጀመረው ችሎት በሁለቱም ወገን ከቀረቡት  መረጃዎች ሌላ ለእየአንዳንዶቻቸው የ15 ደቂቃ የቃል ክርክር ያሰሙ ሲሆን ፤ ይህንኑ ጉዳይ የሚያዩት ዳኞች ወደፊት ያላቸውን የሕግ ውሳኔ እንደሚሰጡበት በማስታወቅ ተፈጽሟል። ይግባኝ ባዩ የከሳሽ ነገረፈጅ ያለደንበኞቹ ብቻውን የቀረበና ስለጠቅላላው የደብሩና የከሳሾችን ጭብጡ አናሳ እንደነበር እህታችን ስትታዘብ፤ የከሳሾችን ወገን ሆነው ለትዝብት የመጡት መስፍን እኝ ብዬ የተባለውና እስስቱ ሰይጣን የሚሉት ሌላው ደብር ከሳሽ ፀሀይጽድቅ የተባሉት አጽራረ ቤተክርስትያንና ጸረ ክርስትያኖች ናቸው። እንደ እህታችን ዘገባ ከሆነ ከደብሩ በኩል እንደጠበቀችው የሰው ብዛት አለማየቷ እራሷን ለመደበቅ አዳድቷት እንደነበር አልሸሸገችም ምክንያቱም ማንንም ፈርታ ሳይሆን ለወደፊቱ አንዳንድ መረጃዎችን ለማግኘት እንዳትታወክ እንጂ። ቀደም ብላም ለሌላ ጉዳይ በአንዱ የዳወንታወን ሆቴል የቀጠሮዋ ሰአት እስኪደርስ በመኪና ማቆሚያ ገራዥ ውስጥ በትራንስፖርት ስራ ወደሚተዳደሩት ወገኖቻችን ጠጋ ብላ አቁማ በነበረበት ጊዜ፤ ከነበሩት ውስጥ አንዱ ተኩላው ነበር። እርሷም የሚላመጥ ባገኝ ብላ ጆሮዋን በመጣል  ያገኘችው ቢኖር “ኮርት አለብኝ….” ሲል ነበርና የትኛው መሆኑ ባይታወቅም እርሷ ከነበረችበት አልታየምና ከየትኛው እንደሆን ወደፊት የሚታወቅ ይሆናል። የዛሬውን የፍርድ ቤት ውሎ ማን እንደሚዘግብለት ባይታወቅም መስፍን እኝ ብዬ ABC አድርጌአልሁ የሚል ከሆነ እንግዲህ ሊታይ ነውና እስስቱ ፀህይጽድቅ ግን ምን እንደተባለ የማይገባው የትምህርት ድሀ ነውና። ከዚህ በፊትም የፍቅሩ ታደሠን ወንድም ብርሀነማርቆስ ታደሠ የሚሉትም ለናሙና ወይም ለቁጥር ከፍርድ ቤቱ ችሎት ተዶለ እንጂ ከተኩላው ያልተሻለና የእንግሊዘኛው ቋንቋ ችግር እንዳለበት በሚገባ አስጨብጦናል።

በተረፈ ስለነበትሩ ገ/እግዚሀብሔርና አለማየሁ ኪዳኔ ላይ ሀገር ወዳድ አስመስለው የጀመሩትና ያስጀመሩት የሀሰት ወሬ መንገዱን እንዳለያዘላቸው ደርባ ገልጻልናለችና በቸር እንሰንብት።

እርሶስ ምን ይላሉ?  

የርሶ ብዕር አስተያየት ተሳትፎ ሕብረተሰባችንን ይጠቅማል ያሉትን አይንፈጉን ገንቢነቱ ቦታ ይኖረዋልና! ማሳሰቢያ፡ ይህ ገጽ የተዘጋጀው የተለያዩ የኅብረተሰባችንን ሀሳብ ለመለዋወጫ እንጂ ለሚሰጡት ማንኛውም አስታየቶች በማንኛውም መንገድ ተጠያቂ አይደለም። ጉግል ድርጅትም ኃላፊነት አይወስድም። ኃላፊነቱ በሙሉ የአስታየት ሰጪው ብቻ ነው።


fromlegal-support@google.com
todallaseotc@gmail.com
dateTue, May 3, 2011 at 7:27 PM
subjectRe: Subpoena notice from Google (Internal Ref #135517)
mailed-bytrakken.google.com
signed-bygoogle.com
hide details May 3 (1 day ago) 
Hello,

Google has received a subpoena for information related to your Google
account in a case entitled Fetelework Golla, et al. v. Does 1-3, District
Court of Dallas County, Texas, DC-11-04530 (Internal Ref. No. 135517).

To comply with the law, unless you provide us with a copy of a motion to
quash the subpoena (or other formal objection filed in court) via email at
legal-support@google.com by May 22, 2011, Google may provide responsive
documents on this date.

For more information about the subpoena, you may wish to contact the party
seeking this information at:

Michelle C. Jacobs
Haynes and Boone, LLP
2323 Victory Avenue
Dallas, TX 75219
(214)651-5000

Google is not in a position to provide you with legal advice.

If you have other questions regarding the subpoena, we encourage you to
contact your attorney.

Thank you,

Google

We the Bloger are not intimidate by such action, it is our first amendment right to comment on the blog world and Google must protect its user by any means before collaborating.