Sunday, July 31, 2011

ፍልፕ ፍሎፕ / flip-flop

የርሶ ብዕር አስተያየት ተሳትፎ ሕብረተሰባችንን ይጠቅማል ያሉትን አይንፈጉን ገንቢነቱ ቦታ ይኖረዋልና! ማሳሰቢያ፡ ይህ ገጽ የተዘጋጀው የተለያዩ የኅብረተሰባችንን ሀሳብ ለመለዋወጫ እንጂ ለሚሰጡት ማንኛውም አስታየቶች በማንኛውም መንገድ ተጠያቂ አይደለም። ጉግል ድርጅትም ኃላፊነት አይወስድም።


ፍልፕ ፍሎፕ / flip-flop

የጎረፉልን  መጣጥፎች ብዙ ናቸውና እኛም ሆን በማለት ያደፈጥነው ብዕራችን የምትጨምቀው ቀለም ደርቆ ሳይሆን በተቀጣጠለው እሳት ላይ በዚህ በጋ የድርቆሽ ሣር ላለመጨመር አሊያም እንደ ቀያችን አዋራው እስኪከስም ለሰላም ፣ ለፍቅርና ለአንድነት ባለን ቅንነት በመሆኑና ጦመሯ የተደባየውን ለመለይት ወጀቡን ስታመዛዝን መሆኑን ለመጠቆም በቅድሚያ ትዳዳለች። የተወደዳችሁ የገጻችን ተከታታቶች እንደምን ከርማችኃል? በሰላምና በጤና ጠብቆ ለጠዋት ማታ ጸሎታችን ምላሽ እያደረገና እንባችንን እያበሰ ላለለውና ለፈጠረን ልዑል እግዜብሔር አሁንም ክብር ምስጋና ይሁን! ወደፊትም እስከመጨረሻው ይሁንልን። አሜን።

ከሁሉ በፊት ያሳሰበን ሁለት ነጥብ ልንጋራችሁና ከጸሎታችሁ እንድታስገቡት የሚያስፈልግ ማሳሰቢያ ነው።
1. በአሁኑ ወቅት በትውልድ አገራችን ላይ እንዲሁም በአካባቢው አጎራባቾችን ጨምሮ የደረሰው የአየር መዛባት ከፍተኛ የሆነ የረአብ አደጋ መድረሱን የሁላችንም ግንዛቤ ነው። ምንም አይነት ምክንያትና ሰበብ ሳንይዝ የተቻለንን መርዳት ለየትኛውም ዕምነት ተከታይ የሚጠበቅበት ብቻ ሳይሆን ሰብዐዊነትም ጭምር ነው። አማኝ የሆነም ሆነ የሆነች ሁሉ ከእርዳታ ጋር ፈጣሪንም በፀሎት መጠየቅ ይገባል።
2. በሀገራችን አሜሪካን ምክር ቤት የተፋጠጡበት የእዳ ጭመራ ውዝግብን በመግባባት በቶሎ ይቋጩት ዘንድ ማሳሰብና መፀለይ ይገባናል። ምክንያቱም አሁን ያለው ምጣኔ ሀብት ቀውሱ አለምን እያናጋና ብዙዎችን ከኑሮ ሕይወታቸው ዛሬም እያናጋው ያለበት ወቅት ላይ ይኼው ሲጨመርበት ወደ ባሰ ጎዳና ይገፋዋልና የየትኛውም የፓለቲካ ፓርቲ ደጋፊና አባል የሆናችሁ ሁሉ ለምክር ቤቱ  ተወካዮቻችሁ ማሳሰብ ተገቢ ነው በማለት ገጻችን ያሳሰባትን አበይት ትኩረት ታካፍላለች።

የኛን ገጽ ለማንበብ የምትናፍቁ ከልብ የምትውዷት ወዳጆችዋ ብቻ ሳትሆኑ በኛ ዝምታም ግራ የሚገባቸውና ቀልባቸውን የሳበቻቸው ውስጥ ቅድሚያ የምንሰጣቸው በገጻችን ስማቸው የተጠቀሱት ሁሉ በምጎሳም ሆነ በነቀፊታ ሱስ ሆናባቸው እንዳለች ፀሀይ የሞቀው እውነታ ነው። ነቀፊታችን የሚመራቸው ሁሉ በገጿ ላይ ከመፋጨት ይልቅ ወደ ቅንነትና ወደ በጎ መስመር ገብተውልን ለማየት ለፈጣሪያችን የዘወትር ፀሎት ከማቅረብ አልቦዘንም። ሁላችሁም በዚህ ብትተባበርሩ ገፃችን ደስታዋ የላቀ ነው። ሌላው ወገን ደግሞ የድርጅት ሱሰኞችን ገጻችን በሰፊው አፍርታለች። በአውሮፓና በአሜሪካ ተቀማጭነትን ይዘውና እንዲሁም በኤትዮጵያ ውስጥም ያሰረጉት የትግሬ ነፃ አውጪ ምንደኞች ፣ ከኢትዮጵያ ከፍተኛ ባለስልጣናት፣ ከሊቀ ጳጳሱ ጀምሮ እንዲሁም የማህበረ ቅዱሳን የተባለው የከልት ቡድን በሀገር ቤትና በውጪ ያሉትን ፣ ብሎም የአጽራረ ቤተ ክርስትያን ቡድን ሆነው ፤ አንዳንዶችም የሀሰትና ፍሬ አልባ ግብረሰናይ በማቅዋቋም የሚንቀሳቀሱትን ያካትታል።

ከላይ እንደጠቀስነው ብዙ አስተያየቶች ቢደርሱንም ሆነ ከዝህ በፊት የኮነንነው ምግባርም ገና ዳኛው ሳይፈርድ ነበር አካሄዱን የምናስተውል። በተለይ በአእምሮ ኹከት ምክንያት የምትቸገረው እህት ቀደምትነትና እንደእርሷ ለይቶ ለሕክምና ያልዳረጋቸው ነገር ግን የጤናው እውክታን በተለይ መልኩ እየተገበሩ ያሉት ከዳላሱ የቅዱስ ሚካኤል ጋር ያላጋቸው፤ ትሁትና ታጋሽ መልአክትነቱን ሊመክረን ደገመ እንጂ በእነርሱ  እንደማይወድቅ አረጋገጠልን። ይግባኝ ሰሚው ፍርድ ቤትም ደገመልን። በዚህ ላይ የምንለው ቢኖር የደብሩ ጠበቆች በቀጥታ ይግባኝ የተባለበት ጉዳይ ፍርዱን የሰጠው የበታች ችሎት ነጥብን ብቻ እንጂ ተጨማሪ አቤቱታን እንደማያይ እንዴት መረዳት ተሳናቸው። በወቅቱ አመራር ላይ የነበረው አስተዳደር መወሰን የነበረበትና የመጀመሪያ ክስ ሲደርሳቸው ፤ የክስ ክስን አስገብተው ቢሆን ኖሮ የታችኛው ችሎት ይወስን ነበርና ዛሬ ደብሩ አዲስ የኪሳራ ክስ ለመክፈት ወደ ሌላ ጎዳና ባልተመለከተ ነበር ብሎ ያስመዘገበን የሚካኤል ሠይፍ  ከሚናለው ቡድን ተወካይ ነው።

2. ተወካዩም አያይዞ ካቀረበልን ውስጥ ፤ በተኩላውና ብጤዎቹ የተከፈተው ክስም የመጨረሻ ውስኔ ሊሰጥበት ሲጠበቅ ከሳሽ ክሱን አንስቻለሁና ጉዳዩ ይዘጋልኝ በማለት ያቀረበው መንገድ አደገኛ ስለሆነና ለሌሎችም በር የሚከፍት ስለሆነ በመመሪያ ተቀብሎ ነገር ግን ኪሳራዬ ይከፈለኝ የማለት መብቱን ማስጠበቅ አለበት። ይህ ካልሆነ የህግ አማካሪዎቹን ባስቸኳይ መለወጥ ካልሆነ ፤ አሁን ያለው አመራርን መለወጥ የግድ ይሆናል።

ሌላው ከዚህ ቀደም አስተዳደር ቦርዱ ለ2 ጌዜ የጠራው ስብሰባ አስፈላጊው ቁጥር ባለመሟላቱ መሰረዙ የታወቀ ነው። በወቅቱም በድጋሚ ጭምር የተገኙት አነዚያ ብቻ ናቸው በኦገስት 6 ስብሰባ ይጥራልን ብለው ባቀረቡት መሰረት ሲሆን አሁንም እነአርሱ ብቻ እንጂ ሌላ ክርስትያን ለነገርና ለክርክር አልፎም በእነርሱ ሊስሟጠጥ ብሎም ሊሰደብ የሚመጣ የለም። ካለእነርሱ ሀይማኖተኛ ለአሳር ፣ እንእርሱ ብቻ ለደብራችን እጣ ፈንታ አዋቂ ፣ ከዚህ ካሳለፍነው ፈተና የዶሉን እነእርሱ፣ ቆራቢም እነእርሱ፣ አስከሳሽና አካሻሽ እንእርሱ፣ ቅን አገልጋዮችን አዋኪና እንቅፋት እንእርሱ። ዛሬማ እኛ ብቻ የአሽከርካሪውን መቀመጫ ካልያዝን ሌላው መንዳት እንደማይችል ወይንም ማሽከርከ እንደማያውቅ ነው የሚያምኑ በማለት የሚካኤል ሠይፍ ተወካይ ደምድሞልናል።

ተኩላውና አጋሮቹ እንደገና ክርስትና ተነስተው ነው ወይስ የትግራይ ነጻ አውጪ አዲስ ብልሀት መመሪያ ተቀብለው ይሆን። በክርስትናው ከሆነ ደብሩን በግልጽና ባደባባይ የበደሉትን ምዕመን ጨምሮ ካሕን ይዘው መጠየቅ አሊያም ለሰይጣናዊው ምግባር ከሆነም ከፈጣሪ ያገኙታል። አሁንም በቁም እየተቀበሉት ነው። ለዚህም እንደሀገራችን አባባል ፍልፕ ፍሎፕ ያልነው’ በተለይ ተኩላው በወጣትነቱ ነበር ለትውልድ ሀገሩ ቃል ገብቶ መለዮ ያደረገ ክዶ ከኢሕአፓ የተቀላቀለ። አሜሪካ ከርሞ ኢሕአፓ ሆኜም አላውቅ ሲል በሌላ በኩል እዚያው ይልከሰከሳል። እኛ እስከምናውቅ በደብሩ መተዳደሪያ አርቃቂነት ከነግርማቸው አድማሴ ጋር ከአዲስ አበባ መመሪያ እየተቀበሉ የጣፉት በመውደቁ ያኮረፈና ልክፍቱ የተቀሰቀሰበት ትላንት ለመብቱ ነው ብሎ ከብጤዎቹ ጋር አብሮ የከሰሰውን ለምን እስከ ውሳኔ መጠበቅ አቃተው? ከታሪክ እንደምንረዳው ለመብታቸው የቆሙ እስከመጨረሻው መሰላል ይወጣሉ እንጂ እንደ እርሱና ቢጤዎቹ አያፈገፍጉም። ምናምንቴ ፍልፕ ፍሎፐር!

ሌላው ፍልፕ ፍሎፐር ደግሞ ብርሀን መኮንን aka ማክ መኮንን ነው። ሕዝብን መምራት እንደሚጠፈጥፈው ቂጣ መገለባበጥ መስሎት ይሆን የተጣለበትን ሀላፊነት ሸጦ ሲያበቃ በፈቃዱ ከለቀቀ በኃላ አማልዱኝ ብሎ ሰብስቦ መልሱኝ ማለት ምንድን ነው። ቂጣ መጠፍጠፍ ሌላ ሙያ ሕብረተሰብ መምራት ሌላ መሆኑን አላወቀምን? መረዳጃ ማህበር አመራር 101 ትምህርት የለውምን? አሁንስ በመልቀቂያ ወረቀቱ እንደተናዘዘው ሊተገብር ዘዴ ብሎ የያዘው ይኖር? ይህ ግለሰብ ባለፈው ሕብረተሰቡን ለመከፋፈል ዛሬም በሪዲዮኑ እየወጣ ያውካልን? ለማን እንደሚሰራማ በግልጽ በበተነው አይተነዋልና ለምን መለሱት? ብቻቸውን የቀሩ የእርሱ ቢጤዎች ካመራሩ ይኖሩ ይሆን? የእርሱ መመለስ ከጉዳቱ ጥቅሙ ምንድን ይሆን? የገባውንም የገንዘብ ቃል እስከ ዛሪ እንዳላስገባ ነው መረጃ የሚያሳየን ፣ እንግዲህ መጨረሻውን እዛው ለናንተ ዳላሶች እንተወዋለን።

በተለይም በዳላስ ስላለው አለም አቀፍ የምዕመን ማህበር ስለሚለውና የኢትዮጵያን ቀን በዳላስ አንባቢ እንዲያውቀው ገጿ ያዘጋጀችውን እንደ አመቺነቱ ወደፊት ታስነብባለች። ማህበረ ቅዱሳን aka ማቅ የተባለው ከልት እንደምህጻረ ቃሉ ማቅ እየለበሰ ነው። ቅንነትና ከልብ ያልሆነ ሁሉ ግዜ ይፍጅ እንጅ እውነቱ ገህድ ወጥቶ ፀሀይ እንደሚሞቅ የታወቀ ነው። በሰሜን አሜሪካ ያለው የነርቭ ሴንተራቸውም ሁኔታዎችን ለመቆጣጠር ከአቅሙ በላይ ሆኖበት ምናልባት ሌሎቹን ተሀድሶ ባለበት አንደበቱ ዛሬ ተሀድሶ ለእርሱ ወይንም አብሮ ወደ መቃብር ወራጅነቱን ከሚደርሱን ዘገባዎች ልንረዳ ችለናል። ይህም ከሚከተሉት የብዕር ጨመቃ ስራዎች የሚካተት ይሆናል። ለዛሬው ቸር ያሰማን በማለት ስንሰናበት መልካሙን ሁሉ እየተመኘንላችሁ ነው።

እርሶስ ምን ይላሉ?    

Thursday, July 7, 2011

ማርገብ ወይስ ማራገብ?

የርሶ ብዕር አስተያየት ተሳትፎ ሕብረተሰባችንን ይጠቅማል ያሉትን አይንፈጉን ገንቢነቱ ቦታ ይኖረዋልና!

ማሳሰቢያ፡ ይህ ገጽ የተዘጋጀው የተለያዩ የኅብረተሰባችንን ሀሳብ ለመለዋወጫ እንጂ ለሚሰጡት ማንኛውም አስታየቶች በማንኛውም መንገድ ተጠያቂ አይደለም። ጉግል ድርጅትም ኃላፊነት አይወስድም።


ማርገብ ወይስ ማራገብ?

የተወደዳችሁና የምንነፋፈቅ የገጻችን ተከታታዮች እንደምን ከረማችሁ? በልዑል እግዜአብሔር ፈቃድ ደግመን ብዕራችንን እንድንጨምቅ ወደ እናንተም እንዲደርስ ለፈቀደው ለእርሱ ሁሉም ክብርና ምስጋና ይሁንልን። ስለገናናው ስሙ በፍጥረቱ ዘንድ ሁሉ ይወደስልን። አሜን።

ጌታችን አምላካችንና ፈጣሪያችን በባዕድ ምድር አምጥቶ የማያልቅ ቸርነቱንና በረከቱን አፈሰሰልን። እጅ ለእጅ ተያይዘን በአንድነት እንግዳ የሆነውንና ያልታወቅውን እምነታችንን ከሩቅ ውቅያኖስን አሻግረን በየከተምንበት ሁሉ በማዳረስ ከአንድ ቤተክርስትያን ቁጥር እያበለጥን በእርሱ ጸጋ መብቃታችንን በማስተዋል ፈቃዱን በመቸሩ ምስጋናችንን ከልብ ማድረግ ይገባናል። ጽድቅ ባለበት ሁሉ አጥህ እንደሚያደናቅፈን መዘንጋት አያስፈልግም። እጅ ለእጅ ተያይዘን የጀመርነውን አብቦ ለተተኪው የማስተላለፍ ደግሞ የግድ ነውና በዚህ ሳምንት ማገባደጃ ላይ እየተካሄደ ያለው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ተከታይ አማኞች በአይነቱ ለመጀመሪያ ጊዜ በሰሜን አሜሪካን በቴክሳስ ግዛት በዳላስ ከተማ አካባቢ የሚገኘው የደብረ ምህረት ቅዱስ ሚካኤል ካቴድራል ደብር የጀመረው ከታዳጊ እስከ ወጣት የሚያካትተው መንፈሳዊ ጉባኤ ታላቅ ቦታ ይሰጠዋል። በተለይም ከአመት በፊት ይህ ደብር ከተወሳሰበ ፈተና ብቻ ሳይሆን ሕልውናው አደጋ ላይ እንደነበር ለማንም ግልጽ ነው። እነዚህ ጠላቶች በተለያየ መልኩ የከፈቱበትን ፈተና በእግዜአብሔር እገዛ ለዚህ ታላቅ ምዕራፍ ጎህ ቀዳጅ ሆኖ በመገኘቱ ደግሞ ደስ ሊለን ይገባል። እኝባችንን አብሶልናል ጸሎታችንንም ስምቶናልና። ለፈጣሪያችን ምስጋና ይሁንልን። አሜን።

ዛሬም እንደዚህ አሜህላ የሆኑ እህትና ወንድሞች ጨርሰው አልጠፉምና በጸሎታች በርትተን መጽናት ይገባናል። ፈጣሪም እንደዚ ያሉትን እጸጽ ከማራገብ አውጥቶ አርጋቢ ያድርግልን እንላለን። የተከፈተው የወጣቶች ጉባኤ ወጣቶቻችን የምንጠብቅባቸውን የተረካቢ ጎዳና ውስጥ እንዲሳተፉ ፈጣሪያችንን እንማለዳለን። አንድነትና ሕብረታችንን ይጠብቅልን። ቤተክርስትያናችንን ቅን አገልጋዮቿን ይጠብቅልን። ጉባኤውንም የታቀደውን ግብ ያድርስልን፡። አጽራረ ቤተክርስትያንን ያስታግስልን። አሜን።

ከዚህ ፈቀቅ ስንል ደግሞ የዳላስ መረዳጃ ማህበርን አስመልክቶ ባለፈው ያወጣነውን ትኩስ ዜና የከተማችሁ መነጋገሪያ እንደነበርና ግንዛቤን ያጫበጠ መሆኑን ከሚደርሱን አስተያየቶች ስላገኘነው፣ ስለተሳትፎዎቿችሁ ልባዊ ምስጋናችን ይድረሳችሁ። ቀደም ሲል የነበረው ሴራ ውስብስብ እንደነበር ከመኃላችሁ የተረዱት በጣት የሚቆጠሩ ቤሆንም ቀደም ብለው ፊት ለፊት የገጠሟቸውን ወይዘሮ ላይ የከፈቱት ዘመቻና የግለሰቧን ቆራጥነት ገጻችን ታደንቃለች። የተራዷቸውና የደገፏችውንም ምስጋና ይድረሳችሁ እያልን ድርጅቱ ባለቤቱ ለሆነው ወገኖቻችን ተመለሰ ለማለት የሚያስችለው ፈጽሞ ሲጠራ ብቻ ነው።

በተለይ ድርጅቱን ለማጥፋት ዘመቻው የተጀመረው ቀደም ሲል ነበር። ወደመረዳጅው ማህበር ዘልቀው በመግባት የተቆጣጠሩት ጥቂት ግለሰቦች በእድር ሽፋን የሕይወት ኢንሹራንስ ለመሸጥ ነበር። እነዚህ የኢንሹራንስ ደላላዎች የታያቸውና የታወሩት በግል ጥቅም ብቻ ስለነበር፣ አጋጣሚው ድርጅቱ ደካማ እንዲሁም ተቆርቋሪ የለውምና ፤
1. የመረዳጃ ማህበሩን ሕጋዊ ስምና ፈቃዱን በማብከን። ጊዜው ሲደርስ ደግሞ በእራሳቸው ስም የማውጣት ቁልፍ ዋነኛው ስልትና በስሙ ከተለያየ መንግሥታዊና ግላዊ ድርጅቶች በኢትዮጵያውያን ስም ገንዘብ ማግኘት ነበር። ምሳሌ አውራዎቹ የፈጠሯቸውን የግብረ-ሰናይ ስሞች ብዛትና ማን ማን እንደሆነ እኛና ሌሎች በገጾቻችን ያስነበብነውን ማየቱ ይጠቅማል። ለዚህም ነበር የዳላስና አካባቢውን የኢትዮጵያን መረዳጃ ማህበር ሕጋዊ ፈቃድ አብክነው የነበሩ።
2. መረዳጃ ማህበሩ በድህረ-ገጹ እንዳስቀመጠው እድሩ በስሩ እንዳለ ያደረገውን አስነብቦናል። ነገር ግን እድሩ የተቋቋመበት ጊዜ መረዳጃ ማህበሩ ሕጋዊ ሰውነት የሌለውና ፈርሶ እንደነበር ይታወቃል። አላማው መረዳጃ ማህበሩ ስሙ ከመከነ በኃላ በግለሰብ ስም ለመተካትና ማንም ሳያውቅ ለመበዝበዝ ሲሆን፤ ይህ ቢታወቅም አንዴ ሕጋዊ ሰውነትን ከያዘ ማስመለስ አይቻልምና። ይህን እስከለጠፍንበት ደቂቃ እድሩ ምንም አይነት ሕጋዊ ሰውነት የሌለው ነገር ግን በጠረፔዛ ስር የተደረገ ሕገ ወጥ እድር ነው። ይህንንም ጊዜዊ ከለላ ያስተናገደው የቀድሞ መረዳጃ ማህበር አመራር ሲሆን የአሁንስ ምን ይል ይሆን? ዋናው አላማ እድሩን በመረዳጃው ማህበር ለመተካት ወይንም መረዳጃ ማህበሩን ለማገት ሲሆን፣ በዚህም ኢንሹራንስ ደላሎችም በእድር ስም ነገር ግን ጃንጥላ የተባለውን መድህን በመግዛት ከሆነ የራሳቸውን መድህን መክፈት ካልሆነም መሀል ቤት ሆነው ወገኖቻችንን መዝረፍ ነው። ነገርን ነገር ያነሳዋል እንዲሉ፤ አሁን እድሩ እክል ላጋጠመው መክፈል ባይችል ተጠያቂው ማነው? ለሚለው ጥያቄ ማንም የለም ነው መልሱ።።

ምክንያቱም እድሩ ምንም ሕጋዊ ሰውነት የሌለውና ተጠያቂ የሚሆን ሕጋዊ ተወካይ የሌለው ነው።
መረዳጃው ማህበርም ቢሆን ህገ ወጥ ስራ ሲሰራና በተባባሪነት ስሙ ሲጠቀስ እንጅ በመተዳደርያ ደንቡ ላይ ያልተቀመጠ በመሆኑ አላውቅም ባይ ይሆናል። ከዚህ ጋር ተያይዞ ሂሳብ ደብተሩ በገለልተኛ አካል ተመርምሮ ያልተረጋገጠና ሀቀኛ ቁጥሩ የማይታወቅ መሆኑን በተግባር ያሳየ ነው። መረዳጃውም ቤሆን በሂሳብ አያያዙ ላይና ቁጥጥር የማያደርግለት መሆኑ ይታወቃል። እድሩ ስም እንጂ በራሱ ገለልተኛ ነው። ሕጋዊ ፈቃድም በምንም ጎኑ የለውምና። 500 በላይ አባል አለን የሚሉትና አመራሩን የያዙት ቢሆኑም እምነት የማይጣልባቸውና በወገኖቻችን ላይ ለሚደረገው ስውር ብዝበዛ ተጠቃሚዎች እንጂ ንጹሀን እንዳይደሉ እናሰምርበታለን።

ዘግይቶ እንደደረሰን ከሆነ ባለፈው ሳምንት ለወራት የመረዳጃ ማህበር ሊቀመንበር የሆነው ብርሀን aka ማክ መኮንን ለቦርዱ እንቅፋት በመሆኑ ቦርዱ በመረጃ በተደገፈና በአንድ ድምጽ ወስኖበት እንደነበር ነው ግን ከእነርሱ መግለጫ ስላልመጣ አልፈነው በእርሱ ፈቃድ እንደለቀቀ አድርጎ የበተነውን ያነበባችሁ ሁሉ ትገነዘባላችሁ እንላለን። በጥሁፉ ላይ ከጠቀሰው ስም አንዱ የበተነውን ኢ ሜይል እንደዚህ ይነበባል።


--- On Tue, 7/5/11, Daniel Gizaw wrote:

From: Daniel Gizaw
Subject: Emergency meeting
To:
Date: Tuesday, July 5, 2011, 10:14 AM

SELAM  All EDIR members,

You might have heard the Ethiopian Community Radio Ato Birhan  on Sunday the MAAEC chairman  calling an emergency meeting. When there is an impasse to resolve an issue or issues the by-law give the chairman authority to call an emerngency  meeting. The Board members division is a sign of unhealthy atmosphere which  take our community and EDIR backward.  Therefore, we can not stress enough that your participation on the meeting which is going to be held July 10th at Double tree Hotel located at Central and Campbell.

We highly encourage you  to pass this information to EDIR members that you know.

Thank you very much

The EDIR  secretary  

Daniel Gizaw

እንግዲህ ከጠሀፊው አጻጻፍ የስፔሊንግና የግራመር ጉድፉን ለእራሱ በመተው ( ሊያው ሚስቱስ ቢሆን የመረዳጃው ማህበር በጠሀፊነት ተቀጣሪ ተመሳሳይ ችግር ያላት ስለሆነች ባልና ሚስት ከአንድ ውኃ ብለን እንለፋት)። የጥሁፋችን መነሻ ያደረግነው ‘ማርገብ ወይስ ማራገብ’ ወደ አልነው እርእስ ቢወስደንም አንባቢ የራሱን ግምገማ ያድርግ እንላለን። እንደ ደረሰን አስተያየቶች እንግዲ አቶ ብርሀን  ለግለሰቡና ለሚስቱ በጣም የተነካ ባስመሰለው የስንብት ጥሁፉ ካዘነላቸው፤ በግሉ ከሚያስተዳድረው ንግድ ቤት በቂጣ ጠፍጣፊነት ወይንም በፒሳ አድራሽነት የተላላኪ ስራ ውስጥ ቢዶላቸው እንጂ እርሷ ለመረዳጃው ማህበር ሳይሆን አብዛኛውን ጊዜዋን የምታጠፋው ለቢሮው ተጋሪዎች በማገልገል ሲሆን እርሱም መረዳጃውን በእድርና በሕይወት ኢንሹራንስ ድርጅት ለመተካት ነው። ምናልባትም አቶ ብርሀንም የዚያ ራዕይ ተጋሪ ለመሆን አስቦ ይሆን? ስለነእነርሱ የአዞ እንባ የያዘው። የተመረጠው ለመረዳጃው ማህበር ጥቅምና ጥቅም ብቻ መሆኑን አላወቀውምን?

ይህ የተበተነውና ተጠራ የተባለው ስብሰባን በተመለከተ የሚመለከታችሁ ሁሉ በቀጥታ የመረዳጃ ማህበር ተመራጮቹን በማነጋገር መረዳት ይገባችኃል። ጠሪው የቀድሞው ሊቀመንበር በግሉ እንጂ መረዳጃው እንዳልሆነ ስላረጋገጥን ይህ ሕገወጥ ስብሰባና ወገኖቻችንን አንድነት የሚያናጋ ሰይጣናዊ ስብሰባ ነው። የመረዳጃውንም ማህበር እንዲፈታተን ጥቅማቸው የተነካ ግለሰቦች አብረው የሚደልቁት ከበሮ ነው እንላለን።  

በሚቀጥለው መጣጥፋችን እስክንገናኝ፤ ለሁላችንም ማስተዋልና ቅንነትን ይስጠን። ከመካከላችሁ አሜኸላ የሆኑባቸሁን ውንድሞችና እህቶች ፈጣሪ ልቦናቸውን ይመልስልን፤ ቸር ወሬ ያሰማን ፤ በቸር ያገናኘን። አሜን።

እርሶስ ምን ይላሉ?

Monday, July 4, 2011

አንጀቴ ቅቤ ጠጣ!

ማሳሰቢያ፡ ይህ ገጽ የተዘጋጀው የተለያዩ የኅብረተሰባችንን ሀሳብ ለመለዋወጫ እንጂ ለሚሰጡት ማንኛውም አስታየቶች በማንኛውም መንገድ ተጠያቂ አይደለም። ጉግል ድርጅትም ኃላፊነት አይወስድም።


 አንጀቴ ቅቤ ጠጣ!

ከውስጡ ትኩስ ዜና ስለ አቶ ብርሀን የመልቀቂያ ደብዳቤ የተሰጠውን አክለንበታል።

የተወደዳችሁ የገጻችን አንባቢዎች እንደምን አላችሁልን? በእርሱ ፈቃድ ደግመን ብዕራችንን ለመጭመቅ ፈቃዱን ላደረገልን ለልዑል እግዜአብሔር ክብርና ምስጋና ይሁን። አሜን። ስለ ታላቁ ስምህ አሁንም ክብር ምስጋና ይሁን።

በዳላስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ደብረ ምህረት ቅዱስ ሚካኤል ካቴድራል ደብር የቅዱስ ያሬድ መንፈሳዊ ተቋም ከፊታችን ሀሙስ ጅላይ 7 እስከ 9 2011 ድረስ በደብሩ ውስጥ የሚያኬደው መንፈሳዊ ጉባኤ በአይነቱ ለመጀመሪያው ጊዜ በሰሜን አሜሪካ የኢትዮጵያ ተወላጆች ዘንድ ታላቅና ታሪካዊ ቦታ የሚሰጠው ነው። ይህ ተቋም በዚሁ ከቀጠለ ወደፊት ሀገር በቀል የኦርቶዶክሳዊ ዕምነት አገልጋይና ተረክቦ ጠባቂ የሚሆኑ የዕምነቱን ሊቃውንትና ካህናትን ማፍለቂያ ምንጭ ይሆናል የሚል ከፍተኛ ዕምነትን ሊያስጨብጥ የሚያስችል መሰረትን ይጥላል የሚለውን ራዕይ ያደርሰናልና ሁላችንም በያለንበት በጸሎታችን ሁሉ ልናስበው የሚገባን መሆኑን ገጻችን ታሳስባለች።

ከታሪክ እንደምንረዳው ከሆነ ደብሩ በዳላስ ኪንግ መንገድ ላይ ከሚገኘው የቀደምት ስፍራው አሁን በጋርላንድ ውስጥ በሰሜን ጁቢተር መንገድ የተዛወረበት ምክንያቶች ውስጥ አበይቱ ስለ ታዳጊ ልጆቻችሁ እንደሆነ ነበር። በየጊዜው ከሚመረጡት የደብሩ የስራ አመራሮች አብዛኛዎቹ ተደጋግመው የሚመረጡት አበይት ምክንያት ሆኖ ወደ አዲሱ ሕንጻ ያስገዛቸውን ጉዳይ ላይ የሰጡት ትኩረትና ያስመዘገቡት እድገት ለራሱ ምስክር ስለሚሆን ግምገማውን ለሚመለከታቸው እየተውን፤ ለወጣቱና ለህጻናቱ ተብሎ የተቀጠረው አዲሱ መምህርና አዲሱ የአስተዳደር አባላት እያስመዘገቡ ያሉትን ልዩነት በኛ ብዕር ብንከትበው ደግሞ ወገነኛ ያሰኘናልና እናንተው ገምግሙት የምንለው። ምክንያቶችን ዘርዝረን የአነጻጸርንበትን ነጥቦች ማቅረብ አይገደነም ነገር ግን የቀደሙት አመራሮች ምንም ሰሩ ምንም ባላቸው የዕውቀትና የአመራር ብቃት ለተተኪው አድርሰዋልና የአሁኖቹን ራዕያቸው ደግሞ ምንድን ነው ? የሚለውን እናንተው ዳላሶች ናችሁና የምትኖሩት፤ አብራችሁ በቅንነት ከአመራሩ ጎን በመሆን ለተተኪና ተረካቢ ልጆቻችሁ የሚጠበቅባችሁን በምትችሉት ሁሉ በመተባበር ለሀይማኖታችሁ ቀጣይነት አጋዥ በመሆን የበረከቱ ተካፋይ እንድትሆኑ ክርስትያናዊ ጥሪዋን ገጻችን ታቀርባለች።

ገጻችን በየጊዜው ከሚደርሷት መልዕክቶች ውስጥ አንዳንድ ጥቅማቸው የተነካባቸው አሊያም ከኛ ውጪ ወይንም እኛ ባልነው በማለት መልካምና ትሁት የሆኑትንና ያለምንም ጥቅም በበጎነትና በቅንነት እንባረክበታለን ብለው የሚያገለግሉትን ምዕመኖችን በተለያየ መንገድ ለማወክ እንቅፋቶች እየሆኑባቸው ይገኛሉ። እነዚህ ከውስጥ ሆነው የሚያውኩትን ልቦና ሰጥቶና መክሮ እንዲመልሳቸው ለፈጣሪ እየለመንን ፤ ቅን አገልጋዮችንም ትግእስትን እንዲሰጣቸውና በረከቱን እንዲያበዛላቸው ፈቃዱን ያድርግልን እንላለን። የወጣቶቹን ጉባኤ እንዲሳካ ለተሳተፉት ሁሉ እግዜአብሔር ይክፈላቸው፣ ልጆቻችንንም ይባርክልን፣ አጽራረ ቤተክርስትያንን ያስታግስልን። አሜን።

ከዚህ እልፍ ስንል ደግሞ የዳላስ ኢትዮጵያ መረዳጃ ማህበር የጁላይ 3 እሁድ የሬዲዮ ዝግጅትን በኢንተርኔት ለመስማት የሞከርነውን ድራማ አስቂኝና አሳዛኝ ነበር። ብዙ ጊዜ ገጻችን ያስጨበጠቻቸው እውነታዎች ዛሬም እየተደገሙ በመሆናቸው ‘አንጀቴ ቅቤ ጠጣ!’ የሚለውን ዘይቤ ያስታወሰን እውነትነቱ መዳገሙ እንጂ አስደስቶን አለመሆኑን ልናሰምርበት እንፈልጋለን።

ዝግጅቱ ጥራት የሌለው ብቻ ሳይሆን ብቃት ያጣ አስተናጋጅ ያቀረበው መሁኑን ያደመጠው ሁሉ ዋቢ ይሆነናል። ከሁሉም በላይ ሬዲዮኑ የማን ነው? ኃላፊና ተቆጣጣሪስ አለውን? የሚቀርቡትንስ ዝግጅቶች የሚገመግመው ማነው? አሊያስ በጣት የሚቆጠሩ የሬዲዮ መናገሪያውን ይዘው እንዳሻቸው የሚፈልጉትን መደስኮሪያ መሳሪያቸው ይሆን? ወዘተ……የመሳሰሉትን ጥያቄዎች የሚመለከታቸው የመረዳጃ ማህበር አመራሮችን መስሎ ስለማይታየን ማን ይሆን የሚመልሰው? የሚለውን አንባቢዎቻችን የቤት ስራ ይሁናችሁ እንላለን።

የመረዳጃው ማህበር ተመራጭ ያደረገውን የፊታችን እሁድ የስብሰባ ጥሪን አስመልክቶ ተቃራኒ የሆነ ዲስኩር ያደረገው ግርማ ንጉሴ የተባለው በምሬትና በቁጭት የተመራጩን ንግግር አጣጥሎና አዋርዶ የሰጠውን መግለጫ የለየለት ጸረ መረዳጃ ቅስቀሳ እንደነበረ አስደምጦናል። ቀደም ሲል መረዳጃ ማህበሩን አፍነው ከሚመዘብሩት ውስጥ አንዱ የሆነውና በታቀደው የአመቱ የኢትዮጵያ ቀን በዓል ተሳትፎ የግል ጥቅሙ እንደሚቀርበት ከወዲሁ በመረዳቱ ከነግብረ- አበሮቹ የከፈቱት አዲስ ዘመቻ ነው። ስለዚህ ግለሰብ ቀደም ባሉት መጣጥፎቻችን ውስጥ ብዙ የተካተተ ስለሆነ እንደ እነዚህ ላሉት ግለስቦች መረዳጃ ማህበሩና ወገኖቻችን ከወዲሁ ነቅተው መዘጋጀት ይገባቸዋል።

ከዚሁ ጋር ተያይዞ የስብሰባውን ጥሪ ያስደመጠው የመረዳጃ ማህበሩ ሊቀ መንበር ብርሀን መኮንን የተባለ ሲሆን፣ ከምንጮቻችን እንደተረዳነው ከሆነ ይህንን የስብሰባ ጥሪ አስመልክቶ ቦርዱ ምንም አይነት ስብሰባና ውሳኔ አለማድረጉንና ምንም አይነት ቃለ ጉባኤ ያልጨበጠ መሆኑን፣ በግሉ ያደረገው ጥሪ ነው በማለት ሌሎች ተመራጮች መናገራቸውን አስምረውልናል። በዚህ የራዲዮ ስርጭት ላይ ከተደመጠው ጋር ሌላው አቅራቢ ስለ በትሩ ገብረእግዚሀብሄር የኮሚኒቲ ጀግና የሚል እውቅናና ሽልማት መደረጉን ነበር። ይህች ገጽ ከዚህ በፊት የግለሰቡን አስነዋሪ ምግባርና በቴኔሲ ፍርድ ቤት ከነባለቤቱ የተወነጀለብትን በቀደምት ገጾቿ ማስነበቧ ይታወቃል። በዳላስም የተለያየ ግብረ- ሰናይ ድርጅት ስሞችን በመጠቀም አልፎም በወገኖቿችን ስም በመነገድ እንጂ በዳላስ አካባቢ ለሚኖሩት ወገኖቿችን ያበረከተውና ለኮሚኒቲ ጀግና ተብሎ የሚያበቃው ያየነው አንድም ጠብታ የለም። እርሱና የጥቅም ተካፋዮቹ ጥቂት ግለሰቦች የሚቀቡት ስያሜ ነው ሲል ምንጫችን አስረድቶናል። አሁን ደግሞ አዲስ የተመረጠው መረዳጃ ማህበር ቦርድ ሊቀ መንበርም ሕብረተሰቡን በመወከል በዚህ ግብዣ ቦታ መገኘቱን ራዲዮው ማስደመጡ ይህ ሰው ማነው ወደሚል ግምገማ ጋብዞናል። በዚህም መሰረት ብርሀን በሚል መጠሪያ የተመረጠው ግለሰብ ጥንድ ስም ያለው ለመሆኑ ከመረዳጃው ማህበር ድህረ ገጽ ለመረዳት በቅተናል። ስሙም ማክ መኮንን ነው። እንዴት በሁለት ስም ይጠራል? ለምንስ አስፈለገ? የሚለውን ጥያቄ ላንባቢ እየተውን የተጓደኛቸውንና አብሮ በአላቸውን ያዳመቀላቸውን በማስተዋል ሊታይ ይገባዋልና የወደፊቱ የድርጅቱን ጉዞ በዚህ አይነት ግለሰብ አመራር ስር ለመተንበይ አያዳግትም ያሰኛል።

የአስቸኳይ ስብሰባው አላማ እንደተደመጠው ከሆነ የኢትዮጵያን በዐል ቀን አስመልክቶ  ቢሆንም በመረዳጃው ማህበር ድህረ ገጽ ላይ ቀኑንም ጨምሮ እንደሚከበር የተወሰነ ሲሆን፤ በግሉ የጠራው ስብሰባና የግርማ ዲስኩር ተዳምሮ ምን እየተሰራ መሆኑና አዲሶቹም ተመራጮች ከድጥ ወደ ማጡ እየተጓዙ መሆናቸውን ያሳያል። በሌላ በኩል በድህረ ገፁ በተቀመጠው መሰረት የሬድዮ ዝግጅቱ የመረዳጃ ማህበሩ መሆኑን ሲያስነብብ፤ አቅራቢዎቹ ግን የግላቸው በማድረግ ያሻቸውን እንደሚያደርጉና ለመረዳጃ ማህበሩ አመራር ውሳኔ እንደማይገዙና ተጻራሪ ዘመቻ እንደሚያደርጉ ግርማ የተባለው ግለሰብ በ07/03/2011 ያስደመጠው ጉልህ መረጃ ነው። ስለዚህም መቼ ነው ሕብረተስቡና መረዳጃ ማህበሩ እውነተኛ የሬዲዮ ባለቤትነታቸው የሚታወቀው? ውይስ ለጥቅም ሸጠውታል? የሚያሰኘው። ሌላው ከገጹ ላይ የታዘብነው ቢኖር እድሩን አስመልክቶ ተመሰረተ የተባለውና በመረዳጃው ማህበር ስር ነው የተሰኘው የተባለበት ወቅት መረዳጃው በሕግ ፈርሶ እንደነበር ከዚህ በታች ያለውን መረጃ ማየቱ ጠቃሚ ሲሆን፤ ድርጅቱም ቤሆን በገጹ ለምን ይህንን አልገለጸም? በመረዳጃው ማህበር ስር እንዴት ሕገወጥ ጋብቻ ተደረገ? በመተዳደሪያው ሕግ ላይስ ለምን በግልጽ አልተቀመጠም? እድሩ በሕግ መሰረት በመረዳጃው ማህበር ስርና አካል ከሆነ እንዴት አድርጎ ነው ለአባላቱ እርዳታን የሚሰጥ? ምንስ ሕጋዊ ከለላ አለው? ወዘተ……..  
 
ሌላው መረዳጃ ማህበሩ በስሬ አቅፊ አለ የሚለውና እራሱን ግብረ-ሰናይ ድርጅት ነኝ የሚል ስለ ዐይን የተቋቋመና ከኤትዮጵያ ዐይን ባንክ ጋር ትስስር አለኝ የሚለውን ድርጅት አስነብቦናል። በየጊዜው አዳዲስና የመረዳጃው ማህበር አባላት ተሰብስበው ባልወሰኑት ላይ ጥቂት ግለሰቦች የሚፈጽሙት ሕገ ወጥ ጋብቻ ከመተዳደሪያ ደንቡና ሀገሪቱም ካወጣችው የግብረ-ሰናይ መተዳደሪያ ህጎች ተጻራሪ ተግባር መሆኑን ተረድተውት ይሆን? ወይስ በዳላስ አካባቢ ነዋሪ የሆኑት ወገኖቻችን መካከል እውቀትና ማስተዋል ያለው ማንም የኢትዮጵያ ተወላጅና ድርጅቱ የሁላችንም ነው ብሎ የሚነሳ ወንድ ወንድም ወይስ ሴት እህት ይጥፋ! ወይስ መሀይምና ደንቆሮ ብቻ ይሆን ብለን ለማስመር ባንዳዳም ጉዳዩ አስቸኳይና ታላቅነት ያለው ነው እንላለን። የሊቀ መንበሩን የትምህርት ደርጃ አጣርተን ባናውቅም ለጊዜው ቦርዱ ካቀፋቸው ውስጥ 2 የዶክተርነት ዲግሪ ያላቸውን ድሀረ ገጹ አስነብቦናል። የክብር ይሁን የዕውቀት ዲግሪ እኛ እስከምናውቀው ድረስ አምሃ የተባለው ግለሰብ ማንኛውም አይነት እንደሌለውና ከሚሰራበትም መስሪያ ቤት ያረጋገጥን ስለሆነ መረዳጃው የሀሰት ማዕረግ መቀባቱን ቢያርም ስንል፣ ስለሌላው ዶክተር ምርምራችንን ስላልጨረስን የምታውቁ ካላችሁ ብታካፍሉን እንወዳለን። እኛም ትምህርት ቤታቸውን ካወቅን እናረጋግጣለንና የዕውቀት ገብያቸው በሰጣቸው ደርጃ ሁሉ በቅን ከወገኖቻቸው ጎን ተሰልፈው ለሚቸሩ ሁሉ ገጻችን ምስጋናና አድናቆታን ለመለገስ አትቆጠብም። እንቅፋት ቢመታቸው እንኳን ትደግፋለች፣ አስፈላጊም ሲሆን እርማት ትለግሳለች ፣ ለመሻሻልም የሚጠቅሙ ጎኖችን ታካፍላለች፣ በጥፋቶች ላይ ትተቻለች፣ ተመሳሳይ አስተየየትና ነቀፌታዎችንም በእራሷ ላይም ትቀበላለች።

እንደተለመደው እርሶስ ምን ይላሉ ብለን ከመደምደማችን በፊት ከዳላሱ ምንጫችን የደረሰን ትኩስ ዜና እንደሚቀጥለው ይሆናል። ነገር ግን የኛ ዘገባ ሳይለጠፍ በፊት ይህ ቢደርሰንም አሳዝኖናል ሆኖም እራስን ብቁ አድርጎ ከልብ በቅንነት መቆምና በሌሎች ሳይደለሉና 2 ቢላዋ ሳይዙ የተጣለብዎትን  መወጣት ያቃቶትና ከወጡበት ዳገት ለምን ተንከባለው ወረዱ? ይህ ሕዝባዊ መረዳጃ ማህበር እንጂ በግሎ የሚያስተዳድሩትና እንዳሻዎ በግሎ የሚወስኑበት የንግድ ድርጅት አለመሆኑን እንዴት ጋረደቦት? ከመልቀቂያ ጥሁፎ እንዳሰመሩት ለሁለት ጌታ የሚያገለግሉና የመረዳጃ ማህበር ቦርዱን የመከፋፋይ ንፏቄ እየተገበሩ መክረሞን በገሀድ አስቀምጠውታል። በተለይም ድርጅቱ እንዳያብብ ሲያቀጭጭ ለኖሩት ባልና ሚስት አንጓችና አዛኝ ሆነው የከተቡት ጥሁፎ የህሊናም ሆነ የዕውቀት አድማሶን ስፋትና ብስለትን መስታወት ሆኖ ለእርሶ ያልታየበትን? ወይም ለከተማው እንግዳና ባይተዋር ሆነው ይሆን? ይህም ባይሆን አመታት ያስቆጠረውንና ቃል የገቡለትን የመረዳጃ ማህበር የገንዘብ እርዳታ በጨበጣ ይዘው እያቁለጨለጩ በወገኖቻችን ሕዝባዊ ድርጅት ላይ ገበጣ መጫወቶ ይሆን? ቃሎንስ ጠብቀው ሊቸሩ ወይስ ቃሎን ሊያጥፉ? የቀድሞ ደም ያሏቸውን ግለሰቦች ማንነት ያውቃሉን? ተርማቸው ካበቃ በኃላ በጉልበት አንለቅም ያሉ መሆናቸውን ምስክር አይደሉምን? የሕዝቡን ምርጫ ምላሽን ከእነርሱ ጋር አብረው ሊድጡና ሊጨፈልቁ የተነሱ መሆኖን ከዚህ በታች ያቀረቡት መልቀቂያ የበተኑላቸው ሁሉ ቦርድ ውስጥ የሌሉና የማይመለከታቸው እንዲሁም እርሶን ከኃላ ሆነው የሚዘውሩት ጌቶቾ ለመሆናቸው ጥሁፎ  በሚገባ አስቀምጦታልና አንባቢዎቻችን የራሳቸውን ግንዛቤ ይውሰዱ በማለት ከዚህ በታች ለጥፈነዋል።

---------- Forwarded message ----------
From: Mac Mekonnen
Date: Mon, Jul 4, 2011 at 1:39 AM
Subject: Resignation Letter
To: Ato Endeshaw Chckol , Ato Seyume Argaw , Ato Surafel Belay , Dr Ameha Gebremichael , "Dr. Sisay Teketel" , "Enge. Paulos Berhane" , "Enge. Samuel Kirub" , Wyzero Sene Yohannes
Cc: MAAEC InDFW , Yonas Liben , Hewan Yimer , solomon hamelmal , yilma.zerihun@gmail.com, YILMA FELEKE , ethdaydallas2011@googlegroups.com


To the Board (the original Board)…

I am resigning as Chairman and Board member of MAAEC at the conclusion of the General Assembly, on July 10.

Here are the reasons:

I can only work with one Board. Clearly, we have two Boards within MAAEC. Please refer to all email communications and some decisions made by the “other Board”. Refer to all emails that you received from these ‘Board” members.

I cannot work for or with a mob. Please look at some of the decisions made in the past 2 months. Please refer to all the decisions and direction you have witnessed by these Board members.

I cannot work with Board members who divide the community into two groups…the Old Blood and the New Blood. These Board members forget that the Old Blood was the reason for the position they are in. The Old Blood still flows into the heart of the MAAEC. The heartbeat of MAAEC you hear has the soul of the Old Blood. Having New Blood is good only when one recognizes the wisdom of the Old Blood.

I cannot work with Board members who by nature are designed to ruin what is built. When issues arise from the Old Blood, they will not stop to shut off the voice. Please refer to the genuine request that was made by the ED Committee.  Please refer to the sincere comments that were made by the EDIR and other committee members.

I cannot be a witness to see the MAAEC going astray after so much sweat, money, and many scarifies.

I cannot stand a Board member who diminishes a human being. The punishment and treatment that Wizero Yordanos received is unforgivable.  The treatment that Ato Daniel received was evil and no apology can heal it.

If requested, all records of events that transpired in the past two months will be available for the General Assembly.

I have extended all my apologies to the people who are hurt by all of the decisions that were made by the “other” Board.

I sincerely thank and apologize (for my departure) to Board members who are good at heart and have done everything possible to point out the ship is going astray…..

My regrets, I wish I were from the Old Blood!

Sincerely,

Mac Mekonnen
Chairman
MAAEC

እርሶስ ምን ይላሉ?

Saturday, July 2, 2011

የዳላስኢኦቲሲብሎግ.ካም መልካም ምኞቷን ትገልጻለች።

የዳላስኢኦቲሲብሎግ.ካም መልካም ምኞቷን ትገልጻለች።

የርሶ ብዕር አስተያየት ተሳትፎ ሕብረተሰባችንን ይጠቅማል ያሉትን አይንፈጉን ገንቢነቱ ቦታ ይኖረዋልና!

ማሳሰቢያ፡ ይህ ገጽ የተዘጋጀው የተለያዩ የኅብረተሰባችንን ሀሳብ ለመለዋወጫ እንጂ ለሚሰጡት ማንኛውም አስታየቶች በማንኛውም መንገድ ተጠያቂ አይደለም። ጉግል ድርጅትም ኃላፊነት አይወስድም። ኃላፊነቱ በሙሉ የአስታየት ሰጪው ብቻ ነው።


እግዜአብሔር አሜሪካንን ይባርክልን- ጁላይ 4 የደስታ ዕለት ይሁንልን
Happy 4th of July- May God Bless America
የጁላይ 4 በዐላችን አከባበርዎ ከሳምንቱ መደምደሚያ ጋር ታላቅ እንዲሆንልዎ ምኞታችን ነው።
Have a great weekend as you celebrate the 4th of July.
The best from all of us at http://www.dallaseotc.blogspot.com/

የዳላስኢኦቲሲብሎግ.ካም መልካም ምኞቷን ትገልጻለች።