Saturday, April 30, 2011

…..“ ሳምንት ይቆያሉ ብለው ያላሰቡን የቦርድ አባላት….’

የርሶ ብዕር አስተያየት ተሳትፎ ሕብረተሰባችንን ይጠቅማል ያሉትን አይንፈጉን ገንቢነቱ ቦታ ይኖረዋልና!

ማሳሰቢያ፡ ይህ ገጽ የተዘጋጀው የተለያዩ የኅብረተሰባችንን ሀሳብ ለመለዋወጫ እንጂ ለሚሰጡት ማንኛውም አስታየቶች በማንኛውም መንገድ ተጠያቂ አይደለም። ጉግል ድርጅትም ኃላፊነት አይወስድም። ኃላፊነቱ በሙሉ የአስታየት ሰጪው ብቻ ነው።

 …..“ ሳምንት ይቆያሉ ብለው ያላሰቡን የቦርድ አባላት….’


የተወደዳችሁ የገጻችን ተከታታዮች እንደምን ሰንብታችሁ? እንኳንም ለዳግማይ ትንሣኤ በሰላም አደረሳችሁ፤ ፈቃዱ ሆኖ ሁላችንንም ለዚህ ላደረሰን ለእግዚሀብሔር ታላቅ ክብርና ምስጋና ይሁን። አሜን። የዳላሱ ደብረ ምህረት ቅዱስ ሚካኤል ካቴድራል ደብር ከምንግዜውም በላይ በታላቅ በዐል ትንሣኤን እንዳከበራችሁ ከጸሎተ ሀሙስ ጀምሮ ከከተማችሁ ገብታ ከናንተ ጋር የከረመችው የገጻችን እድምተኛ አካፍላናለች።

አሁንም እስከ ዳግማይ ተንሣይ እንደምትከርምና ሰፋ ያለ ዘገባ ደብሩንና ባጠቃላይ ወገኖቻችንን አስመልክቶ ወደፊት እንደምታካፍለን ተስፋችን የጎላ ነው። በተለይም በበዐሉ ላይ ከመቼውም ጌዜ የበለጠ ቁጥር ምዕመናን መሳተፉንና በአዲስ ልብሰ ተክህኖ ባጌጡ ካህናት የተካሄደው ግልጋሎት ከአዲሱ ዝርግፍ መብራት ጋር በጣም የደመቀ መሆኑንን ከህታችን ተረደተነዋል። አዲስም ሆኑ የቆዩት የወገኖቻችን የክርስትና እምነት ቦታዎች ሁሉ በጥሩ ሁኔታ መከበሩንም አልሸሸገችም።

በሌላ በኩል ደግሞ የቄስ ሽታ መሰናበትና በዚያው አካባቢ የተያያዘው ዘገባዋ ብዙ የሚላመጥ ስላለው እንደ አመቺነቱ ወደፊት የሚቀርብ ሲሆን፣ የዳላሱ ሚካኤል አስተዳደር ተመረጭ ጠሀፊና ሚስታቸው የሌላ(ዲቪ ጊዮርጊስ) ቤተክርስትያን ቦርድ አባልነት፣ ይኸው ቤተክርስትያን ከሌላው ጊዮርጊስ ጋር ውህደት፣ ወደ አባ ጳውሎስ ጎራ መግባት የመሳሰሉት ዘገባዎችን ከፊታችን አቆይተን ወደ መርዳጃው ማህበር በመዞር ከዚህ በፊት ተፈራወርቅና በትሩ የተመራውንና መረዳጃ ማህበር ፈቃዱን በማብከን በስማቸው ለማዞር ያደረጉትን ሴራ በወ/ሮ የሐረርወርቅ ጋሻው በመጋለጡ በሳቸው ላይ የተከፍተውን ዘመቻ የቅርብ ትዝታ መሆኑን ለሁላችሁም ግልጽ ነው። የወ/ሮዋ ጥቅም ፈልገው ሳይሆን አስቀድመው የደረሱበትና ሲወለድ ጀምሮ የተንከባከቡት ድርጅት ጭምር በመሆኑ ነው። አጋሮቻቸው እነ ዘውገ በወቅቱ እያወቁ በሌለ ድርጅት ስም እየጠሩ በራዲዮ የደሰኮሩት ዛሬ ምን ይበሉ?

የኢህአዴግ ልዑካን በመጡበት ጊዜ ከተቃዋሚዎች ተለይተው ዘውገና በትሩ ፊትና ኃላ ሁነው በጓሮ በር በተኮላ መኮንን aka ተኩላው አማካኝነት ለመግባት ሲሞክሩ በፖሊስ መጀመሪያ የተጋለጠውና ስለመታሰሩም ምንም መረጃ ያልተዘገበለት እንደ ታጋይ አድርጎ በሬዲዮ ያቀረበው፣ ሰሞኑንም እንደጀኔዎችና አበበዎች ለበትሩ ታጋይነት የጀመሩት ዘመቻ፤ የስብሰባው ምሽት አብረው ለምን ከልዑካኑ ጋር የእራት ምሽት አሳለፉ? አዲሱ መረዳጃ ማህበር አመራር ዘውገና ስጦታው የተባሉትን የኢህአዴግ የውስጥ ቅጥረኞችን ከራዲዮ፤ እነበትሩን ከሕንጻ ኮሚቴው ባስቸኳይ ማስወገድ አለበት።  

ሌላው ተኩላው ዘሬ በግላጭ ከሳሽነቱንና የመረዋ ቦላጊነቱን ባደባባይ አስቀመጠ። ሲጥፈው …..“ ሳምንት ይቆያሉ ብለው ያላሰቡን የቦርድ አባላት….’ ብሎ ። እራሱን እንደ ገለልተኛ አድርጎ ዋሽቶ መክረሙና በተለያየ የብዕር ስም መጠቀሙ እኛ ያልነውን አርጋገጠ። የጋንት 44 አባል በኃልም ጋንት 1 አባል በመሆን በተደረገው አፈና ፣ ሰቆቃዊ ምርመራና ግድያ በኢሕአፓ ውስጥ የፈጸመው ቡድን ነህ ስንለው፣ እኔ ኢሕአፓ አይደለሁም ሆኜም አላውቅ ያልክ በሕይወት አበጀ ቢመሰክር ምን ምድር ትዋጥህ? 10 ሳንቲም ለሚካኤል ለስኳር የማትል ገብትህ ዘኬ ስትዝቅ ምን አይነት ሆድና አእምሮ ይኖርህ? አባል ያልሆንክበትን ደብር በሀሰት ከሳሽነት ሲገርመን ያለስራህ ገብተህ ንብረት ቆጣሪነትህ ለምንድን ይሆን? ባንድ ወቅት የጌቶችህ ጌታ መለስ ዜናዊ መፍረስ ካለበት ደንበልም ይፈርሳል ያለው ገና ባዲስነቱ ነውና እንደ አስፈላጊነቱ ሁሉም ይሻሻላል። ከወደድከው ገራዥ ሴል ላይ ጠብቀህ መብራቱን መግዛት ትችላለህ። ቲቪውም ቢሆን ከዋናው ደህንነት መቆጣጠሪያ ቤሮው ውስጥ ከ10 በላይ አዲስ የተተከሉትን ምስል መቅራጫዎችን መመላከቻ ሆኖ እንደ አንተ አይነቱን አጽራረ ቤተክርስትያን የምታደርገውን ሁሉ ከውስጥም ሆነ ከውጭ ይመዘግባልና፣ የዛሬው የምላስህና የብዕርህ ሀሰት ነገ ደግሞ እጅ ከፍንጅ እንዳይሆንብህ እነ አባ ጳውሎስና ጌቶችህ የትግሪ ነጻ አውጪ ወደ ከፈቱት መካተቱ ይሻልሀል። ኸዚህ ደብር ሆኖ እንጂ አንተን ማየትም የሚፈቅድ ያለም አይመስልምና ከቀባሪህና ሊደግፍ ከሚችል ወገንህ ጋር ባትካረር መልካም ነበር። ለዋቢነት ወንድምህ መስፍንን እንዴት አድርገው አስከሬኑን እንደሸኙልህ መዘንጋት ከሌላው ክህደትህና ሀሰትህ ሁሉ ይከፋልና ልቦናህን ወደ ፈጣሪ መልሰህ አስገዛ።

በመጨረሻም ከሚካኤል ሠይፍ በተጥየቅነው መሰረት የፊታችን ሜይ 4 ቀን በነጥሩአየር ደብሩ ተከሶና ተፈርዶ የነበረውን ከሳሾች ይግባኝ ብለው የጠየቁትን በዚሁ እለት በይግባኝ ሰሚው ችሎት በመገኘት ለደብራችሁ ድጋፍ እንድታደርጉ ሲጠይቁ ዝርዝሩን ከደብሩ ታገኙታላችሁ ብለዋል። መልካም እድል ለደብሩ እየተመኘን አምላክ የተሳሳቱትን ወደ እውነተኛው መንገድ ይመልሳቸው፣ ሁላችንንም በምህረቱ ይጠብቀን። አሜን።

እርሶስ ምን ይላሉ?  

Saturday, April 23, 2011

እንኳን ለብርሀነ ትንሣኤው አደረሰዎ!

የርሶ ብዕር አስተያየት ተሳትፎ ሕብረተሰባችንን ይጠቅማል ያሉትን አይንፈጉን ገንቢነቱ ቦታ ይኖረዋልና!

ማሳሰቢያ፡ ይህ ገጽ የተዘጋጀው የተለያዩ የኅብረተሰባችንን ሀሳብ ለመለዋወጫ እንጂ ለሚሰጡት ማንኛውም አስታየቶች በማንኛውም መንገድ ተጠያቂ አይደለም። ጉግል ድርጅትም ኃላፊነት አይወስድም። ኃላፊነቱ በሙሉ የአስታየት ሰጪው ብቻ ነው።

                                                ሞትን ድል ነስቶ ተነስቷልና! እኛም በእርሱ ድነናል!
                                                   እንኳን ለብርሀነ ትንሣኤው በሰላም አደረሰዎ!

Sunday, April 17, 2011

ብርቱካን መዴቅሳ

የርሶ ብዕር አስተያየት ተሳትፎ ሕብረተሰባችንን ይጠቅማል ያሉትን አይንፈጉን ገንቢነቱ ቦታ ይኖረዋልና!

ማሳሰቢያ፡ ይህ ገጽ የተዘጋጀው የተለያዩ የኅብረተሰባችንን ሀሳብ ለመለዋወጫ እንጂ ለሚሰጡት ማንኛውም አስታየቶች በማንኛውም መንገድ ተጠያቂ አይደለም። ጉግል ድርጅትም ኃላፊነት አይወስድም። ኃላፊነቱ በሙሉ የአስታየት ሰጪው ብቻ ነው።




የቀድሞ የኢትዮጵያ ዳኛብርቱካን መዴቅሳን የክብር እንግዳ በማድረግ የሰሜን አሜሪካ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፈዴሬሽን ለፊታችን አመታዊ ውድድሩ በአትላንታ ከተማ ላይ የ2011 የክብር እንግዳ በአንድ ድምጥ አድርጎ በመወሰኑ በደስታ እየተቀበልን፣ መጪው ውድድር የተሳካ እንዲሆን እንመኛለን።




Thursday, April 14, 2011

ዝንባም ዳይስፖራ!

የርሶ ብዕር አስተያየት ተሳትፎ ሕብረተሰባችንን ይጠቅማል ያሉትን አይንፈጉን ገንቢነቱ ቦታ ይኖረዋልና!

ማሳሰቢያ፡ ይህ ገጽ የተዘጋጀው የተለያዩ የኅብረተሰባችንን ሀሳብ ለመለዋወጫ እንጂ ለሚሰጡት ማንኛውም አስታየቶች በማንኛውም መንገድ ተጠያቂ አይደለም። ጉግል ድርጅትም ኃላፊነት አይወስድም። ኃላፊነቱ በሙሉ የአስታየት ሰጪው ብቻ ነው።


ዝንባም ዳይስፖራ!


አቤቱ የሠራዊት ሁሉ ጌታ የሆንኽ ፈጣሪያችን ሆይ፣ ሁሉን ቻይና ታጋሽ መድሐኒተ ዓለም ይህንን ጊዜ ፈቃድህ አድርገህ በርቀት ከሚገኙ ወገኖቻችን ዘንድ በዚህ ጦመር ዳግም ስላመቻቸህልን ለታላቁና ገናናው ሥምህ ክብርና ምስጋና ይሁንልህ። አሜን። የጀመርነውና ለመጨረስም ላቃረብኸን ፣ በዐለ ፆሙንም ጨርሰን ለትንሣኤ በዐል በሰላም ታደርሰን ዘንድ ፈቃድህ ይብዛልን። የተያዘውንና የቀረበውን ፆምና ፀሎታችንን ተቀበለን? ለሁላችንም ምሕረትና ሰላምን ስጠን? በዐለ ትንሣኤን ባርክልን? አሜን። 

እኛ በሥራ ምኸንያት ከናንተ ብንርቅም፣ የኛም ጋደኞች በሥራ ግዳጅ እርቀውን፣ ሕይወታቸውም በአደገኛ አካባቢ ቢሆንም ዘወትር ባለን ፍቅር በኢ-ሚይል ወይንም ቻት ግንኙነታችን ስንችልም በድምፅ  ለመለዋወጥ በመቻላችን ለታላቁ ጌታ ለእግዚሀብሔር ክብር ምስጋና ይሁን። የእርሱ ጥበቃና ከለላ ለእነዚህ ወንድሞች አይለይ። በዚህ አብይ ፆም በፍጡም በዚህ ጦመር ላለመውጣት ወስነን ነበር። ግዜውን በፆምና በጸሎት ለወንድሞቻችን ለመስጠት የወሰንበት ነበር። ባለፈው የመጨረሻ ጥሁፋችንም የተለየናችሁ ከትንሣኤ በኃላ ለመገናኘት ነበር። ዛሬ ብቅ ብንልም ከደረሱን ዘገባዎችና በእጃችንም ካለው ጨምረን ለማስታወስ ብቻ እንጂ ፤ በፆመ እማማት ምንም ሆነ ምን እንደማታገኙን ለማስረገጥ መሆኑን ከወዲሁ ልንጋራ እንፈልጋለን።

የዳላሱ ቅዱስ ሚካኤል ደብር ካሉት የሚካኤል ሠይፍ ወዳጆቻችን ያተረፍነው ለጆራችን ቢኖር በአዲሱ ዲያቆን አማካኝነት የሚካኤል ወዳጆች ለትንሣኤ በዐል በጋራ ያበረከቱትን አዲስ ሻንድለር መብራት ለማየት መጓጓታቸውን ነው። እኛም ሰምተን እንደዳዳነው እናንተም የበረከቱ ተካፋይ ለመሆን ስትሉ የሚገባችሁን እንድታደርጉ በዚህ አጋጣሚ እያካፈልን ፤ አንዳንድ በሬ ወለደ ባዮች ደብሩ ከነ እከሌ ሲኖዶስ ተደባለቀ የሚሉት የፍርድ ቤቱ ጉዳያቸው ኪሳራ ላይ የጣላቸው የአጽራረ ቤተክርስትያን መሆኑን የሚካኤል ሠይፍ ተወካይ አካፍሎናል።  በሌላ በኩልም ለትንሣኤ ክብረ በዐል ዝግጅቱ እየተጧጧፈ መሆኑንና የፊታችን ሰንበት የሚከበረውን የሆሳህና በዐል ሁላችሁም በአንድነት በመሆን እንደምታደምቁት እርግጠኞች ነን። ያማረ በዐል ያድርግላችሁ። እንዚያም አርፋጅ፣ ለነገር ብቻ የሚመጡትና በአዳራሹ ብቻ እየተቀመጡ ነገር የሚሸርቡት፣ ፈጣሪ ልቦናቸውን ለውጦ የምሕረትን መንገድ ያሳያቸው እንጂ፣ የፍርድ ቤቱ ጉዳይ ሲያልቅ የማይታረሙ ከሆነ ወይ ቦታቸውን ይፈልጉ አሊያም የቤተክርስትያኑ አገልግሎት አልቆ ወደአዳራሹ ለሕዝበ ክርስትያኑ እስኪከፈት ድረስ ይታገዱ፤ አዳራሹ ለአጽራረ ቤተክርስትያን መዶለቻና ለበረከቱ በማለት በነጻ የሚያገለግሉትን እህትና ወንድሞችን መተቺያ ስፍራ አይደለምና። በግለስቦች መልካም ፈቃድና ጉልበት ከፀሎቱ መጨረሻ በአዳራሹ ለምዕመናን የሚቀርበው ሻይም ሆነ ምግብ ሁሉ ወጪ አለውና ከማዕዱ ተሳታፊ  በእህቶች በተቀመጠው ትናንሽ ሳጥኖች የተቻላችሁን የገንዘብ ድጎማ ብታደርጉላቸው ከበረከቱ ታሳታፊዎች ትሆናላችሁ።

ቀደም ሲል ከአዲስ ከሳሽ ተራ የገባው የአጽራረ ቤተክርስትያን ቡድን  ያቀፋቸው የአንዳንዶች ስም ለመያዝ ያቀድነው ከደብሩ አመራር ጋር ስህተታቸውን በመገንዘብ ይቅርታ እየጠየቁ ያሉትንና ለመመለስ ያመለከቱ መኖራቸውን ከምንጮቻችን ስለደረሰን ነው። ከዚህ በፊትም በገነት ከበደ በተባለችው ላይ ቀደም ታሪኳን ከኢትዮጵያ ውስጥ አዲስ አበባም ሆነ ድሬዳዋ ብሎም የጂቡቲ ሕይወቷም ከዚያም የአሜሪካን ጨምሮ የደረሱን አሳዛኝ ዘገባዎችን ወደፊት የምንጋራችሁ ሲሆን፤ ግደይ ከምትባል እህታችን ጋር ስትጋራው የነበረውን ባለትዳር አፍሪካዊ በወኪሎቻችን በኩል እያፈላለግነው ስለሆነ የምታውቁ ትጋሩን ዘንድ እንጠይቃለን። ይህች ያጎረሷትን ሁሉ ነካሽ ከምትሰራበት የፓርኪንግ ሌብነት ብትፈናቀል በዚህ በተንቋቋ እድሜዋ የሥራ እድል በጠበበት በማለት እንጂ የጸሀይ ጽድቅ እድል እጅ ከፍንጅ እንዳይጥልባት ስርቆቱ፣ በተለይም በኛ ገጽ በጣሙን መመታትሽ ደርሶናል በሴት የመጨክን ሳይሆን የእጅሽን ትንሹን ብቻ ነው የሰጠሽ እንጂ አሁን አንቺ የምታሚያቸው ሁሉ በነገር የሉበትም፣ እንደ እድሜሽና እንደቆርቆሮ መንቋቋቱንና መጮኹን አቁመሽ የሰይጣን መሳሪያ ከመሆን ታቅበሽ፤ ከደብር መካሰስሽን በማቆም በንስሀ እንድትመለሽ እናሳስብሻለን።

የትግራይ ነጻ አውጪ አባልና በሕይወት የሌለው ክንፈ የተባለው ከድርጅቱ ያምታታውን ንዋይ ውስጥ በአሜሪካን መሸሸጉ የሚታወቅ ነው። ይኸንኑ ገንዘብ በመከታተል ላይ የሚገኘው ድርጅታቸው የዳላስ ነዋሪ ወደሆነውና ሙሉጌታ ወራሽ aka ቀዳዳው ዘንድ እንደነበር በሚገባ ያረጋገጡ ለመሆናቸው ለጉዳዩ ቅርበት ካላቸው ደርሶናል። ብዛቱ ለጊዜው በአኃዝ ባይታወቅም በርካታነቱ እሙን ነው። ድርጅቱም ጥንቃቄ በመላበት ሁኔታ ዘገባውን እያጠናቀቀ ሲሆን በምን አይነት ሕጋዊ መንገድ ማስመለስ እንደሚችሉ መላ እየተነበዩ ነው። ከሟቹ የአደራ ገንዘብ የበላውና ሟቹ የአንድ ቀዬ ና የትግራይ ዘር ብቻ ሳይሆን ጠለቅ ያለ ቤተሰብነትንም አፍርተዋል። የቀዳዳውን አባት ተኩሰው ከገደሉት የትግራይ ነጻ አውጪ ተዋጊ ቡድን በሥፍራው ከነበሩት ውስጥ አጁ አለበት ብቻ ሳይሆን ገዳዩም ክንፈ ነው የሚሉም አሉ። ቀዳዳውም ዳላስ ላይ አባላቸው ለመምሰልና ወያኔ ነኝ እያለ ሀሰታዊ መፎለሉን እንዲያቆም ከኢሀዴግ ማስጠንቀቂያ እንደደረሰውና ተኮማሽሾ እንዳለ አብሮን የደረሰን ዘገባ አክሎበታል። እንደዚሁም ውሸቱ የሰላቻቸውና በትምህርትም ሆነ በኑሮ ከማይመጥናቸው የማለዳ የቁርስ ተቃማሾቹ ከሆኑት የሲቲ ካፌ ደንበኞች አካባቢ፣ ፊት ስለነሱትና የትግሬውም ድርጅት ብላክ ማርኬት ዶላር ንግዱን ስለደረሱበት አንገቱን ደፍቶ መራቁን መርጦቷል። እንደዚሁም የተሰለፈበትም የአጽራረ ቤተክርስትያን ጎራም በቀዳዳነቱ እያገሸሹት መሆኑንም ዘጋቢያችን አካፍሎናል።
  
ከዚህ ወጣ ስንል ደግሞ የምንለው ቢኖር እንድንተችበት ከብዙዎቻችሁ ስለተጠየቅን ያጠናከርነውን ነው። ለምን የትግሬ ነጻ አውጪ ድርጅት የተለመደው ተቃውሞ አላገኘውም የሚለውና በዚያ ዙሪያ ያለውን ነው። አንዳንዶች እራሳቸውን እንደሚዋሹት ሳይሆን በዳላስ ከተማ ለሚገኙት ወገኖቻችን ሕብረተሰቡን አስመልክቶ ከሚዘገቡት ውስጥ ብዙ አንባቢን ካተረፈውና ከማንም ሳይወግን የተቻለውን ያህል ሲያስገነዝብና ቢሳሳትም ይቅርታን ከመጠየቅ የማያፈገፍገው ጦመራችን ሲያስረግጥ የቆየውን በገሀድ ውጤትን ያስመዘገበበት አጋጣሚ ስለነበር ነው። እንደዚሁም ለግል ጥቅም ብቻ በጎብኝዎቻቸው ቁጥር ብዛት በማስታወቂያ ገቢ ለሚተዳደርት ነባር ድህረ ገጾች ምን አጀንዳ እንዳነገቡ አንባቢያን በመረዳታቸውና ዘወትር ለገጾቻቸው ተሳታፊ የሆኑትን በትምህርታቸው የገፉም ሆነ ምንም የሌላቸው በጥንድና በተናጠል የሚያራምዱትን ምግባር የተረዱና ፀረ ሰላምና አንድነት መሆናቸውና ባለው የፖለቲካ መዛባት አጋጣሚ ተጠቃሚዎች ማንነት በመረዳት ለልፈፋቸው ቦታን በመንፈግ የሰጡት ምላሸ አንዱ ገፅታ ነው። እነዚሁ ኢሕአፓ እንደዚሁም የትግሬ ነጻ አውጪ ወይንም የሌላ ቡድን አባል አሊያም ቡችላ የነበሩና ዘመናቸው የረፈደባቸው በሕይወት በሌለ ድርጅት ስም የሚንቀሳቀሱ መሆናቸውን በመረዳቱም ጭምር ነው።  

እኛ የትግሬ ነጻ አውጪ ድርጅትንና እርሱ የወለዳቸውን ሁሉ የምንኮንነውና የምንታገላቸው የተለያዩ ነጥቦች አሉን። የሰሯቸው ጥሩ ስራዎች አሉ የሚሉን ቢኖሩ እጅጉን ከኛ ይለያሉ። አንድ ትውልድ ሙሉ ዘመን ሲያስተዳድሩ፤ የጤናና የማሕበራዊ ችግሮችን ያልቀረፉ፣ የሀገሪቱን የእድገት ጎዳና አንቀው የያዙ፣ በዘርና በጎሳ ነጣጥለው በመግዛት ነቀርሳ የተከሉ፣ የትምህርትን እድገት ላራሳቸው ብሔር ቅድሚያ የሰጡ፣ የዲሞክራሲ ጎዳናዎችን የዘጉ፣ ተቃዋሚዎቻቸውን ሁሉ በተለያየ መንገድ እያጠፉ ያሉ፣ የንግዱን ተቋም በሙሉ በቁጥጥራቸው ሥር ያዋሉ፣ ለነሱ ብቻ ያጎበደደ ወይንም የነሱ ብቻ ብሄር ለሆነ ለይተው ዕድል የሚሰጡ፣ ወዘተ…..ማለት ይቻላል። ቀደም ሲል ኮሚኒስትና ለመገንጠል የቆመ ድርጅት እንደመሆኑ ሁሉ፤ ለኢትዮጵያና ለሕዝቧ አንዴም ቅንነት ያልነበረውና ወታደራዊውን መንግሥት በሕዝብ አመጽ ሲወድቅ የተደራጁ እነርሱ ብቻ በመሆናቸው በምዕራባዊያን ምርቃት የምኒሊክን ቤተመንግሥት ለመያዝ በበቁ ማግሥት አገርን ያስገነጠሉ። አንድ የትውልድ ሙሉ ዘመን ጨብጠው ዛሬም ሀገሪቱ በአለም ደርጃ የመጨርሻዋ ድሀና ኃላ ቀር አድርገው የያዙ፤ ብዙ እድገትና የተሻለ ለውጥን ማስመዝገብ በቻሉ ነበርነገር ግን ሁል ጊዜ ስለ አባይ ወንዝ እንዘፍናለን የሚያደርሰውንም ጉዳት እናወራለን፤ ከዘመን ወደዘመን ፣ ከመሪ ወደ አዲስ ስንል አሁን በሰሜን አፍሪካና በዓረቡ ዓለም በተጀመረው የለውጥ እንቅስቃሴ ሀሳብ ማጨናገፊያ የሚሉ ቢኖሩም ፤ ግድቡን ከልባችን የምንደግፈውና እንዲተገበር በጎ አመለካከት አለን። ይህንኑም የሚጋሩን እጅግ ብዙ ሲሆኑ ችግር ያለበት ዝምባሙ ዳይስፖራ ብቻ ነው። ምቀኝነትና ጥላቻ፣ ደም መፋሰስና ሁካታ መተዳደሪያው የሆነ  እርሱ ነው። ተቃውሞ ሰልፍ የወጣ እርሱ ነው። በምዕራቡ ሀገር ድሕረ ገጽ ከፍቶ በማስታወቂያ መተዳደሪያው ያደረገ እርሱ ነው። ልብ ካላችሁ በከተማችሁ በያለበት የፖለቲካም ሆነ የማህበረሰቡ ጉዳዮች አካባቢ ብቅ ጥልቅ የሚያበዙት እነማን ናቸው እነርሱ አይደሉምን? በህብረተሰቡ መረዳጃና ሬዲዮኑን ይዘው እየከፋፈሉ ተጠቃሚ እነርሱ አይደሉምን? በናንተው ስም ከተለያዩ ድርጅቶች እርዳታን እየጠየቁ ለግላቸው የሚያውሉ እነርሱ አይደሉምን? ባለፈው በናንተ ራዲዮ አብሬው ነበርኩኝ ያለው ዘጋቢና ታሰረ የተባለው ሽማግሌ እነማን ናቸው? በትሩ የተባለ በዚያን ሰሞን የታሰረ የፖሊስ መዝገብ የለም የማይመስል ነገር ግን ለማስመሰል። ጋዜጠኛ ነኝ እያለ በሌለው የሙያ ብቃት መለኪያም ሆነ መረጃ እራሱን የሚጠራው ዘውገስ ቢሆን አትገቡም ከተባሉ በኃላ ከተቋዋሚው ተለይተው ለምን በየጓሮው አስካሄዳቸው? ተደብቀው ለመግባት? እነዚህ በ2 ቢላዋ የሚበሉ አይደለምን? በምሽት ከኢትዮጵያ መንግሥት ከተላከው ልዑካን ጋር እራት አብሮ ሲበላ አልነበረምን ለምንስ በራዲዮው አልዘገበም?

ኸዚሁ እራት ከተሳተፉት ውስጥ ፈተና ውድቆ በሌላ ባለፈ ስም የኢትዮጵያ ባሕር ሀይል የቀደመ ተቀጣሪ፤ ዳላስም ከመጣ በኃላ በመረዳጃ ማህበር ውስጥ በተመራጭነት ሲያጨማልቅ የነበረ፣ ለትግራይ ነጻ አውጪ ቡችላ የሆነና በሬዲዮ አካባቢ ያሰማሩት፣ አሁን ደግሞ በቂ ድምጽ ሳያገኝ አጭበርብረው አስርገው ለአስመራጭነት በመረዳጃው ማህበር የዶሉትና ግርማ ንጉሴ ወይንም ግርማ ታደሰ ተብሎ የሚጠራው ይገኙበታል። ይህ ቡችላቸው ቀደም ሲል ከየመን የመጡትን የቀድሞ የባሕር ሀይል ሠራዊት አባላትን ለመከፋፈል ባደረግው እንቅስቃሴ መጋለጡ የሚታወቅና ትምህርት የሌለው በመሆኑና በጋብቻ ከጸረ ኢትዮጵያን ጎራ የሰመጠ በስውር የሚንቀሳቀስ ጠላት ነው። ፀረ ሕዝብና አንድነት የሆኑት ሌሎቹ ውሮዎች ደግሞ እንደነ ደጀኔ፣ ሰሎሞን አባተ፣ መንግሥቱ ሙሴ፣ ሌንጮ ወይንም መሀመድ፣አበበ ንጋቱና ሊሎች አበበዎች ወዘተ……እያለ ይሄዳል። እነዚህ ሀቀኛ ታጋይ መሳይ ነገር ግን ባደባባይ ተቃዋሚ መሳይ ለሕዝብ አንድነትና እድገት ነቀርሳ መሆናቸውንና ይህንኑ መተዳደሪያ እንዳደረጉት በተመሳሳይ ገጽና በኛም ሲመዘገብ ቆይቷል። ዝምባሙ ዲያስፖራ እንጂ የገባውማ በነሱ እንደማይመራ እየለየለት ነው። የነርሱ ዘመን አበቃ። ካፍንጫቸው ስር ያለውን የመረዳጃ ማህበርን ከሀቀኞችና ለህብረተሰቡ የሚጠቅሙትን አርቀው ፤ ዛሬ በግላጭ ለትግራይ ነጻ አውጪ እያስረከቡ ለመሆናቸው እያስመዘገቡ ያለው ሂደት ምላሽ ነውና ተጨማሪ ማብራሪያ እንደማትሹ በመተማመን ነው። አሁንም እነዚህ የሕዝብ ሾተሌዎችን ከመረዳጃ ማህበራችሁ ለማጥፋት በነቂስ በመውጣት በቅርቡ በሚደረገው ምርጫ በመሳተፍ ማህበራችሁን አጥሩ! የኤትዮጵያ ተወላጅነታችሁ ብቻ ምርጫውን ለመሳተፍ በቂ ነውና ምንም አይነት ቅድሚያ ምዝገባም ሆነ ክፍያ የሚጠይቅ መተዳደሪያ ሕግ የለውምና። ኸዚህ ያልጠቀስናቸው ቅጥረኛና አባሪዎቻቸው ስም አለንና እንደአስፈላጊነቱ  ወደፊት እንጋራችኃለን። በዳላስና አካባቢ ያለው የኢትዮጵያ ተወላጅ ትላንት በሀሰት የመሩትንና በዚያም የተጠቀሙበትን አጥርቶ እየለየ ለትውልድ ሀገሩም ሆነ ለሚኖርበት እንዲሁም ለወገኑ የሚበጀውን አገናዝቦ በወሰደው አቋም የተጨበጠው ዕውነታ ውጤት ነው። እነዚህ ጥቂት የሀሰት ታጋዮችና ሽብር ቀማሪዎች ከዝንባም ዳይስፖራ ጋር የተሰለፉበት ተቃውሞ የተመዘገበበት ጎራቸውን ክፉኛ መቶባቸዋል። ዝንምባሞችም ከዚህ ተምረው ራሳቸውን እንደሚያጠሩ ጥርጥር የለንም።

መልካም የትንሣኤ በዐል እንዲሆንላችሁ እንመኛለን!


እርሶስ ምን ይላሉ?   

Friday, April 8, 2011

የሀሰት ተቃዋሚና ያገኘው ጣጣ!

የርሶ ብዕር አስተያየት ተሳትፎ ሕብረተሰባችንን ይጠቅማል ያሉትን አይንፈጉን ገንቢነቱ ቦታ ይኖረዋልና! 

ማሳሰቢያ፡ ይህ ገጽ የተዘጋጀው የተለያዩ የኅብረተሰባችንን ሀሳብ ለመለዋወጫ እንጂ ለሚሰጡት ማንኛውም አስታየቶች በማንኛውም መንገድ ተጠያቂ አይደለም። ጉግል ድርጅትም ኃላፊነት አይወስድም። ኃላፊነቱ በሙሉ የአስታየት ሰጪው ብቻ ነው።


የሀሰት ተቃዋሚና ያገኘው ጣጣ!

አቤቱ ፈጣሪያችን ሆይ! ለዚህ ጊዜና ሰአት ፈቃድህ ሆኖ ከሩቅ ላሉት ወዳጆቻችን በዚህ ገጽ አማካኝነት እንድንገናኝ ላደረከው ለቅዱስ ስምህ ክብርና ምስጋና ይሁን። የተውደዳችሁ የዳላስ እድምተኞቻችን እኛ በመዳህኒዓለም ጸጋ በያለንበት ሰላም ነን።

የቅዱስ ሚካኤልም ደብር ድንቅና ውብ እያደረገ አገልግሎቱን እያበረከተ ለመሆኑ ከስፍራው የሚደርሰን መሆኑን እያስረገጥን በተለይም የሚካኤል ሠይፍ አባላትም እየተጠናከሩ ይገኛል። በአስተዳደር ቦርድ ውስጥ ፖለቲከኞች ያሰረጉትና ባለፈው አመት በጠሀፊነት ያገለገለውን አበበ ንጋቱን ጊዜው አሁን ነውና ከሀላፊነቱ እራሱን እንዲያገል ግፊት ጀምረዋልና ሀሳባቸውን እኛም እንጋራዋለን። ካልሆነም በመጪው ጠቅላላ ስብሰባ ላይ ተነስቶ ፣ እንዲለቅ መደረጉ አይቀሬ ነውና። ሌላው አንዳንድ አዛውንት አይባሉ ወይ በሰላም የማይቀመጡ ጡረተኞች ከማንም በላይ በጡረታ ገቢ እያገኙ ነገር ግን ከደብሩ የአባልነት መዋጮ ከ5 ዶላር በላይ መክፈል ያልፈለጉ፣ እንዲያውም ቆራቢ ነን እያሉ የለየላቸው ዋሾ ሌላው ሁሉ ቢከሽፍባቸው፤ ዛሬ ደግሞ እንደ ለመዱት ቄስ የማነ የተባለውን ቅጠሩት የሚል ዘመቻ ከፍተዋል አሉ። ከዚህ በፊት ቦርዱ የክፍት ሥራ ቦታ ማስታወቂያ አውጥቶ በነበረበት ወቅት መስፈርቱን ባለሟሟላት ሊቀጠር አልቻለም። የጠመጠመ ሁሉ አንድ እንዳልሆነ ሁሉ አሁንም ሚካኤል ደብር እንደ ወጣቱ ዲያቆን ያሉትን እጅግ የላቁና ከፍተኛ ግልጋሎት መስጠትና ችሎታቸውን በመተግበር ያረጋገጡትን ፤ ደብሩንና ምዕመኑን ብቻ ሳይሆን ተረካቢውንም ትውልድ አንጸው የሚይዙትን ዛሬም ይፈልጋል። ዕድሉ ቢጠብ እንኳን ባሉት ይተካል። ያ ነው የአስተዳደሩ ሀለፊነት፣ ደብሩን ማሳደግና መጠበቅ፣ የአጭርና የረጅም ጊዜ ዕቅድ አውጥቶ መተግበር፤ ለምዕመኑ የሚያስፈልገውን ተገቢ ግልጋሎት በሰፊው እንዲቀርብ ማድረግና ማረጋገጥ፤ ብቁ የሆኑ አገልግሎቶችና አገልጋዮችን መተግበር ማረጋገጥ እንጂ ሥራአጥ ጡረተኞችን እሽሩሩ ማለትን አይደለም።

በሊላው በኩል በትውልድ ሀገራችን ከምርጫ 97 በኃላ ምንም አይነት ሀቀኛ የተቃዋሚ ጎራ አለ ለማለት እየታወክን ባለንበት ወቅት ፣ የገዢው አካል ጭፍሮቹን በ16 የሰሚን አሜሪካና በ2 የኢሮፕ ከተሞች የሰደደ ሲሆን ከዚህ ውስጥ 14 በአሜሪካን ግዛት ሲሆን አንደኛው በናንተ በዳላስ ከተማ እንደሚሆን ቀደም ብለን መዘገባችን እሙን ነው። ተቃዋሚ ነን ባዮች የራሳቸውን ስብሰባ እንደሚከውኑ ሁሉ ገዢውም ዲሞክራሲ ባለበት ሀገረ አማሪካ ቢለማመደው ትምህርትን ያገኝበት ይሆናል ለማለት ባንዳዳም፤ እንደምንሰማው ከሆነ ግን ለታላቁ ሚሊኒየም ለተባለው የአባይ ሀይል ማመንጫ ግድብ የሚሆን ንዋይ አሰሳ ነው ስለተባለ ፤ ይህንኑ እውን ለማድረግ መረዳዳቱ አይከፋም። ነገር ግን በግል ጥሪ ብቻ የሚደረገውን ስብሰባ እኛም ሆን ገጻችን እንኮንነዋለን። ብልህና አስተዋይ አመራሮች ቢኖሩ ኖሮ ማንኛውም የኢትዮጵያ ተወላጅ ሁሉ እንዲካፈል በማድረግ በሩን ሲከፍቱ፤ ምን አልባትም የደህንነት ችግር ጥርጣሬ ካለ፣ እያንዳንዱ ተሳታፊ መታወቂያውን እያስመዘገበ እንዲሳተፍና የሕግ አስከባሪውም ሕግን እንዲያስከብር ማድረግ በተገባ። የመንግሥት ተወካዮችና ደጋፊዎቻቸው በስብሰባው ላይ የተጠቀሙበትን እኩይ ሰአትም ለተቃዋሚ ዕድል በመስጠት እንዲተነፍስና ሁሉም ወገን የየራሱን ግንዛቤ እንዲጨብጥ መድረክ ማዘጋጀቱ በተገባ ነበር።

በሌላ በኩል የድርጅት ሥም ብቻ ያነገቡና ከወጣትነታቸው ዘመን ጀምሮ የተቆራኛቸው በሽታ ቢኖር የአዲስ አበባ ቤተመንግስት እንጂ የጊዜው የፓለቲካ ትግል ስልት ያልቃኛቸው፤ ከወጣትነታቸው ዕድሜ ብረት አንስተው ኃይልና ደም መፋሰስን የሚያውጁ፣ አንዴ ኢሕአፓ፣ ሲፈልጉ ቅንጅት፣ ወዘተ,,,,,, አሁን ደግሞ በቃና ወዘተ እያሉ ንጹሀንን ደም እንዲፈስ የሚቋምጡ፣ ትላንት እሰየ አብርሃ የተባለውን የትግራይ ነጻ አውጪ ከፍተኛ ሀላፊና ሀገር አስገንጣይ እንዲሁም በንጹሀን ደም ተጠያቂ ጋር የገጠሙ፤ ኸረ ስንቱን እንበል፤ ነፍሰ ገዳይ ሁሉ በኮበለለ ቁጥር አንድ ከሆነ እንግዲህ ነገ መለስ ዜናዊ ሮጦ ቢወጣ ቀይ ምንጣፍ አንጥፈው የሚቀበሉ ጉዶች ሁሉ፤ ዛሬም የኢትዮጵያ ጠላትነታቸውንና የህብረት አፍራሽንነታቸውን ባላቸው የግል ጥቅም ምክንያት እንጂ ከዚያ የዘለለ የላቸውም። ትምህርት የሌላቸውም ሆነ የሚያድሩበት ሙያ አልጠቅም ወይ አልጠግብ ብሏቸው አሊያም ክፉ በሽታ የሆነባቸው ናቸው። እንጀራ መጋገሩም ሙያ ሊሞዚን መሾፈሩም ሙያ፣ ሌላውም እንደዚያው ነገር ግን ሁከትና ጥላቻ መፍጠር ሳይሆን አንድ ሆኖ ተቀምጦ በውይይት መስተናገድን አንቀበል ብለው እስከ ሆቴል አስተዳደር ድረስ በመቅረብ ኃይል የተሞላበት ማስፈራራት ማድረግና የሆቴሉን ተስተናጋጆች ደህንነትን ጥያቄ ላይ ማድረስ ሕገ ወጥ ብቻ ሳይሆን ተያይዞ የሚያስከትለው ጣጣ በሽብርተኝነት መጠየቅም ጭምር ነው።

እንግዲህ ይህን የሚተገብር ወይንም የሚያስተገብር ህሊና ጨብጦ ነው ላገር መቆርቆር? ይህ አሲምባ ወይንም የኢትዮጵያ ጫካ አይደለምና ከተጠያቂነት ማምለጥ አይቻልም። በተለይም የ ዲኤፍ ደብልዩ ኢትዮጵያ ገጽ ወይዘሮ የጠቀሷቸው ግለስቦችን የኛም ገጽ ይጋራቸዋል። ወደ ዳላስ የመጣውም ቡድን ከፈለገው ወገን ጋር በጋራም ሆነ በተናጠል የመገናኘት መብቱን ብንጠብቅም፤ ከላይ እንደጠቆምነው በሩን ለሁሉም ክፍት ቢያደርገውና ሁሉንም ቢያስተናግድ መልካም መሆኑን ደግመን ልናስገነዝብ እንፈልጋለን።

የዳላሱን መረዳጃ ማህበርን አሻፈረኝ አንለቅም ያሉትን የዳላሱ ሕብረተሰብ በተባበረ ሀይሉ ማንሳትና ይሆኑኛል ባላቸው መለወጥ ይገባዋል። ስለዚህ ጉዳይ ባለፉት መጣጥፎቻችን ብዙ ዘግበነዋልና አንመለስበትም። የውጤቱ ቀማሾች ዳላሶች ብቻ ናችሁና መልካሙን ሁሉ እንመኝላችኃለን። መልካም የትንሳኤ በአል ይሁንላችሁ።

እርሶስ ምን ይላሉ?

Tuesday, March 29, 2011

ቃል እንደገባነው

የርሶ ብዕር አስተያየት ተሳትፎ ሕብረተሰባችንን ይጠቅማል ያሉትን አይንፈጉን ገንቢነቱ ቦታ ይኖረዋልና!

ማሳሰቢያ፡ ይህ ገጽ የተዘጋጀው የተለያዩ የኅብረተሰባችንን ሀሳብ ለመለዋወጫ እንጂ ለሚሰጡት ማንኛውም አስታየቶች በማንኛውም መንገድ ተጠያቂ አይደለም። ጉግል ድርጅትም ኃላፊነት አይወስድም። ኃላፊነቱ በሙሉ የአስታየት ሰጪው ብቻ ነው።


ቃል እንደገባነው

ተወዳጅ የገጻችን ተከታታዮች እንዴት ናችሁ? በገባነው ቃል መሰረት የትግሬ ነጻ አውጪ ቅጥረኛ የሆነው የአዲስ አበባው መንግሥት ተወካዮች በከተማችሁ ላቀዱት የፕሮፓጋንድ ሥራ በ04/09/2011 ከቀኑ 2ፒ ኤም እስከ 6ፒ ኤም በዳላስ ፓርክ ዌይና በቤልት ላይን መንገድ በደቡብ ምዕራብ ዳርቻና በአድሰን ክፍለ ከተማ ውስጥ በሚገኘው በማርዮት ኮረም ሆቴል ውስጥ በሚገኘው ግራንድ ቦል ሩም አዳራሽ ውስጥ እንደሆነ ከሆቴሉ ለማረጋገጥ ችለናል። ይህ ቦታም የተያዘው በኤምባሲው ስም ለመሆኑ አብሮ የደረሰን ዘገባ ያስረዳል።

ቦታው የሚገኘው በ14901 Dallas Parkway
                      Dallas, Texas 75254
                      Tel. (972) 661-2800

ይህንንኑ አስመልክቶ በከተማችሁ የሚገኘውና የኛ ገጽ  ከሚደብራቸው ብሎጎች አንዱና የተቃዋሚ ልሳን አርጎ እራሱን የሚያቀርበው ብሎግ በገጹ ያወጣው የሚላመጥ ይኖረዋልና ጎራ እንድትሉና እንድትቃኙት እንጋብዛለን ። ለመግባት ይህንን መዛለያ ይጨቁኑ (ይጫኑ) http://www.ethiodallas.blogspot.com/
አልሆን ካለዎት እንዳለ ኮፒና ፓሴት በማድረግ ይጠቀሙ። በዚህ አጋጣሚ የዚህን ገፅ አቅራቢ በሀሳብ ልዩነት ቢኖረንም ለሚያደርገው ግልጋሎት እያመሰገንን ከብሔራዊ አጅንዳ በፊት የአካባቢ ሕብረተሰብ ባለው የመረዳጃ ማህበር ችግሮች ላይ ዝምታን በመምረጡ ትችታችን ታላቅና ባስቸኳይ መተግበር ያለበት በመሆኑ ሕዝባዊነት ከቄይ ይጀመር፣ ድምጡ ለታፈነበት መብቱ ለተረገጠበትና ለተቀማበት ቅድሚያ ይሰጠው እንላለን! አሊያ ለግል ጥቅምና ለሥልጣን ከሚያልሙት፣ መብትን ከሚረግጡት መፈረጅን ያመጣልና ይተግበር እንላለን። የዳላስ ወገናችን የጊዜው አንገብጋቢ ጥያቄ በጥቂት እብሪተኞች እየተፈጸመ ያለው ችላ የማይባል የነዚሁ የትግሬ ነጻ አውጪ ተቀጣሪዎች ተግባር ነውና ትግሉና ጽዳቱ ከቄይ መጀመር የግድ ነው እያልን ጥርያችንን በዚህ ገጻችን እናሻግራለንና መልሱን ለመተግባር እግዚሀብሔር ይጨመርልን እንላለን።

ተመሳሳይ ጥያቄና ጥሪያችን እንደዚሁ ለhttp://www.dfwethiopiancommunity.blogspot.com/
አዘጋጅ ወይዘሮ እያቀረብን ፤ በገጾ የጀመሩትን መውጋት ብቻ ሳይሆን ከዚህ በፊት እንደሚያደርጉት ባደባባይ መውጣትና በየስብስቡ ይገኙልን ዘንድ በትህትና  እንድንጠይቆት ተደጋግሞ በቀረበልን ጥያቄ መሰረት ነው። ባደረግነው ጥናት ያካበቱት ልምድና ያበረከቱትን አስተዋጾ አይናችን ስለገባ ይበርቱና መረዳጃ ማህበሩን ወግ እንዲይዝ የበኩሎን አጉሊ አስተዋጾን ያደርጉ ዘንድ የክብር ጥሪያችንን እናቀርባለን? የእርሶን ቢጤ እህቶቻችንን እግዚሀብሔር ያበርክትልን፣ ያበረታታልን። ካልጫ ሱሪ ቆራጥ ቀሚስ ይበልጣልና ትምህርት ለሁላችንም እንደምትሆኑ ተስፋችን የላቀ ነው።

እርሶስ ምን ይላሉ?

Sunday, March 27, 2011

በየፈርጁ ሲመተር

የርሶ ብዕር አስተያየት ተሳትፎ ሕብረተሰባችንን ይጠቅማል ያሉትን አይንፈጉን ገንቢነቱ ቦታ ይኖረዋልና!

ማሳሰቢያ፡ ይህ ገጽ የተዘጋጀው የተለያዩ የኅብረተሰባችንን ሀሳብ ለመለዋወጫ እንጂ ለሚሰጡት ማንኛውም አስታየቶች በማንኛውም መንገድ ተጠያቂ አይደለም። ጉግል ድርጅትም ኃላፊነት አይወስድም። ኃላፊነቱ በሙሉ የአስታየት ሰጪው ብቻ ነው።


በየፈርጁ ሲመተር

የተወደዳችሁ የገጻችን ተከታታዮች እንደምን አላችሁ? እንዲሁም የኦርቶዶክስ እምነት ተከታይ ለሁናችሁ ሁሉ እንኳን ለደብረዘይት በሰላም አደረሳችሁ!  ፈቃዱን ላደረገው ለልዑል እግዚሀብሔር አሁንም እስከ ዘላለሙ ክብር ምስጋና ይሁን። አሜን! እንዲሁ ለበዐለ ትንሣኤው በሰላም ያድርሳችሁ!  የተጀመረውን ሁዳዴ ጾም በሰላም ያስጨርሰን፣ ጥበብና ማስተዋልን፣ ትህትናና መተሳሰብን፣ ፍቅርና ሰላምን ያብዛልን፣ የተቸገሩትንና እርዳታን ለሚሹት ሁሉ ደግ እናደርግ ዘንድ ልቦናችንን ይክፈትልን፣ አጽራረ ቤተክርስትያንን ያስታግስልን፣ለዓለም ሁሉ ሰላምን ይስጥልን፣ ፍቅርና በረከቱን ያበዛልን ዘንድ ምሕረቱን ያደርግልን! አሜን።

በዛሬው ልሳናችን ከዳላስ አካባቢ ካገኘናቸው አበይት ነጥቦችን ለመሰንዘር ስንዳዳ፣ ከመስመር የወጡትንም ፈጣሪ መክሮና አስተምሮ ይመልሳቸው ዘንድ ጸሎታችን ነው። ወደ ህብረተሰቡ ወቅታዊ ሂደቶች ከመግባታችን በፊት፤ በተለይም በዳላስ ቅዱስ ሚካኤል ደብር ላይ አጽራረ ቤተክርስትያን የሆኑ ጥቂት ግለሰቦች እራሳቸውም ተሳስተው ሌሎችንም አሳስተው ከቤተክርስትያናችን ሥርዐትና ሕግ ውጪ እራሳቸውን ኦርቶዶክስ ነን በማለት ነገር ግን ኢኦርቶዶክሳዊ ተግባራትን ዛሬም በዚህ ዓብይ ፆም ሰአት እየተገበሩት ይገኛሉ። ባለፈው 03/23/2011 የፍርድ ቤት ቀጠሮ ላይ ጉዳዩን የሚያየው ዳኛ ለከሳሽ ጠበቃ የይግባኝ ሰሚው ችሎት የበየነውና ለእርሱም ችሎት የሰጠውን መመሪያ በመጥቀስ ከመቃብር ውስጥ ሞቱ የተረጋገጠለትን ሕይወት አለው ይውጣና ይታይልኝ የማለት ሂደቱን በአመክሮ መንገድ እንደጠቆመው ከስፍራው ከነበሩት ስንረዳ፤ በዚህ ዕለት እንደ ክስ ማሻሻያ ብሎ አዲስ ሁለት የተከሳሾችን ሥም አክሎ በማቅረቡ ዳኛው ደስተኛ አለምሆኑን በሁኔታው የተረዱ ታዛቤዎችን አትርፏል። ከነዚህ አዲስ ታካይ ከሳሾችም ውስጥ፡-

1ኛ/ ኃይሉ እጅጉ የተባለውን ግለሰብ ባለፈው ጥሁፋችን ማንሳታችን ይታወሳል። ይህ ግለስብ የመተዳደሪያውን ዳንኪራ ቤት ጭምር ከፍቶ ስለቤተክርስትያን ጉዳይ መወዛገቢያና የአጽራረ ቤተክርስትያን ሴራ መዶለቻ አድርጎታል። ከዚህም በተጨማሪ የነተኮላን (ተኩላው) መኮንን ክስ በገንዘብ የምደግፈው እኔ ነኝ ያለና እግዚሀብሔር በሰጠው ንዋይ መልሶ የሚወጋ ነው። እንደምንሰማው ከሆነ ዶሮ ከነዕንቁላሏ ነው የምትጣፍጥ ብሎ አለ የተባለለት፤ ኢትዮጵያ በነበረበት ጊዜ በነበረው ወዳጅነት ታምኖ ያአሁን ሚስቱን እርሱ ዘንድ ተጠግታ እንድትማር ብትላክ የገባውን ቃል ሰብሮ ልጅቱን ደፍሮ የያዘ፤ ባለበት ያመንዝራ ጠባይ ካንዲት የጥቁር አሜርካዊ እህት ጋር በመጋለጡና ለዚያ መፍቴ ሴቲቱን በገንዘብ ሚሽቱን በቁርባን በማድረግ በፍቺው ምክንያት ለጊዜው የሚደርስበትን የንዋይ ኪሳራ ቢያተርፍም ፈጣሪውን ከማወክ ያላቆመ ነው። በእውነት ለመናገር ግለሰቡ ለዚህ ደብር ቀደም ሲል ከልቡም ሆነ ለመታያ የገንዘብ እርዳታ አድርጓል ፣ ያ ግን ደብሩን አቅጣጫ የመምራት መብት አይሰጠውም። እንግዲህ ይህ ሰው እንደ ኦርቶዶክስ ተከታይ የቆረበ ለምን ሲዋሽ ከርሞ ዛሬ በከሳሽነት ባደባባይ ያውም በአብይ ፆም ? የሚለውን ጥያቄ መልስ ለአንባቢያን እየተውን ምን አለ በዚህ ዕድሜው ከፈጣሪው ባይታገል? ምን አለ ንዋይም ካለው ከአብራኩ ለወጡት ልጆቹ መደጎሚያ ቢያደርገው? ትልቋም ልጁ እስከመቼ መረጃ የሌላት ሕገ ወጥ ነዋሪ ትሆናለች፣ በዕውነት ይህን ማስተካከል አቅቶት ይሆን? አይመስለንም እንደው ……..
ዛሬ ፈጣሪ በገንዘብ እየቀጣው እንደሆነ በቅርቡ ከነ በትሩ ገ/እግዚሀብሄርና በነመስፍን ገብሬ የተጀመረው የፓርክ ሌይን ፕሮጄክቱ ከመሬት ሳይነሳ ከ200መቶ ሺህ ዶላር በላይ ያስወጣው የኮንትራት ኪሳራ አይመክረውም ይሆን? ፈጣሪ ሲቆጣ አርጩሜ ቀጥፎ እንደማይመጣ አበው አስተምረውናልና ንስሀ መድሀኔት ነው። የገንዘብ ቅጣት ቀላል ነው በቤተሰብ ውስጥና በጤና ላይ ግን የሚመጣው ቀላል አይሆንምና ፈጣሪ ሁላችንንም ከዚያ ይሰውረን።

2ኛ/ ገነት ከበደ የተባለችው ነች። በዳላስ ኑሮዋ የምትታወቀው ከሀገር ቤት ጀምሮ ሴትኛ አዳሪ፣ ትምህርቷም ከሁለተኛ ክፍል ያላለፈና አሜሪካ እስከመጣችበት ድረስ እንደ ኢሕአፓና መሰሎቻቸው ሌላ በወንጀል የሚያስጠይቃት ስም እንደነበራት ነው የሚደርሱን ዘገባዎች። ዳላስ ላይ ህገወጥ (ዝጉብኝ) የተሰኘ ቀኑን የጫትና ምሽቱን የአልኮል መቸርቸሪያ በማድረግ የምትኖርበትን አፓርትመንት ስትጠቀም መኖሯ የታወቀ ነው። ከሰከረውም ኪሱ የምትገባ አለው ከተባለም ከትዳሩ ለማፈናቀል ያላደረገችው የለም። በእውነት ቤተክርስትያኑ ውስጥ ስትታይ ንስሀ የገባችና ሀይማኖቱን ያወቀች በመምሰል ተጠግታ የድብሩን የንዋየቅድሳት መሸጫ በመያዝ እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ ያለምንም ተመልካችና ቁጥጥር ይዛው እንደነበር ከምንጮቻችን ደርሶናል። እኛም ለምን በጥቅሟ መጣችሁባት በማለት ብናሾፍም ፣ ከፍተኛ የጤና ችግር እንዳለባት በመስማታችን ፈጣሪ ጤናዋንና ሕሊናዋን ይመልስላት ዘንድ እንመኝላታለን።

3ኛ/ በብሎግ ገጹ ባወጣው መሰረት ክሱን ተቀላቅያለው ያለው በነተፈራወርቅ መሪነት ተቋቁሜ ያለሁት ለማስታረቅ ነው የሚለው አጽራረ ቤተክርስትያን ቡድን ነው። ጭፍሮቹን በተለያየ ወቅት በመላክ ደብሩን ሲያስከስስና ሲያሳውክ የቆየ ከእጅ አዙር ወደ አደባባይ ወጣ እንጂ ምንም አዲስ ነገር የለም። ቀደም ብለን በገጻችን የዘገብነውን አረጋገጠ እንጂ እራሱን እንደሰየመው አስታራቂ፣ ሰላም አምጪ፣ ገለልተኛ እንዳልሆነና የኦርቶዶክስ ሥርዐትና ሕግ እንደዚሁም እምነቱንም የተከተለ መንገድ ባልጨበጠ ጎዳና የሚዳክር አናሳ ቡድን ነው። ትምህርትና ዕውቀቱ የበራላቸው ከሆነና 03/23 ፍርድ ቤት ታዘብን ብለው እንደዘገቡት ከሆነ ዳኛው የተናገረው ገብቷቸው ነው ወይንስ ቀድሞ እኛ እንደዘገብነው ለሌላ ጥቅም የቆሙና ይህንኑ ለማስፈጸም የማይፈነቅሉት ድንጋይ ላይኖር ነውን? እነዚሁ ቅጥረኞች ደብሩን የሚፈልጉት እውነት ለኃይማኖት ነውን? እንግዲህ ፤ ኃይማኖት ከሆነ ፆምና ጸሎት ለአማኞች ሲሰራ እንጂ በአለም ፍርድ ቤት ሲመለስ አላየንምና የምትከፍሉት ዋጋ ቀላል አይደለም፣ ከላይ እንዳልነው አርጩሜ ቀጥፎ አይመጣምና ከቅጣቱ ሁላችንንም ይሰውረን እንላለን።

ከዚሁ ሳንርቅ የዚሁ ቁጥር 3 ቡድን አውራዎች በመረዳጃው ማህበር ሲፈጽሙት የነበሩትን በደል ሕዝቡ በመረዳት ሊለውጣቸው መነሳቱን በመረዳታቸው የሰሩት ተጋልጦ ወደፊት በህግ እንዳንጠየቅ በማለት ቦርድ ኦፍ ትረስቲ በማዋቀር ካልሆነ አዲስ ተመራጮች ተመርጠው እንዳይረከቡ የማያደርጉት ተንኮልና ሴራ የለም። ይህንኑ በዛሬው የራዲዮ ፕሮግራማቸው ላይ ተወካያቸው አምሃ ታምሩ የተባለው አረጋግጧል። ዛሬም ደግመን የታዘብነው ቢኖር አቅራቢው ፤ ዶክተር ሳይሆንና ማረጋገጫ ሳይኖረው ሆን ተብሎ ንጹሀን የህብረተሰቡን ክፍሎች የተለቀ ትምህርት እንዳለውና ከፍታኛ ሚና እንደሚያበርክት አድርገው በሀሰት ያጠለቁለት ካባ መሆኑን በሚገባ አረጋግጠናል። ስንቶች ለፍተው ያካበቱት የትምህርት ደረጃ እንጂ ለመንገደኛና ለአማጺ የሚሰጥ አይደለም። የጠለቀ ትምህርት እንደሌለውም ማሳወቂያ ሲተዋወቅም ሆነ እራሱን ሲገልጥ የዶክተርነት ትምህርት እንደሌለው ነው። ነገር ግን በሌለው ዕውቀት ሲጠራበት ለእውነት የቆመ ቢሆን አይደለሁም ማለት ሲገባው አስመስሎ ማጭበርበርን እንደሙያ ማደሪያ ያደርገ መሆኑን በይፋ ያረጋገጠ ነው። ባለፈው እንዳስነበብነው የመረዳጃ ማህበር ሊቀመንበር ነኝ ባዩ ተራ የነዳጅ ማደያ ሱቅ ሰራተኛ ተዳዳሪ ሆኖ እያለ አዲስ ሰው አግኝቶ ሲተዋወቅ የሚሰጠው ካርድ ግን ኢንቨስትመንት አማካሪ ነኝ ብሎ ነው። ውሻ አጣቢውም ሆነ ሱቅ ሰራተኛው በሙያው መኩራትና ለተሻለ ነገር እራስን በዕውቀት ማጎልበትና ሌላ መንገድን በሀቅ መጨበጥ ሲገባ በአቋራጭ ያልዘሩትን ለማጨድ ማዋረድ ብቻ ሳይሆን በህግም ያስጠይቃል እንላለን።

ሌላው በራዲዮኑ ከአስመራጭ ኮሚቴ የቀረበውና ግርማ የተባለው የነርሱ ቅጥረኛና አስርገው ያስገቡት ነው። ባለፈው እሁድ የቀረበው ሮቤል የተባለውና ቁጥር ሁለት የተባሉት ህብረት ናጂ ቡድን አባል የሆነውና አስርገው ያስገቡት የተናገረው ፍጹም ተቃራኒ ሲሆን፤ የግርማ ግን ቀደም ብሎ ባለው ሪኮርድ መሰረት መረዳጃ ማህበሩት ሲያጨማልቁና ሲወጉት ከነበሩት የቀድሞ ተመራጮች ተርታ የተመዘገበ ሲሆን ከቁጥር 2 ቡድን ጋርም አብሮ የወገነ ነው። ለዚህም ነው ማንው የአስመራጭ ተወካይ ወይንም መሪና መግለጫ አቅራቢ የሚለውን ጥያቄ መሰተናገድ ያልተቻለው። አስመራጭ ኮሚቴው የተጣለበትን ሀላፊነት በነጻነት መወጣት አለመቻሉ ከራዲዮ ምልልስ ግልጽ ቢሆንም ማንኛውም የተመሰረተ ኮሚቴ የተሰጠውን የሥራ ኃላፊነት ስርቶ በተባለው ቀንና ሰአት ለማቅረብ ዝግጁ ከሆነ የተፈጥሮ እክል ካልሆነ በቀር አንድ እንኳን ሰአት ማሳለፍ የለበትም። ተጠሪነቱ ለመረጠው እንጂ ተርሙን ለጨርሰው ቦርድ አልነበርም። የንርሱ የሆነውንም አጀንዳ ውስጥ ጣልቃ መግባት የለበትም። እነርሱን ሲመርጥ ሕዝቡ በወቅቱና በሰአቱ ሌላውን የቦርድ አጀንዳ የተባለውን በሙሉ የጣለው ስለሆነ፣ አስመራጩ የዚያ ተጽኖ ወይንም እስረኛ መሆን ባልተገባ። ታላቅና ግዙፍ ስህተት እንለዋለን። አሁንም የህብረተሰቡ ጥያቄም ሆነ ችግር በየግለሰቡ ቡና ቤት ሳይሆን የሚፈታው በአንድ ወጥ ሲሆን ነውና የቡናቤቱ ቀጠሮ ለነገር ሸራቢዎችና ድርጅት ማብከን ስራዬ ብለው ለያዙት መተው መልካም ነው እንላለን። ይኸው አስመራጭ ቡድን የጠራና ገለልተኛ የሆነ አለመሆኑን ያረጋገጠ ስለሆነ የጉዳዩ ባለቤቶች የሆናችሁ ሁሉ ግንዛቤን መውስድ የግድ ነው። ከዚህ ጋር የምናያይዘው ቢኖር ትረስቲ የተባለው ቡድን ቢቋቋም አስተዳደር ቦርድ ከመምረጥ ይልቅ የቤሮ ጉዳይ ፈጻሚ መቅጠር የሚቀል ነው። ለዚህ ያበቃን ከምንጫችን በደረሰንና እኛም በገመገምነው አዲስ የታለመውን መተዳደሪያ ደንብ ካየነው በኃላ ነው። የትረስቲው አሽከር ለመሆን የሚመረጥና የሚያገለግል ንጹህና ገለልተኛ አስተዳደር ቦርድ ማግኝት ስለማይቻል እነዚሁኑ አመጸኛና አምባገነን ምልሶ አስቀምጦ አዲስ  ወጣትና ገለልተኛ የሆኑትን ትረስቲ በለያቸው መሾምና ለሌላው ያዘጋጁትን ጥዋ ለእነርሱ መጋቱ መልካም ነው።

ከዚሁ ቀጥሎ በትላንቱ ዕለት ሁለት ስብሰባ በከተማችሁ ተይዞ ነበር። አንደኛው የሕክምና ባለሙያዋች አንደኛ አመት አስታኮ እየደረገ ባለው የወገን ለወገን አገልግሎት ነበርና በዚሁ በርቱ እደጉ ስንል፤ ሌላው የቁጥር 2 የበታኙ ቡድን ስብሰባ ነበር። ይኸው 30 የማይሞሉትን ያካተተው ስብስብ ባለው የከተማዋ ወቅታዊ ጉዳይ ላይ ማተኮሩንና የወገኖቻችን ድምጽና መብት መገፋትን በማራቅ የተደርገው የውስጥ አርበኛ ቅጥረኞች ያደርጉት ሴራ ነው። የመረዳጃ ማህበሩ አመራር አፍንጫቸው ሥር ቁጭ ብሎ የሕዝቡን ድምጽ ሲቀማ ያልቆሙ ነገር ግን ወያኔ እየተባለ አህጉር ዘለል አስመሳይ ታጋይነትን የታየበትና እንዚሁ የትግሬ ነጻ አውጪ ተቀጣሪዎች ስብስብ መሆኑ ነው።

አሜሪካ እየኖሩ ስለመብት ተከራካሪ አድርገው ካቀረቡ የሌላውንም መብት ማክበር የግድ ነው። ከዚህ በፊት እንደጠቀስነው የትግሬ ነጻ አውጪ ተቀጣሪ የሆነው የአዲስ አበባው መንግሥት ተውካዩን ስለ 5ቱ አመት የዕድገት ዕቅድ በማለት የኢትዮጵያ ተውላጆች በሰፈሩበት የውጪው አለም በሙሉ እንደአሰራጫቸው የታወቀ ነው። በዳላሱ የመረዳጃው ማህበር የራዲዮ ስርጭት ማስታውቂያ በቀረበው መሰርት ይህንኑ የተልእኮው ቡድን በ04/09/2011 በማርዮት ኮረም ሆቴል ውስጥ እንዳለው ሲያስታውቅ፣ ለማረጋገጥ ባደረግነው ሙከራ በእለተ ሰንበት ምክንያት የሽያጭ ክፍሉ ዝግ ስለሆነ አልተሳካልንም። መርጃውን እንዳገኘን ልናጋራችሁ እንሞክራለን። ነገር ግን ቁጥር 2 ቡድን ትላንት እንዳካሄደው ስብስብ ሁሉ የትግራይ ነጻ አውጪ ቅጥረኞችም ስብሰባ የመጥራትና የማካሄድ መብታቸው የተጠበቀ ነው። ያለውን መንግሥት የሚደግፍና አሊያም የእድገት እቅዱን ለማወቅና በትውልድ ሀገሩ የሚካሄደውን ግንዛቤ ለመጨበጥ የመካፈል መብቱ የተጠበቀ ነው። የተሳተፈ ሁሉ ወይንም በሀገሩ ቅሪት ማድረግ የጀመረ ሁሉ የሕዝብ ጠላት አድርጎ መፈረጅ ስህተት ነው። የፓለቲካ ልዩነቶች እንደተጠበቁ ሆነው ለሀገር ልማትና እርዳታ ማድረግ ይቻላል። እንደዚሁም ደግሞ ያለውን አስተዳደር ችግሮችን እንዲቀበልና እንዲያሻሽል መንገዶችን መቀየስና ለዚያ መታገል የሁላችንም ግዴታ ነው። አንድ ወጥ የሆነ የጋራ እቅድ ሳይጨበጥ በተናጠል የሚደረግ ሩጫ ከምርጫ 97 መገንዘቡ መልካም ነው። ብዙዎቻችን በእድሜ በገፋን ወቅት የአቅም አድማሳችንን መለካት ያቃተን ይመስል እኛ ብቻ ካልመራን ወይንም እኛ ከሌለንበት ሁሉም መፍረስ አለበት የሚል የጨቅላ ጨዋታ ያልወጡትን ወገኖቻችንን ስናይ ያሳፍረናል።


በሰለጠነ አለም እየኖርን አህጉር ተሻግረን ጠመንጃ ለመማዘዝ የረፈደብን መሰለን። ፍትህና እኩልነትን መጀመርያ ከቤታችን ከዚያም አሳድገን በኮሚኒቲያችን ብሎም በሀጉር ደርጃ እንኳን ብናደርሰው የትግሬ መንግስት ከደጁ ሳይደርስ ሊንበረከክ ይችላል። ዋናው ነጥብ መደራጀትና ሪሶርሶችን በአግባቡ አቀናጅቶ መጠቀምን ልምድ ማድረግ መጀመሩ ለኛም ሆነ ለደረሰው ትውልድ ለማስገንዝብ እንወዳለን። ከቁጥር 2 ቡድን ካካተትነው ውስጥ ደጀኔ የተባለው በትላንቱ ስብሰባ በከተማችሁ ውስጥ እየተካሄደ ላለው ወቅታዊ ሂደትና የወገኖች መብት መረገጥን በመደገፍ አስመራጭ ኮሚቴውና ቦርዱ የተስማሙበትና ያለቀ ጉዳይ ነው በማለት እርሱን ፈቅዶ ያንበረከከና ሊኣሎችም እንዲበረከኩ ያደረገ የውስጥ ጠላታችሁ ነው። ትላንትና ቅንጅት በሌላ ጊዜ ደግሞ በሌላ ስም እየለዋወጠ ሌላ ሕዝባዊ ድርጅት እንዳያብብ የሚያኮላሽ አንዱ ጸረ ሕዝብ በመካከላችሁ የሚሽሎከለክ ጉድ ነው።

ትላንትም ሆነ ዛሬ የቅንጅት ስምና ማህተም በመጠቀም የሀሰት ሰነድ በማዘጋጀት በመሸጥ መተዳደሪያው ካደረገ ቆይቷል። እነዚሁ የሀሰት የፖለቲካ ጥገኛ ጠያቂዎችን መጠቀሚያ ባደረገበት ወቅት የተማረው ሌላው ወንጀል ሥራ ቢኖር አዲስ እንደሙያ የያዘው ኢ-ሐርሞኒ አይነት የፍሮጅ ጋብቻ በማድረግ በጋብቻ የመኖሪያ ፈቃድ አስወጣለሁ እያለ የጀመረው ሥራ ነው። እንዲ አይነቱ ሞላጫ ነው እንግዲህ ከሱ የተሰለፉ ሀቀኛ ታጋዮችን አንገት የሚያስደፋ ፣ እንግዲህ እንዲ አይነቱ ነው ለራሱ ጥቅም የታወረና የመረዳጃ ማህበሩ ችግር በማጣጣል ወደ ትግሬ ነጻ አውቼጪ የዳላሱ ስብስብ ተቃዋሚ ዝግጅት ላይ ብቻ እንዲተኮር ያደረገው ለግል ጥቅሙ ነው። በእርሱ የዳላስ ጩኸት የአዲስ አበባው መንግሥት ወይ ፍንክች! እርሱ ግን ተቃዋሚ በማለት በሀሰት ገንዘብ ለመስራት ብቻ ነው። ሌላው የእርሱ ቢጤና እኩዩ የሆነው ሰሎሞን አባተ የሚሉት ቀደም ሲል በፓርኪንግ ሥራ ሲወሰልት የነበር ከዚያም በሊሞ ብሎም በሱቅ የሚተዳደር የሀሰት ታጋይ ነው። በዛሬው የራዲዮ ፕሮግራም ላይ እንደጠቀሰው ’ጠላትማ ጠላት ነው አስቀድሞ መግደል አሾክሻኬውን ነው’ ብሎ ያለውን በየትኛው ጦር ኣንዳዘመተ ባናውቅም አቋም የሊለውና ለጊዜዊ ጥቅም ያደረና አንገብጋቤ የሆነውን የወገኖቻችንን መረዳጃ ማህበር መስተካከል ሲገባው፣ ባህር ዘሎ ነገር እንደማይደርሱበት አውቆ እንደው ዘራፍ ማለት ይስብላል።

አዎን ከስብሰባው አዳርሽ ውጪ ሕግን የተከተለ ተቃውሞ መውጣት ይቻላል፣ በአዳራሹ ውስጥም ገብቶ በመልካም ክርክር እነሱንም አስረድቶ የተሰበሰበውንም አሳምኖ የስብሰባውንም አላማ ማክሸፍ ሲቻል እንዴት በሀሳብና በአቋም በመለያየት የዛቻ ድምጽ በራስ ወገን ላይ በራዲዮ ይሰነዘራል። እንደነዚህ አይነቱ ነውን ፓለቲካውን ይመራል በማለት ተስፋ የሚጣልበት ወይስ የህዝቡን አቋምና ውሳኔ ስለመደፈሩ የተስማውን ወገናችንን ትግል በመላ (በዘዴ) ማስለወጥ ነው ትክክል?    

የሕዝብን አንድነትና ትግልን የሚቦረብሩ ይጋለጣሉ!
አንባገነን የመረዳጃው ማህበር መርዎች ይወገዳሉ!
አጽራረ ቤተክርስትያኖች በደሙ ይቃጠላሉ!

እርሶስ ምን ይላሉ?