Wednesday, June 29, 2011

‹‹በጎውን ማን ያሳየናል የሚሉ ብዙ ናቸው››

የርሶ ብዕር አስተያየት ተሳትፎ ሕብረተሰባችንን ይጠቅማል ያሉትን አይንፈጉን ገንቢነቱ ቦታ ይኖረዋልና!

ማሳሰቢያ፡ ይህ ገጽ የተዘጋጀው የተለያዩ የኅብረተሰባችንን ሀሳብ ለመለዋወጫ እንጂ ለሚሰጡት ማንኛውም አስታየቶች በማንኛውም መንገድ ተጠያቂ አይደለም። ጉግል ድርጅትም ኃላፊነት አይወስድም። ኃላፊነቱ በሙሉ የአስታየት ሰጪው ብቻ ነው።



                                                   ‹‹በጎውን ማን ያሳየናል የሚሉ ብዙ ናቸው››

                                                                     (መዝ. 4፥6)፡፡



ስለ ዘመናችን ድንቅነት ብዙ ተነግሯል፡፡ የንግግሩ ምራቅ ሳይደርቅ ግን አሳዛኝነቱ ይተረካል፡፡ ዘመናችን ከተደነቀባቸው ነገሮች አንዱ የመረጃ ዘመን መሆኑ ነው፡፡ ሰዎች ስለ ራሳቸው ሳይሆን ስለ ሌሎች፣ ስለ ጎረቤታቸው ሳይሆን ስለ መካከለኛው ምሥራቅ ብዙ መረጃዎችን የሚሰሙበት ዘመን ነው፡፡ የመስማት አንዱ ዓላማ ለመመካከር፣ መራራው ወደ ጣፋጭ እንዲለወጥ ለመጸለይ ነው፡፡ የመረጃው ዘመን ግን ሰምቶ ማዳነቅ ብቻ ነው፡፡ ችግሮች ብዙ ናቸው፣ የመፍትሔ ድምፆች ግን አይሰሙም፡፡ ብዙ የመረጃ መረቦች የጭንቅ ወሬ ካጡ ይጨነቃሉ፡፡ የጦርነት፣ የተፈጥሮ አደጋ፣ የእርስ በርስ መተላለቅ ትልቅ ርእሳቸው ነው፡፡ በአገራችን በኢትዮጵያ በ1998 ዓ.ም በነበረው ግርግር አንድ የጋዜጣ አዘጋጅ ለጓደኛው ሲናገር፡- ‹‹ይህ ግርግር ሳይበርድ ለሦስት ወር ከቀጠለ የጀመርኩትን ቤት እጨርሳለሁ›› እንዳለ፣ ጭንቅ ባላለቀ እያሉ የሚሳሉ፣ እንደ ዕድር ጡሩንባ ነፊ ሞተ እንጂ ተነሣ የማይሉ፣ እንደ ጠመንጃ አፈ - ሙዝ ከአፋቸው ደህና የማይወጣ፣ ያልተባረኩ አንደበቶች በዝተዋል፡፡ ብዙ የቴሌቪዥን ጣቢያዎችን እንለዋውጣለን፡፡ ሁሉም የሚያመነዥጉት ያንን ክፉ ነው፡፡ አዋቂዎቹ የሚሰጡት ትንታኔ የሚመጣውን ቀውስ ጠቋሚ ነው፡፡ ስለዚህ የግለሰቦች ቀውስ እያለፈ ዓለም ራሷ እየቀወሰች መሆኗን እንረዳለን፡፡ ግለሰቦች ሲቃወሱ ምድር ችላቸው ብዙ ዘመን ኖረናል፡፡ ምድር ከቀወሰች ግን ማን ይችላታል@

ተበልቶ እንዳለቀ አጥንት ወይም የበቆሎ ቆረቆንዳ የቴሌቪዥን ጣቢያዎችን ብናገላብጣቸው ለጥጋብ የሚሆን አንድም ነገር የለባቸውም፡፡ ወደ ኢንተርኔት ጫካም ስንገባ ወሬ ከመንግሥታዊ ተቋማት ወደ ግለሰብ ተቋማት ዝቅ ብሎ፣ ‹‹ሐሜት ድሮ ቀረ በቃል ብቻ›› የሚሉ የጽሑፍ ሐሜተኞችን እናገኛለን፡፡ የሰውን ስም ቡና ላይ ከማንሣት ድረ - ገጽ ላይ ወደ ማንሣት ተሸጋግረናል፡፡ ብሔራዊ የነበረውን ኃጢአታችንን ዓለም አቀፋዊ አድርገነዋል፡፡ ጫካ ገብቶ በጥይት የመዋጋት ዘመን በኢንተርኔት ውስጥ መሽጎ በስም ማጥፋት አረር እንደ ተለወጠ እያየን ነው፡፡

ጉድ ያለበት የሰው ልጅ የሌላውን ጉድ ለማውራት በጀት የባጀተበት ዘመን መሆኑን እናያለን፡፡ ዘመኑና ሥልጣኔው መስተዋት ሳይሆን መነጽር መሆናቸውን እናስተውላለን፡፡ መስተዋት ራስን ያሳያል፣ መነጽር ሌላውን ያሳያል፡፡ በክፉ ወሬዎች በተከበበው ዘመን የብዙዎች ነፍስ ተጨንቃለች፡፡ በሩቅ ስላለው ሰው እያወቁ ራስን አለማወቅ፣ የሌሎችን ክፋት እየተረኩ የእግዚአብሔርን በጎነት መዘንጋት ለሰዎች ዕረፍትን አልሰጣቸውም፡፡ በእውነት፡- ‹‹በጎውን ማን ያሳየናል@ የሚሉ ብዙዎች ናቸው›› (መዝ 4፥6)፡፡

ስለ ሰዎች ክፋት አንድ ሰዓት ማውራት መቻል ስለ እግዚአብሔር በጎነት ዐሥር ደቂቃ መነጋገር አለ መቻል በጣም ያሳዝናል፡፡ የሰው ልጅ የትኛውም ማንነቱ አያሳርፍም፡፡ እንኳን ከድካሙ ከብርታቱም ጉድለት አለበት፡፡ ነቢዩ፡- ‹‹ጽድቃችንም ሁሉ እንደ መርገም ጨርቅ ነው›› ያለው ለዚህ ነው (ኢሳ. 64.6)፡፡ የሚያሳርፈው የመስቀሉ ሥራ ብቻ ነው፡፡ ስለ ክፉ አንድ መጽሐፍ መጻፍ ስለ መጽናናት ግን አንድ መስመር አለመጻፍ በእውነት ምስኪንነት፣ የሞትም አገልጋይ መሆን ነው፡፡ የሰዎችን መልካምነት በካባ እየሸፈኑ ትንሽ ስህተታቸውን በአጉሊ መነጽር ማየት በእውነት አለመታደል ነው፡፡ ዘመናዊነትን ስናየው የክፋት ማፍጠኛ እንጂ የመልካም ነገር ማፍጠኛ አለመሆኑ ያሳዝናል፡፡

ብዙ የዓለማችን ሕዝቦች ከመረጃ መረቦች ራሳቸውን እያገለሉ ነው፡፡ የራሳቸውን ችግር ሳይፈቱ ስለ ሰው ኃጢአት መነጋገር እየሰለቹ ነው፡፡ ልክ ያልሆኑ ነገሮችን ከሚያሰሙ ስብከቶች ልክ የሆነውን ወደሚያሳዩ አገልጋዮች ዘወር እያሉ ነው፡፡ የሰው አእምሮ በብዙ ጭንቀቶች በተወጠረበት በዚህ ዘመን፣ ብዙ አደንዛዥ ዕፆች በሚወሰዱበት በዛሬው ጊዜ የሚበጀው ሰላማዊ መልእክት ብቻ ነው፡፡ በራሳቸው መወደድ ያልቻሉ ሌላውን እያስጠሉ ለመወደድ የሚሹ ሰዎችን ብዙዎች እየራቁ ‹‹በጎውን ማን ያሳየናል@›› እያሉ ነው፡፡ እኔ ቆንጆ ነኝ ለማለት እገሌ አስቀያሚ ነው ማለት አስፈላጊ እንዳልሆነ ሕዝባችን እያስተዋለ ነው፡፡ እናንተን የምንቀበላችሁ በራሳችሁ ልክ ስትሆኑ እንጂ እነ እገሌ ስለ ተሳሳቱ አይደለም እያለ ነው፡፡ በእውነት ጠብን ሳይሆን ፍቅርን የሚዘሩ፣ ክርክርን ሳይሆን መግባባትን የሚያመጡ አገልጋዮች እየተፈለጉ ነው፡፡

ራሳችንን ስናየው ሬዲዮን በደንብ ሳንጠቀም ቴሌቪዥን የጀመርን፣ ታይፕን በደንብ ሳንጠቀም ኮምፒዩተርን የተከልን፣ አጠገባችን ካለው ሰው ጋር ሳንግባባ ዓለም አቀፍ መረጃ ውስጥ አሳብ የምንሰጥ፣ ከወንድማችን እየተጣላን ከዓለም አቀፍ ወጣቶች ጋር ማኅበርተኛ መሆን የምንፈልግ፣ በጾም ከበሮ መምታትን እየጠላን ወገናችንን በስድብ የምንደልቅ፣ ያጎረስነው ሰው እያነቀ በላይ በላዩ የምናጎርስ፣ ከሥልጣኔው ክፉውን የምንጠቀም ነን፡፡

በብዙ ውጣ ውረድ ያለፈው ሕዝባችን ዕረፍትን ፍለጋ ወደ ቤተ ክርስቲያን ሲመጣ በሁከት ድምፅ እያሸበርነው፣ ማንንም አትመን እያልን አውሬን እየሳልንለት፣ የሥጋ ቅንዓታችንን ሃይማኖታዊ ካባ አልብሰን እያስጨነቅነው ነው፡፡ ወጣትነቱን በትክክለኛ ጎዳና ለመምራት የመጣውን ወጣት ሃይማኖታዊ ጠብ እንዲጣላ፣ በዝማሬ በስብከት ካጽናኑት አገልጋዮች ጋር እንዲታኮስ እያደረግነው ነው፡፡ ከዓለም ሁከትን ሸሽቶ የመጣው ትውልድ፣ በቤተ ክርስቲያን የሁከትን ድምፅ ሲሰማ ‹‹በጎውን ማን ያሳየናል@›› እያለ እየተጨነቀ ነው፡፡ ያሉት አገልጋዮች ተቀንሰው አይደለም፣ በእጥፍ ተጨምረው እንኳ ሕዝቡን መድረስ አይቻልም፡፡ ከዚሁም ላይ ስም እየሰጠን እየቀነስን ቤተ ክርስቲያንን የወላድ መሐን ማድረጋችን፣ የመናፍቃኑን አዳራሽ አለመሙላት ከውስጥ መግፋታችን አሳዛኝ ነው፡፡ ብዙ የሳጥናኤል የውስጥ ካድሬዎች ከውስጥ ሆነው ሲገፉ ከደጅ ያሉት ደግሞ ይቀበላሉ፡፡ በዋጋ የተሰበሰበውን ሕዝብ ያለ ዋጋ መበተን፣ ፍቅር አጥቶ ከዓለም የመጣውን ሕዝብ ጠብና ክርክር ማስጠናት ተገቢ አይደለም፡፡ አንድ ሕገ መንግሥት (መጽሐፍ ቅዱስ) ይዘን መለያየት ለአረማውያን ሰይፍ ራሳችንን ማዘጋጀት ነው፡፡

ሕዝባችን የፍቅር ሰባኪዎች ሲፋቀሩ፣ የይቅርታ አዋጅ ነጋሪዎች ይቅር ሲባባሉ ማየት ይፈልጋል፡፡ የቃል ስብከታችንን ከተማው ጠግቦት በሕይወታችን ስንኖረው ማየት እየፈለገ ነው፡፡ በየአድባራቱ እየታየ ያለው የጠብ አዝመራ፣ ጭር ሲል የማይወዱት የጠብ ጫሪዎች፣ በሰው ሬሳ ለመኖር የሚያቅዱ የክርስቶስ ጠላቶች፣ ስሜታቸውን መግዛት ያቃታቸው የገምቦኞች ክተት ነው፡፡ ሕዝባችን የእግዚአብሔርን ቃል ዳኛ አድርጎ ማነው የሳተው? ማለት አለበት፡፡ ጋዜጣ ላይ የወጣ ሁሉ የመጨረሻው እውነት ሆኖ ሊታየው፣ በኢንተርኔት የተለቀቀ ሐሜት የሲኖዶስ ውሳኔ አድርጎ ሊቀበለው አይገባም፡፡ ሁሉን የሚበክሉ ሚዛን የለሾች፣ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያንን ከመልካም አገልጋዮች ብቻ ሳይሆን ከተሰቀለው ጌታ ሊለዩአት የተነሡ፣ ወንጌልን ከኦሪት፣ ክርስቶስን ከሙሴ፣ መጽሐፍን ከተረት መለየት ያልቻሉ፣ እውነት በሚመሰል ሐሰት፣ ቅንዓተ ቤተ ክርስቲያን በሚመስል ራስን መስበክ ሕዝቡን እያደናገሩት ይገኛሉ፡፡ ሕዝቡም የሚይዘውን የሚጨብጠውን አጥቶ ‹‹በጎውን ማን ያሳየናል@›› ይላል፡፡

ወገናችን ዕድሜውን በሙሉ ብዙ ጭንቆችን ያየ፣ ብዙ ጦርነቶችን ያሳለፈ፣ የኑሮ ጠባሳ መልኩን ያጠፋው፣ በብዙ ቀBስለትም የሚያቃስት ነው፡፡ በዚህች አገር ላይ የኖረ፣ ያለፉትን ዘመናት ሰቆቃ ያየ ወገን፣ ሕዝቡን እንደ ገና አያስጨንቅም፡፡ የሚያጽናናውን ወንጌል በመስበክ ያረጋጋ ነበር፡፡ ጭጋግና ደመናው ነገን አላሳይ ላለው ወገን፣ ዝናብ የሌላቸው ደመናዎች ላደከሙት ሕዝብ የወንጌልን ማዕድ የምናቀርብበት ዘመን አሁን ነው፡፡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያንን መወከል የማይችሉ አጽራረ ወንጌሎች የአዋቂዎችን ልብ እየሰበሩት፣ ትውልዱ ያዳነውን ጌታ እንዳያይ የክርስቶስን ደም እያክፋፉበት መሆኑ ያሳዝናል፡፡ መሳሳት የማይደክማቸው፣ ከትላንት ጥፋት የማይማሩ በመሆናቸው ሊለቀስላቸው ይገባል፡፡ ሊሰበክ ሊታወቅ የሚገባው ማን ነው@ የቤተ ክርስቲያን መሠረትና ጉልላትስ ማን ነው? ኢየሱስ ክርስቶስ አይደለምን? ‹‹ሞኝ ባያፍር ዘመዱ ያፍራል›› እንዲሉ በእነዚህ ሰዎች እስከ መቼ እናፍራለን? በአይሁድ ምኩራብ ክርስቶስ በተስፋ ይሰበካል፣ አይታፈርበትም፡፡ በእስላም መስጊድ ዒሳ ተብሎ ይነሣል፡፡ በእነዚህ ሰዎች ዘንድ ግን ኢየሱስ ክርስቶስን የጠራ በውግረት ይሙት ተብሎ ይፈረድበታል፡፡ ጠላትነታቸው ከፍጡር ሳይሆን ከተሰቀለው ጌታ ጋር ነውና ንስሐ እንዲገቡ እንጋብዛለን፡፡ ነፍሳቸውም በሐዋርያት ውግዘት ውስጥ ነች፡- ‹‹ጌታን ኢየሱስ ክርስቶስን የማይወድ ቢኖር የተረገመ ይሁን›› (1ቆሮ. 16.22) በተባለው ቃል የታሠሩ ናቸው፡፡

ሕዝቡ በዕንባ የሚዘምረውን ዝማሬ ያንተ አይደለም ይሉታል፣ የራሱ ያልሆነ ነገር እንዴት ያስለቅሰዋል? ልቡን ያሳረፉለትን ሰባኪዎች መናፍቃን ናቸው ይሉታል፣ የተፈወሰበትን መጻሕፍት የባዕድ ናቸው ይሉታል፡፡ በዚህ ሁሉ ውስጥ ‹በጎውን ማን ያሳየናል? የሚሉ ብዙ ናቸው›› (መዝ 4፥6)፡፡

ሕዝባችንም አደባባዩን የያዙ እውነተኞች ናቸው ብሎ ማሰብ የለበትም፡፡ ቅንዓት በዲግሪም አይለቅምና አዋቂዎች ነን በሚሉ ፈሪሳውያን ግራ ሊጋባ አይገባውም፡፡ እውነት ምንድነው? ብሎ ሊጠይቅ፣ ክርስቶስን የማይወድ የተረገመ መሆኑን ሊገነዘብ ይገባዋል፡፡ ትላንት ያስተማሩት አገልጋዮች ዛሬ ጦርነት ሲታወጅባቸው የአንዱን ቀን ማጽናናታቸውን እንኳ አስቦ ለምን@ ሊል ይገባዋል፡፡ ባለቤቱ፡- ‹‹እኔ ኦርቶዶክሳዊ ነኝ›› እያለ አይደለህም ማን ይለዋል? እነዚህስ ስም አጥፊዎች ይህንን እንዲያደርጉ ፈቃድ የሰጣቸውና የወከላቸው አካል ማን ነው@ ማለት አለበት፡፡ መጽሐፍ ቅዱስን በመግለጥ ሁሉንም አገልጋዮች በቃሉ መመዘን ይገባል፡፡ አሊያ ያለፉት ዘመናት ስህተት ሳያንስ ሌላ ደም በእጃችን እንዳይገኝ መጠንቀቅ ይገባል፡፡

ከዚህ በላይ የቀረበው ጥሁፍ ከhttp://dejesemay.org/ ገፅ የተወሰደ መሆኑን እናረጋግጣለን።

ይህን ጥሁፍ የለጠፍንበትም ምክንያት የምንሰራውን ሁሉ በመመርመር እንድናስተውል ይረዳን ዘንድ ሲሆን ከኛ የተለየ ሀሳብ ላላቸውና ለተለየ አላማ አውቀውም ሆነ ሳያውቁ እየፈጸሙ ላለው እጸጽ ፣ ፈጣሪ አስታግሶ የመመርመርና የማስተዋሉን ልቦና እንዲሰጥልን ነው።

እኛ ገፃችንን ከከፈትንበት ዕለት ጀምሮ፤ ገጻችን የኮነነቻቸው ወንድሞችና እህቶችን ብቻ ሳይሆን የሌላውንም አንጀት አስለቅሳለች። ለጀብዱ ሳይሆን ገጿ ከልቧ በቅንንነት ላደረገችው ማንኛውም እጸጽ ዛሬም ይቅርታን ትጠይቃለች። በአንጻሩም ያበረከተችውና እያበረከተች ያለችሁን በጎ ጎኗን ሳይዘነጋላት እንዴት አስተዋጾ ማድረግ እንደምትችል ከላይ የለጠፈችውንም ቅጂ በማስተዋል የተሻለ ግልጋሎትን ይስጣት እንላለን።

የተወደዳችሁ የገጻችን ተከታታዮች እንደምን ከርማችኃል? በእርሱ ፈቃድ ዛሬም ወዶ ለፈቀድልንና ዳግም በዚች ጦመር ላገናኘን ለልዑል እግዜአብሄር ክብርና ምስጋና ይሁን። አሜን። የዳላሱ ቅዱስ ሚካኤል ሠይፍ ተባባሪያችንም እንዴት የደመቀ ጉባኤና የሰኔ ሚካኤል በዐለ ንግሥ እንዳሳለፋችሁ ያካፈለን ውብ ነውና ለዚህም ፈቃዱን ላደረገላችሁ ለልዑል እግዜአብሔር ክብር ምስጋን እስከ ዘለዓለም ይሁን።አሜን።

ለዚሁ በዐል ተጋብዛ ከቅድስት ሀገር ኢትዮጵያ የመጣችውን ዘማሪ ቪዛ እንዳይሰጣት የነበረውን የጠላት ሥራ ከሽፎ ለመጀመሪያ ጊዜ በምድረ አሜሪካ በዳላስ የቅዱስ ሚካኤል ደብር መገኘት ያመማቸው፤ ዘማሪ ዘርፌን ለማብጠልጠል ያልፈነቀሉት ድንጋይ የለም። እርሷ ግን ወደ አለም ገብቼ እግዜአብሄር የሰጠኝን ጸጋ ዋጋ አላሳጣውም በማለት በመንፈሳዊው ዝማሬዋና ግልጋሎቷ እየተባረካችሁበት መሆኑን ነው። ሌላው ኢላማቸው ደግሞ ከአትላንታ የመጣውን መምህር ልዑለቃል ላይ ነበር። ዛሬም በሕይወት ያሉና እስከ ጳጳስነት የበቁ ታላላቅ አባቶች ስር ከቆሎ ተማሪ ጀምሮ በሥርዐት አርቀው አሉን ከምንላቸው የቤተክርስትያናችን ሊቅ ተራ ያደረሱት መምህር ነው። አሜሪካ ከመጣም በኃላ ተመልሶ በቅድስት ሀገር ለአመታት ቤተክርስትያናችንን አገልግሎት ሰጥቶ የተመለሰና አሁንም በአትላንታ ክሚሰጠው  መንፈሳዊ ግልጋሎት ጎን ለጎን እራሱን ወደ ከፍተኛ ተቋም ትምህርት በማሳተፍ ላይ የሚገኝና የቤተክርስትያናችን ተስፋ የጣለችበት ሊቃችን ነው በሚል በቂ የሆነ ማብራሪያን ያካፈለን የሚካኤል ሠይፍ አባል ነው። እንግዲህ እነዚህን ብርቅዬዎቻችን ላይ የተነጣጠረው ደባ ቤተክርስትያናችንን የወላድ መካን ለማድረግና ብቃት ያላቸውን አገልጋዮቻችንን በማራቅ የኦርቶዶክሳዊ እምነትን አዳክሞ ለማጥፋት የተከፈተና እየተካሄደ ያለ ሰይጣናዊ ምግባር ነው።

እነዚሁ በኦርቶዶክስ ካባ ስር በቤተክርስትያናችን ውስጥ የተሰገሰጉትን ለይቶ በማወቅ ማስወገድ ተገቢ ነው። በተለይም በምህጻር ቃል ’ማቅ’ ወይንም ማህበረ ቅዱሳን የተባለው ቡድን በቁጥር 1 የሚጠቀስና ንጹሀንን በማሳሳት ወደ እርሱ ጎራ በማስገባት መሳሪያ ማድረግ፣ ደካማና ለመተዳደሪያ በአገልግሎት ላይ የተሰማሩትንና በፈተና የወደቁትን በመለየት ድክመታቸውን ጨብጦ ማሰፈራሪያ በማድረግ የእርሱ የግዳጅ ሰለባ ያደረጋቸው ሲሆኑ፤ አንተባበር ያሉትን ደግሞ የተለያየ ስም በመስጠት ከቤተ ክርስትያኗ እንዲገለሉ ማድረግ፣ ያልተወገዘውን ተወግዟል፣ ያልተኮነነውን ተኮንኗል፣ ያልሰረቀውን ሌባ፣ የመሳሰለውን ሀሰታዊ ዘመቻቸውን በቃልና በጥሁፍ በተለያየ መንገድ በማሰራጨት ይፈጽማል። ለምሳሌ በዳላስ ቅዱስ ሚካኤል ካቴድራል ደብር ውስጥ ተሰግስገው የነበሩትና ቤተክርስትያኑን በንዋይ ሲያደሙ፣ የደብሩ ተቀጣሪና ፈላጭ ቆራጭነት ሥልጣን በመያዝ፣ ድርጅታቸው በሰሜን አሜሪካ እንዲያብብ ዋሻ በማድረግ፣ እንዳይታወቅባቸው ጥያቄ ባነሳ ምዕመን ላይ የሀሰት ስም በመስጠት መከፋፈል፣ በካህናቱና በምዕመኑ መካከል ልዩነትን መፍጠር፣ የትምህርት ኮሚቴውን በመቆጣጠር የሚጋበዘው መምህር የእነርሱ አባል ብቻ መሆን እንዳለበት፣ ሌላው በእነርሱ መናፍቅ ስም እየተሰጠው ሲገለል፣ ወዘተ…. ያደረሱት በደል ገሀድ እየወጣ ሲመጣና ድርጊታቸው ተወግዞ ድርጅታቸው ሲገለል ፣ ወተት ያቆመች ጥገት ላም አድርገው ደብሩ እኛን ካስከፋ በፈለገውም መንገድ ቢሆን መንጠቅ ካልሆነም ማዘጋትና ማጥፋት በሚል መርሆ የጀመረውን የነውጥና የሀሴት መንገድን ነበር  በሜይ 2ቀን 2010 በደብራችሁ የተመራውን ሁከት የፈጠረው።

ይህ ቡድን በግምባር ቀደምነት ያስተባበረውና የመራው ሁከት፤ በእግዜብሄር ቸርነትና ጥበቃ የረባም ንብረት ውድመት ወይንም ምንም አይነት የሕይወትም ሆነ አካል ጉዳት ሳይፈጠር ቀርቶ ሰይጣናዊ እቅዳቸው ለመክሸፍ ቢበቃም ጠባሳው ዛሬም የኦርቶዶክስን ልጆች ያቃጥላል። ሁከት እቅድ አውጪ፣ አስተባባሪና መሪ ፣ ተዋናያን፣ በፊልም ቀራጭና አራብቶ በዓለም ዙርይ በኢንተርኔት መልቀቅና ሕዝበ ክርስትያኑን ማሳዘንና አንገት ማስደፋት እውነትም እንደ ስሙ ‘ማህበረ ቅዱስ’ ወይስ ኅማህበረ ሰይጣን’ ? የሚለውን ለአንባቢያን ግንዛቤ እንተወዋለን።

ከዚህ ወጣ ብለን ደግሞ መነጋገሪ የሆነው የ240 ሺህ ዶላር ለጋሹ ይመለስልኝ ብለዋል ተብሎ በሰሜን አሜሪካን ወገኖቻችን መካከል መነጋገሪያ የሆነው ጉዳይ ነው። ስጦታው መደረጉን በእርግጥ ተረጋግጧል። እንግዲህ ለጋሹ የንግድ ድርጅት ሆኖ ተለጋሹ የግብረ-ሰናይ ድርጅት ለተቀበለው የንዋይ ድጎማ ምንም አይነት ቅድመ ውል የሚያስገድደው እስከሌለ ድረስ ባሻው መንገድ የድርጅቱን መርሆ በተከተለ ጥቅም ላይ የማዋል ሙሉ መብት አለው። ስለዚህም ቀደም ብለው የሰሜን አሜሪካን የኢትዮጵያን አመታዊ የእስፖርትና የባሕል ዝግጅት አመራር ውስጥ ከነበሩና የግል ጥቅም የቀረባቸው የፈጠሩት እንጂ ምንም አይነት የሕግ ጭብጥ የማይገባው አሉባልታ ብቻ ይሆናል የሚል ግምትን አሳስቦናል። በንግድም ሆነ በግብረ-ሰናይ ድርጅት የሚተዳደሩ ሁሉ ግብር ሰብሳቢው አካል ያስቀመጠውን ሕግ በመከተል ሁለቱም ወገን በተፈቀደላቸው የጊዜ ገደብ  በመጠቀም ወጪና ገቢያቸውን አስታውቀውል የሚል እምነት ስላለን፤ ግርግር ፈጥሮ ለመቀራመት ያሰቡ ይታቀቡ እንላለን።

ይህ አይነቱ አሉታን የሚያመጡ ሥነ-ምግባሮች ለተቋሞች እክል በመሆን የውስጥን አለመግባባት አልፎ ሕልውናቸውንም እስከማጣት አድርሷቸዋል። አንዳንዶችም በማዕበሉ ተውጠው ለመትረፍ ትግል ላይ ሲሆኑ ከነዚህ ውስጥም የዳላሱ የኢትዮጵያ መረዳጃ ማህበር ሲሆን ወይ በቅርቡ ሰምጦ ይጠፋል አሊያም በእድሩ ይተካል፣ ይህንን ቢያልፍ ደግሞ አብቦ ጤናማ ድርጅት ይወጣዋል። ከማዕበሉ ለጊዜው ተርፎ የየብሱን ጠርዝ የጨበጠውና ከማዕበሉ እየራቀ ያለው ደግሞ የዳላስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ደብረ ምህረት ቅዱስ ሚካኤል ካቴድራል ደብር ነው። ይህ ክስተት በዙ ተመሳሳይ የኢትዮጵያንና ትውልደ ኢትዮጵያን ተቋማት በሰሜን አሜሪካ ይስተዋላል። ቅንነት ጠፍቶ በተንኮል፣ ምቀኝነትና ግለኝነት ከተተካ ውጤቱ መልካም አይሆንም።

ለማጠቃለያ ከጁን 7 እስክ 9/2011 በዳላስ የኢትዮጵያ ተዋህዶ ኦርቶዶክስ ደብረ ምህረት ካቴድራል ደብር ለመጀመሪያ ጊዜ በሰሜን አሜሪካ ውስጥ በታሪክነቱ ታላቅ ሥፍራን የሚይዝና ለኢትዮጵያን ፣ ለትውልደ ኢትዮጵያን ለሆኑትና ላልሆኑት ያካተተና የኦርቶዶክሳዊ እምነት ተከታዮች በሆኑ ወጣቶችን በአንድነት የሚካሄድ ሀይማኖታዊ ጉባኤ ይደረጋል። ቀዳሚት ጁን 9/2011 ጠዋት በደብሩ የሚካሄደው ቅዳሴ ለመጀመሪያ ጊዜ በእንግሊዘኛ ቋንቋ እንደሚሆንና ትምህርቱም በተመሳሳይ መንግድ እንደሚስተናገድ አብሮን የደረሰን ዘገባ ይገልጣል። ከተሳታፊዎቹ መካከል የግብፅ፣ የግሪክ፣ የኦሬንታል፣ የህንድ፣ ወዘተ….እንደሚያካትት ተረድተናልና። ላዘጋጁ ደብርና ምዕመን እንኳን ለዚህ አደረሳችሁ ስንል ፤ ለተሳታፊዎችም የመልካም መተዋወቂያና ለወደፊቱ ለሚኖራቸው ሕብረት መሠረት መጣያ ወቅት እንዲሆን ምኞታችንና ፀሎታችን ነው። የአንድ እምነት ተከታዮች ሆነን ነገር ግን በአባቶች መለያየት ምክንያት እራሳችንን ከክርስቶስ እምነት መለየት እንደማይቻልና እርሱን ብቻ አምነን ከዚህና ከተመሳሳይ ጉባኤ እራስን ማገለልን ብሎም ከበረከቱ አለመሳተፍና አልፎም ማብጠልጠል ፍጹም ይለያልና ከክርስቶስ ይልቅ ለአባቶች ያደሩት እራሳቸውን ይመርምሩ እንላለን።

ያስተማረን የመከረን በዚህች ገጽ ላይ ከብዕራችን ጫፍ የጨመቅነውንና ከሌላም የቀላወጥነውን አዋህዶ ለናንተ ለመቸር የፈቀደውን እግዜአብሔር ለገናናው ስሙ አሁንም ክብር ምስጋና ይሁን። አሜን።

እርሶስ ምን ይላሉ?  

Friday, June 17, 2011

እርሶስ እንደኛ እንባዎ ታብሷል?

የርሶ ብዕር አስተያየት ተሳትፎ ሕብረተሰባችንን ይጠቅማል ያሉትን አይንፈጉን ገንቢነቱ ቦታ ይኖረዋልና!

ማሳሰቢያ፡ ይህ ገጽ የተዘጋጀው የተለያዩ የኅብረተሰባችንን ሀሳብ ለመለዋወጫ እንጂ ለሚሰጡት ማንኛውም አስታየቶች በማንኛውም መንገድ ተጠያቂ አይደለም። ጉግል ድርጅትም ኃላፊነት አይወስድም። ኃላፊነቱ በሙሉ የአስታየት ሰጪው ብቻ ነው።


እርሶስ እንደኛ እንባዎ ታብሷል?


እንደምን ሰነበታችሁ? እንኳንም ለሰኔ ሚካኤል በሰላም አደረሰን። አሜን አሁንም ቸርነቱ ለማያልቅበት ለልዑል እግዜአብሔር ክብርና ምስጋና ይሁንልን። ከቀን ወደ ቀን ብሎም ለዳግም አመቱ ላደረሰን እንዲህ በዋዛ እንዳልሆነ ፣ ሕሊና ያለው ሁሉ ያስተውል። ለኛ እንባችንን አብሶታልና የናንተስ? ብሎ በጥያቄ የጀመረን የዳላስ ቅዱስ ሚካኤል ሠይፍ አባልና የገጻችን ታዳሚ ነበር።

የተወደዳችሁ ውድ ወገኖች! እኛም በፈጣሪ ሥራ እየተደነቅን ተዐምሩን እየመሰከርን ለቅሷችንን እያበስን ታላቅ ምስጋናን እናቀርባለን። ከምንጫችን በቀረበልን የትላንትናው የዳላስ ቅዱስ ሚካኤል ደብር የሰኔን ሚካኤል ክብረ በዐልን አስመልክቶ የጀመረው ታላቅ ጉባኤ፤ በባዶ አዳራሽ ውስጥ የተጋበዙት እንግዳ መምህር ሳይገኙ፣ ዘማሪ ዘርፌ በሌለችበት ፣ ማንም ምዕመን ሳይሳተፍበት የከሰረ ጉባኤ ነው የሚሆነው። እኛ ከሌለንበትና እኛ ካልመራነው ምንም አይሳካም። በማለት ሌላውን የሚንቁ ፣ በቁጥር 10 የማይሞሉና አጃቢዎቻቸው በቁጥር 20 ውስጥ የሚሆኑ፣ ከውስጥ ሆነው ደብሩን የሚያውኩ ፣ ባለፈው 2 የአባላት ጠቅላላ ስብሰባ ላይ ብቻቸውን የፈጠጡ፣ ያለውንና ሙሉ አባላት የመረጡት ድንቅዬ ስራዋችን እየከወነ ባለው የደብሩ ቦርድ በቅናት የተቃጠሉ፣ አላሰራም በማለት ዝባዝንኬ ወረቀት እየፈረሙ የደብሩን ስራ እንዳይሰራ የሚያስቸግሩ፣ ደብሩን ለግል ጥቅምና ዝና የሚሹ፣ እነርሱም ሆነ ቤተሰቦቻቸው ባለመመረጣቸው ያኮረፉና በትላንትናው ጉባኤ ላይ አለመገኘታቸው፣ ወዘተ….. በረከቱ ላመለጣቸው እነዚህ ወንድሞችና እህቶች ፈጣሪ መክሮና አስተምሮ ይመልሳቸው ዘንድ እየጸለይን ነውና እናንተም ተሳተፉ ብሎ ያቀረበልንን ጥሪ ተቅብለን ፤ እኛም አጽራረ ቤተክርስትያንን አስታግስልን፣ የተቀበሉትን ወሥጋ ደም በውስጣቸው ይሰራና ያንተን መንገድ እንዲጠብቁ ያድርግልን ፣ ምሕረትንም ፈጣሪ ይስጥልን። አሜን።

ትላንት የተጀመረው ታላቅ ጉባኤ፣ ከዚህ በፊት ታይቶ የማይታወቅ ልዩ የሆነና ተሳታፊዎቹ ሁሉ የተባረኩበትና ትልቅ ትምህርትን ያገኙበት መሆኑን ምንጫችን ሲጠቁመን፣ በተለይም ቅን ስለመሆን፣ በእምነት ስለመቆምና ማንኛውንም አይነት ፈተና እርሱን ይዞ መወጣት እንደሚቻል ነው። ይኸውም ባለፉት ጥቂት አመታት ደብራችሁ በወጀብ ውስጥ ማለፉንና ዛሬ የደረሳችሁበት አስመልክቶ በእምነት፣ በጾምና በጸሎት ፈጣሪን ይዛችሁ በመጽናታችሁ  መወጣታችሁንና ትላንት ብቻ ሳይሆን ዛሬም ለሚያውኳችሁ እንዴት ሁኔታዎችን እንደምታስተናግዱ መሆኑን ያጫበጠ እንደነበር ነው። ይህ ጉባኤ እስከ እሁድ ምሽት እንደሚቀጥልና ቀዳሚት ጠዋትም በታላቅ ሥርዐት የቅዱስ ሚካኤል በዐለ ንግሥ እንደሚደረግ አብሮን የደረሰን ዜና መሆኑን እንገልጻለን። የዚህ ጉባኤ የተሳታፊው ቁጥር ከተጠበቀው በላይ መሆኑንና ምንም አይነት የተጋነነነ ማስታወቂያ ያልተደረገለት በመሆኑ ሌሎች በጉባኤ ስም ከሚያዘጋጁት ለምን የተለየ እንደሆነ መልሱን ለአንባቢያን እንተዋለን።

ከዚሁ ወጣ ስንል ደግሞ ካካባቢያችሁ ከደረሰን የመረዳጃ ማህበር ምንጮቻችን መካከል፤ ሰሞኑንን ከቅዱስ ሚካኤል ደብር ቦርድ ደብዳቤ ያስገቡት ግለሰቦች ለመረዳጃው ማህበርም እንዳስገቡ ነው። አዲስ የተመረጡትንም አመራሮችን ለማዋከብ ሆነ ብለው ስራ እንዳይሰሩና በቅርቡ ሊካሄድ የታቀደውን የኢትዮጵያ ቀን ለማደናቀፍ እንደሆነ የሚታወቅ ነው። ሌላው ያናደዳቸውና ጥቅማቸው የተነካባቸው በመህበሩ ስም የተቀጠረችና በወር ከ2600 ዶላር ያላነሰ እየተከፈላት ነገር ግን ቤሮውን ለሚጋሩት ግለሰቦች ስልክ በመመለስና የነርሱን ስራ በመስራት እንጂ ለመረዳጃው የምታበረክተው ባለመኖሩ ፣ አመራሩ ጉዳዩን በጽሞና በመመርመር የስራ ሰአቷን በመቀነሱ ጥቅማቸው የተነካ አስተባብረው ማወክ መጀመራቸውን ነው። ባይገርማችሁ ይህ ገጽ በዚህ ጉዳይ ዙሪያ ቀደም ብሎ መጣፉ  አይዘነጋም። መረዳጃው በአቅሙ መሰረት መጓዝ ይገባዋል። ካለበት ቦታ በደባልነት የሚከፍለው ኪራይ የናጠጠ ነውና በውብ ሕንጻ ላይ በ200 ዎች ዶላር ያማረ ቢሮ ሊከራይ እንደሚችልና በፈቃደኛ (volunteers) ሰራተኛ ቢሮውን ማሟላትንም በቅርቡ ያደርጋል የሚል እምነት አለን። እነዚህ የሚንጫጩት የጥቅም ተጋሪዎችና በጡረታ ውስጥ ተቀምጠው የሚሰሩት የጠፋቸው ግብዞች መሆናቸውን ገጻችን በሚገባ የሚረዳው ነው። ቅንነት የሚባለው ቃል በእርግጡ ቢረዱ ኖሮ ኃይላቸውንና እውቀታቸውን አዋህደው ለሀይማኖታቸው፣ ለወገኖቻቸውና ለተተኪው ትውልድ የአቅማቸውን ቅን ሥራን ባደረጉና  ለምሳሌነት በበቁ። ያለፈውን በዚህ ገትተው ዛሬ ቅንነትን ታላብሰው ከወገኖቻቸው ተቀላቅለው ቅን በማድረግ የተሻለና የከበረን ስም ይላበሱ በማለት ገጻችን ጥሪውን ያቀርባል?

ይህንን ጥሪ ንቆና ማን አለብኝ ብሎ በዕብሪት ታውሮ በፈረሰ መረዳጃ ማህበር ስም እንዳለፈው ንጹሀን ኮንኖ የሚኖርበት ዘመን ማለፉን ዛሬም ካልተረዱት፣ እስከ ዛሬ አብረን ኖረናልና እኔ ጣቴን በእነ እከሌ ላይ አላነሳም ወይንም የእነ እከሌን ስም ጠርቼ አልኮንንም እየተባለ የተኖረበት የሀሰት ሕይወት ዛሬ አክትሟል። ወገኖቻችን ንቃተ ህሊና ዛሬ ጎልብቷልና እንደ ትላንትናው አይቶ አላየሁም፣ ስምቶ አልሰማሁም፣ ሰላም ልኑር፣ የሚባልበት ወቅት አርጅቶ ግልጽ ውይይት መጃመሩንና ላሉብን ድክመቶች ሁሉ እንዴት ማስተናገድ እንደሚቻል ዛሬ ወገናችን እየተረዳው መምጣቱን በገሀድ እያሳየው ነው። ባለፈው የዳላስ ሚካኤል የአባላት ስብሰባን ያልተገኘው ምዕመን በቃልና በስልክ የተማጸኑትን ችላ በማለትና የእነርሱን ማንነት በመረዳቱ እራሱን ገልሏል። ዛሬ ደግሞ አፉን ከፍቶ በተግባር ሊያስወግዳቸው ተዘጋጅቶ እንደጠበቃቸው በተረዱት በማለት ለዛሬው በዚህ ስንቋጭ በዐላችሁና ግባኤችሁን እግዜብሔር ይባርክላችሁ እንላለን።

ከዚህ በታች ወደ አስቀመጥነው የአባ ሰላማ ገጽ በWEDNESDAY, JUNE 8, 2011
እትሙ ያስቀመጠው የሚላመጥ አለውና ውድ አንባቢያን ጎራ ብላችሁ በማንበብ ያራሳችሁን ግብዛቤ እንድትወስዱ እንጋብዛለን ። ገጹ ለመግባት የሚቀጥለውን ይጫኑ ወይንም ኮፒና ፓሴትን በማድረግ ይጠቀሙ።
http://www.abaselama.org/2011/06/read-pdf_4347.html#more

እርሶስ እንደኛ እንባዎ ታብሷል?

እርሶስ ምን ይላሉ?

Friday, June 10, 2011

እንደ ኤሊዋ በጀርባ ወድቆ

የርሶ ብዕር አስተያየት ተሳትፎ ሕብረተሰባችንን ይጠቅማል ያሉትን አይንፈጉን ገንቢነቱ ቦታ ይኖረዋልና!

ማሳሰቢያ፡ ይህ ገጽ የተዘጋጀው የተለያዩ የኅብረተሰባችንን ሀሳብ ለመለዋወጫ እንጂ ለሚሰጡት ማንኛውም አስታየቶች በማንኛውም መንገድ ተጠያቂ አይደለም። ጉግል ድርጅትም ኃላፊነት አይወስድም። ኃላፊነቱ በሙሉ የአስታየት ሰጪው ብቻ ነው።


እንደ ኤሊዋ በጀርባ ወድቆ

Watch USCIS Director Alejandro Mayorkas and colleagues from U.S. Immigration and Customs Enforcement, Department of Justice, the Federal Trade Commission and the Texas Attorney General announce the launch of a multi-agency initiative to combat immigration services scams through enforcement, education and continued collaboration with federal, state and local government partners. To find out more go towww.uscis.gov/avoidscams

ይህ ከዚህ በላይ የተጠቀሰው አንዳንድ በወገኖቻችን ውስጥ ሲርመሰመሱ የኖሩትን የገዛ ጉዶቻችንን ለማሳሰብና ወገኖቻችንን ከሕግ ወጥ ድርጊት ተባባሪነት ስሀተት ለማገናዘቢያ ቢጠቅም በማለት ያለንን ለመወርወር ያህል ያዳዳንን በቅንነት እንጂ በሌላ መልኩ እንዳይወሰድባት ገጻችን ታበክራለች።

የተወደዳችሁ የገጻችን ተከታታዮችና ተሳታፊዎች እንደምን ከርማችኃል? እኛና እናንተን ዳግም በፈቃዱ በዚህች ገጽ እንድንገናኝ ለፈቀደ ለእርሱ ለልዑል እግዚአብሔር ፍጹም የከበረና ንጹህ የሆነ ታላቅ ክብር ምስጋና ይሁንልን። አሜን።

ጁን 21 መጥቶ ከዳላስ የወጣንበትን አንደኛ አመት ለማሰብ እየተዘጋጀን በዋዜማው ምሽት የመሰናበቻ ጥሁፍ ወርውረን እናከትማለን ብለን ከጅለን የነበረውን በናንተ ተሳትፎ ለዚህ በቅተናል። በወቅቱ በቦኒ ምንያት በቢፒ ከባሕር ወለል በታች የነዳጅና ጋዝ ማምረቻ ላይ በደረሰው ፣  በወቅቱ የ11 ሰራተኞች ሰለባ ፣ ከዚህም በላይ እሳቱን ለማጥፋት፣ የጋዝና የዘይት ፍሳሹን ለመግታትና በቁጥጥር ስር ለማድረግ፣ የተፈጠረውን የአካባቢ ብክለት ፈጽሞ ማጥፋት ባይቻልም በቁጥጥር ስር አድርጎ እራሱን እንዲያድስና ከአደጋነት ውጪ ሆኖ ለአካባቢው ሕይወት ተቀባይነት በሚኖረው ደረጃ ማድረስ፣ በእክሉ ምክንያት ሕይወታቸው የተዛበውን የአካባቢው ተጠቃሚዎችን በተመለከተ አስፈላጊውን እገዛ ማድረግ፣ ለአካባቢው አስፈላጊውን መልሶ ማቋቋም ማድረግ የመሳሰሉትን ተግባራት ወደ ኃላ ዞረን እየገመገምን የሚቀጥለውን ቀሪውን እቅድ መተግበሩ ላይ አካባቢው ይንቀሳቀሳል። እኛም እንጀራ ነውና በአጋርነት የሚጠበቅብንን እየወረወርን እንገኛለን።

እናንተም ከዳላስ ቅዱስ ሚካኤል ደብር ጋር ጸንታችሁ በመቆየት ለደብራችሁ የሚጠበቅባችሁን እያደረጋችሁ በመበርታት ለዚህ ላበቃችሁ ለእርሱ ክብር ምስጋና ይሁንልን። አሜን።  አሁንም ጽናቱን ሰጥቶ ለበረከቱ ያብቃችሁ። ለዚህ ላልታደሉትም መክሮና አስተምሮ ይመልሳቸው። አሁን ደብራችሁ ከመቼውም በላይ ስላምና ፍቅር እየነገሰበት ያለ ፣ ብዙዎች በመጸጸት እየተመለሱ መሆናቸውንና ለበረከቱም ለመሳተፍ እራሳቸውን እያዘጋጁ መሆናቸውን ከሚደርሱን መረጃዎች ብቻ ሳይሆን ራሳችሁን ዋቢ በማድረግ የምናስረግጣችሁ ቢኖር ፤ ላለፈው 2ጊዜ ተጠርቶ በነበረው አመታዊ የአባላት ስብሰባ ላይ ሳይሳተፍ የቀረው አባላት ቁጥር ‘ዝምታም መልስ ነው“ ፣ ከነማን ጋር ነው የምንሰበሰብ በማለት የሰጡትን ባለፈው አስነብበነዋል። ምንም እንኳን አብዛኛው አባላት ባሉት አመራሮች ሙሉ እምነት በመስጠቱ በሕጉ መሰረት እንዲፈጸም በማድረጉ ፣ የተገኙት ደግሞ በተቃራኒው ጎዳና የተሰለፉ ሆነው ቢገኙም በዚያ መልኩ ሳይፈረጁ ፈጣሪ ልቦናቸውን ይመልስልንና መልካሙን መንገድ ያሳይልን እንላለን። ዘግይቶ እንደደረሰን 10 የማይሞሉ ግለሰቦች አቤቱታ ለአስተዳደሩ ማስገባታቸውን ነው። እነዚህ ግለሰቦች ቅሬታቸው በሚገባ ተስተናግዶ መሰመር እንዲይዝላቸው ገጻችን ስትጠይቅ፣ አስተዳደሩም ሙሉ ጥያቄቸውን በሚገባ ተቀብሎ ያከሄደውን ስብሰባና ውሳኔ ለመላ ምዕመን ትምህርትን ይሰጥ ዘንድ በማስታወቂያ ሠሌዳ ላይ እንዳለ እንዲለጠፍ ገጻችን በትህትና ትጠይቃለች?

ከዚሁ ደብር ሳንርቅ ዳላስ በኖርንበት ወቅት አንደኛው የደብሩ ካሕን “ እኔ ካለ ቅዱስ ቁርባን አላጋባም ፣ ዝሙትን ማስፋፋት ነው“ ያሉንና በወቅቱ የእርሳቸውን ሀሳብ በአደባባይ ሲያስተጋቡ ከነበሩት ቀደምት ፊት አውራሪ ሰሞኑን ልጁን በእኚው ቄስ ነኝ በሚሉት ግለሰብ አማካኝነት ያለ ቅዱስ ቁርባን ጋብቻን በሌላ ስፍራ ሲሰጡ በወቅቱ ከተገኙት ወዳጆቻችን ደርሶናል። እኜህ አደራ የተሰጣቸውን ምዕመን ባትሪዬን ጨርሻለሁ ብለው ከቅዱስ ሚካኤል ዐውደ ምህረት ላይ ጥለው ሲኮበልሉ ወይ ገዳም ገብተውም ሆነ በጾምና በጸሎት ያለቀባቸውን ባትሪ ሞልተው በመመለስ በትነው የተውትን መንጋ ሰብሳቤ እረኛ ይወጣቸው ይሆናል አሊያም ቅስናቸውን ይፈቱ ይሆናል ብለን ነበር። 2ቱም ግምታችን አልሰራም። ነገር ግን በሚያዘጋጁት በየጥቂት ወራት ጉባኤም ያለቀው ባትሪያቸው ተሞልቶና ታድሶ ላገልግሎት የጠፉትን ይሰበስብና ይጠብቃል ስንል እንግዲህ አመት ሞልቶታል። ፈጣሪ ሁለተኛ ትላንት በቅዱስ ሚካኤል ደብር ውስጥ ያሰሙት የነበረውን አንደበት ዛሬም እንዲጠብቁና ከዳግም ስህተት ምህረትን ሰጥቶ ፣ በአባትነት ስህተት ሳይሆን የግል ስህተት ብሎ ቆጥሮ ለንስሀ ያብቃቸው። ሀይማኖታችንም ከማያምኑ ተሳላቂዎችና ከጠላቶቿ ይጠብቅልን። አሜን።

ከዚህ ፈቀቅ ብንልም ከሰሞኑ ከደረሱን ጀባ ብለን ብንለይ በማለት የሚቀጥለውን በመወርወር ለዛሬ መቋጫ ያደረግነው ብዙ ነገር አለ። አንዳንዶች ከእስር ቤት ወጥተው ዛሬም እየበረገጉ ያሉ እንዳሉ ነው። ሌሎችም በእስር ላይ ያሉና ቀጣዮችም በራቸው እየተንኳኳ ያሉ ይገኛሉ። በኢንሹራንስ ፍሮድ፣ በሞርጌጅና በኢምግሬሽን ሕገወጥ ጥቅም ላይ ተሰማርተው የነበሩት መካከል ከውጪና በማረፊያ ቤት ያሉት ምንም ያደባባይ ሚስጥር ቤሆንም የእያንዳንዳቸውን ማንነት ከመግለጽ ለጊዜው ብንቆጠብም ፤ የሕጉ ሥርዐት መስመሩን መያዝ ስላለበትና በዚያው መቋጨት ስለሚገባው ነው። ከዚሁ ጋር በጠረቤዛ ስር ያለ ሙያ ስራ ፈቃድ የንግድ መደብሮችን ሁሉ ሲደልሉና ሕገ ወጥ ጥቅም ያጋበሱትን ቀዳዶችንም ያካትታል። የዳላስና ፎርትዎርዝ የኢትዮጵያን መረዳጃ ማህበርም እድሩን በተመለከተ ተራ መዝገቡን እየጠበቀ መሆኑን ከሚደርሱን ጥቆማዎች ለመረዳት በቅተናል። ቀደም ሲል መረዳጃው ማህበር ፈርሶ በነበረበት ወቅት በስሙ ሕገወጥ ስብሰባና ውሳኔ ብሎም ገንዘብ ስብስብ ሁሉ ሲደረግ እንደነበር ስንቶቻችሁ ታውቁ ነበር? በዚህ ገፅ መረጃውን ለመለጠፍ የኮፒ መብት ስለሌለን የዲኤፍ ደብልዩ ኢትዮጵያ ኮሚኒቲ ብሎግ የለጠፉትን በዚህ አድራሻ ገብታችሁ አንቡት። http://www.dfwethiopiancommunity.blogspot.com/
እንግዲህ በወቅቱ ሰብሳቢና አሰባሳቢ፣ ከሳሽና አስከሳሽ፣ ጁሪና ዳኛ የነበራችሁ፣ ገንዘብ ሰብሳቢና ተካፋይ ካላችሁ ህሊናችሁን አስተካክላችሁ የወሰዳችሁትን መልሳችሁ የበደላችሁትን ካሳም ሆነ ይቅርታ ተቀብላችሁ ወደ ቅን መንገድ ትገቡ ዘንድ ዛሬም አልመሸም። ሌሎችም በሳህን ከመቶ ዶላር በላይ እየተከፈለላችሁ በመረዳጃው ማህበር ገንዘብ በመጋበዝ የተመገባችሁና የተሳተፋችሁ ሁሉ ንስሀ መግቢያችሁ ዛሬ ነው። መረዳጃው ሲቋቋም ለተቸገሩት ውገኖቻችንን መርጃ እንጂ ለዝና ያለውን ጥሪት በጥቂት ግለስቦች ጥቅም ሲባል መማለያ አልነበረም። በተለይም 4 ግለሰቦች ሕብረተሰባችን አንቱ ያላቸውና በመረዳጃው ማህበር ስም በየጊዜው ገንዘብ ከቻርቲ ድርጅት እየተቀበሉ የሚካፈሉት እነማን እንደሆኑ ታውቁታላችሁ። ገጻችን የነዚህን ግለሰቦች ስም በየጊዜው ስትወቅስ ከርማለች ዛሬ ህሊናቸውን መርምረው የበደሉትን ወገኖቻቸውን ይቅርታ ቢጠይቁ ፣ እኛም ብዕራችንን በገታን። ጉዳቱ ተፈጽሟል። ከውጤቱ ጋርም እየኖራችሁ ነው። እንዳይደገም ማድረግ እንጂ፣ እንዚህ በጥቅም ታውረው ከስህተት የወደቁትንና በዕድሜ የገፉትን ለሰሩት በደል ሕግ ይዳኛቸው በማለት ለመረዳጃው ማሕበርም ሆነ ለተጠቃሚው ሕብረተሰብ የሚጨምረው ሳንቲም የለምና የራሳችን የቤተሰብ ጉዳይ በማድረግ በአስቸኳይ ይቅር ለእግዜአብሔር መባባሉን ገጻችን ስታሳስብ፤ ይህን ሳያደርጉ ቀርተው ጉዳዩን ሕግ ከጨበጠው የሚዳኘው ከክልል እስከ ብሔራዊ ደረጃ ባሉ የሕግ አንቀጽ መሆኑንና ውጤቱ ሁላችንንም አንገት የሚያስደፋ ይሆናል። ከዚያም አልፎ ወደፊት ለወገኖቻችን እርዳታን ለሚያደርጉ ግለሰቦችና ድርጅቶችም አሉታን ይፈጥራል በማለት ገጻችን ትሰጋለች።

ውድ ወገኖች፣ ዳላስ በነበርንበት ወቅትና ከወገን ለመደባለቅ በምናጠናበት ጊዜ ያየነው ቢኖር ብዙ ችግረኛ መኖሩንና መረዳጃው ማህበር አንድም ሲረዳ አለማስተዋላችንን እንጂ ወደ ቅዱስ ሚካኤል ደብር በማምጣት ግን ንዋይ ሲለመንላቸው ከነበሩት ውስጥ በአሀዝ ለመቀመር ቀርቶ አደረገ ተብሎ ለናሙና የሚበቃም አይደለም። አንዳንዶች በምግባራቸው ሲኮነኑና በተሰጣቸው አደራም ሆነ በቡድን ተደራጅተው ሳይመረጡ ፣ በወገኖቻችን ችግር መጠቀሚያና የኑሮ ምንጭ ማስገኛ በማድረግ ክቡር ስምን ከማስጠቀብ ይልቅ ለግል ጥቅም ሲባል በሌላው ወገን ላይ ጉዳትን ማድረግ ከሞራል ተጠያቂነት አልፎ የሕግንም ጥያቄ ያስከትላል። ከዚያ በላይ የኮሚኒቲውንም ንፁህ አባል የሆነውን ሁሉ አሉታን ያመጣበታል። ለዋቢነት ለመጥቀስም ባለፈው አመት በሜይ 2 ዕለተ ሰንበት በዳላስ ቅዱስ ሚካኤል ደብር ውስጥ ሁካታን የፈጠሩትና ይህንኑም ምስል ቀርጸው ያራቡትን ግለስቦች ጨምሮ የፈጸሙብን በደል ከሀይማኖት አልፎ ማንኛውንም የኢትዮጵያ ትውልድ ያለውንና ኢትዮጵያዊ እንዲሁም የኢትዮጵያዊያንን ወዳጆች ጭምር አንገት ያስደፋና አስነዋሪ ምግባር ነው። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ክርስትና ዶክተሪን ከየት ቦታ የዚህን አይነት ምግባር እንኳን ሊያስተምር አይደለም ፣ ድርጊቱን እውቅና የሚያሳይበትን ለማወቅ ባደረግነው ጥናት ወይንም ላቀረብነው ጥያቄ ከማንኛቸውም ምሁራን አባቶች ልንጨብጥ ባለመቻላችን ድርጊቱ በሚገባ መወገዝ ብቻ ሳይሆን አድራጊዎቹንም በመለየት ቤተክርስትያኗ መስመር የማሲያዝ ግዴታ አለባት።

ቀደም ሲል መረዳጃ ማህበሩን ከመሰርቱት መኃል ብቅብቅ ያሉ እንዳሉ ብንሰማም በ80ዎቹ ውስጥ እንደነበረው ወደ ቀድሞ የኢትዮጵያ ተወላጆች የነበራቸውን የክብር ስም ያስመልሳሉ የሚል እምነትን እያሳደረ ይገኛል። በትግል የወረደው የቀድሞ የመረዳጃው ማህበር አመራር አመጸኛነቱን በገሀድ ያስመሰከረው ላለመውረድ ያደረገው ስርዐት አልባነቱና በጉልበት የስራ ዘመኑን በማራዘም፣ መረጃዎችን ማጥፋትና አለ ሲባል የነበረውን ንዋይ አሟጦ መልቀቅን ነበር። በየትኛውም መልኩ በበቁ የውጪ መርማሪዎች የሂሳብ መዝገቡ ተመርምሮ የማያውቀው፣ ዛሬ ጉዱ እየወጣ ላደባባይ በመብቃት ላይ ነው። ባዶ መዝገብ የተረከበውም አዲሱ አመራር ለወገኖቹ ቅንነትን ለማድረግ ሲል የለመዱት የኢትዮጵያ ቀን ምንም ቀኑ ቢያልፍ ለማክበር በማቀድ የዝግጅት ኮሚቴ ለማቋቋም ባለፈው እሁድ ከሰአት በኃላ በጠራው ስብሰባ ላይ የታሰበው ኮሚቴ መመስረቱን አብሮ የደረሰን ዜና ነበር። በዚህ ስብሰባ ላይ ከተነሱት ጥያቄዎች ውስጥ ከ40 ሺህ በላይ ወገኖቻችን ይኖራሉ በተባለበት አካባቢ ለምን ከሺህ የማይደርስ ብቻ ነው በየአመቱ የሚሳተፈው የሚሉትና ተመሳሳይ ጥያቄዎች የተስተናገዱበት ነበር። ለብዙ አመታት ይህንኑ የሚያዘጋጁትና ሁሌም ከነርሱ እጅ ያልወጣው፤ አዲሶቹ ቦርድ ያው እኛ ባልናቸው ስለሆነ እኛኑ ነው የሚለምኑ ብለው እንደሆነ ይሁን ወይንም የሕጉ ጉዳይ አድቋቸው አልታወቀም አንዳንዶቹ በየግራጁዌሽን ግብዣ በመታየታቸው፣ አሊያም እንደ ጦር የሚፈሯቸውን የወ/ሮ የሐረር ወርቅ ጋሻውን ከብዙ አመት በኃላ መገኘትን አስበርግጎዋቸው የታወቀ ነገር የለም በጣት ከሚቆጠሩት አገልጋዮቻቸው ውጪ በሙሉ የተገኘው ጉዳዩ ያገባኛል ያለው ወገን ብቻ ነበር።

አዎን የወ/ሮዋ ብቅ ማለት ብቻ ሳይሆን የእርሳቸው የአዘጋጅ ኮሚቴ ኃላፊነቱን እንዲወስዱ የቀረበላቸው ጥያቄን በመቀበላቸው ገጻችን የተቃና የሥራ ጊዜ እንዲሆንላቸው መልካም ምኞቷን በዚህ አጋጣሚ ትገልፃለች። በዚህ ተቃራኒ ከላይ የጠቀስናቸውና የቦደኑት ጥቂት ግለሰቦች በዐሉ እንዳይሳካ ዘመቻ የጀመሩ መሆናቸውን ምንጮቻችን አልሸሸጉንም። ወገኖቻችንን ለመከፋፈል የማይቆፍሩትና ለመውጣት የማይሞክሩት ተራራ አይጠፋምና ጠንቅቆ ከወዲሁ መመርመር የሚበጅ ነው። እነዚህ ቡድኖች በተለያየ ወቅት በተለያየ ስምና ድርጅት የዳላስን ወገኖቻችንን መጠቀሚያ በማድረግ አመታትን አስቆጥረዋል።  ዘና ብለውም ይህንን ምግባራቸውን ሲከውኑ ክድርጅት አልፈው ተመሳሳይ ተግባር አጋጣሚን በመጠበቅ በደብር ላይ አነጣጥረው ተነሱ። በመጀመርያ ደብር ለመያዝ ማህበረ ቅዱሳንን መምታት፣ ቀጥሎ በምዕመን፣ በቀሳውስትና በቦርድ ተመራጮች መካከል ከፋፍሎ ማሸበር። በመረዳጃው ማህበርም ውስጥ በያዝነው አመራር በመጠቀም መከፋፈልን ማስፋትና በተለያዩ የፖለቲካ ድርጅት ስም ውስጥ በመካተት መረባችንን  ማስፋት በማለት ነበር የተጀመረው። ነገር ግን ክፉኛ የተቆጣው እውነተኛው ምዕመን አንድ በመሆን በፀሎትና በፆም በመታገዝ እንደ አመጣጣቸው እየመለሳቸው ይገኛል።

እንደ ኤሊዋ ሲንቀረፈፉ ያለሙትንም በሚሊዮን የሚቆጠረው ዶላር ከሚካኤል ደብር አጡት። በየፖለቲካና በግብረ ሰናይ ድርጅት ውስጥ ከየተሰገሰጉበት እየተፈነቀሉ ወጡ። ከሁልም በላይ ጠቅላይ መምሪያቸው የሆነውን  የመረዳጃ ማህበርን በትረስቲ በማዋቀር እድሜ ይፍታህ ምኞታቸውም ነጠፈና ከመረዳጃ ማህበሩም እየተመነቀሩ ይገኛሉ። እንግዲህ እንደ ኤሊዋ ጉዞ ዘና ብለው ባይዙት ኖሮ ዛሬ ያሰቡት ተሳክቶ ላገልግሎታቸውም የተገባላቸውን የ52ቱ ነጥብ ተሸላሚ ባደረጋቸው ነበር ። ነገር ግን በምን ጥፋቷ ድንጋይ እንዳለበሳት ባንጠይቅምና ምን በጀርባዋ እንዳጋለላት ባይነገረንም ፤ 4 እግሯ ብቻ በጀርባዋ ተንጋላ ብታወራጭ እንደወትሮ የትም መንቀሳቀስ እንዳልቻለች ነው የተረዳነው። አንገቷንም አውጥታ ለማየትም ማጅሯቷ ጭንቅላቷን መሸከም የቻለም ባለመሆኑና የሷም ቢጤዎች ከሩቁ ብቻ የሚያላዝኑ ሆነው መታየታቸውን በጣሙን እንድንመረምን የሚከጅለን። በወቅቱ ፈጥነው ፈጥመው በነበር ነበር። አሁን ግን የበደሉትን ይቅርታ የሚገባውን ሁሉ ጠይቀውና ከፈጣሪያቸው ታርቀው የተቀረ የዕድሜ ክፍላቸውን ለማጣጣም ያብቃቸው። እኛንም  ሆነ እናንተን እንደ ኤሊዋ በጀርባ ወድቆ ከመንጋለል እንዲሰውረን ፈቃዱ ለሁላችንም ይሁን። አሜን።

አቶ ኩባን ለዳላስ የሚያደርጉትን በጎ ስራ እያደነቅንላቸው ቡድናቸው ለደረሰበት ደርጃ ለእርሳቸው፣ ለቡድናቸውና ለደጋፊዎቻቸው እንኳን ደስ ያላችሁ! ለቀሪውም ግጥሚያ በለስ በናንተ ይሁን እያልን ለዛሬ GO MAVERICKS
GO እንላለን።

እርሶስ ምን ይላሉ?