Sunday, November 7, 2010

የኮብራ እባቡን ያዙልንና እንለፍ ለሚሉ

የርሶ ብዕር አስተያየት ተሳትፎ ሕብረተሰባችንን ይጠቅማል ያሉትን አይንፈጉን ገንቢነቱ ቦታ ይኖረዋልና!

ማሳሰቢያ፡ ይህ ገጽ የተዘጋጀው የተለያዩ የኅብረተሰባችንን ሀሳብ ለመለዋወጫ እንጂ ለሚሰጡት ማንኛውም አስታየቶች በማንኛውም መንገድ ተጠያቂ አይደለም። ጉግል ድርጅትም ኃላፊነት አይወስድም። ኃላፊነቱ በሙሉ የአስታየት ሰጪው ብቻ ነው።


የኮብራ እባቡን ያዙልንና እንለፍ ለሚሉ

በዚህ አገር የኮብራ ዘር የሆኑት የእባብ አይነቶች አደገኛ ገዳይ ሀይል ያላቸው በመሆናቸው እጅጉን የተፈሩ መርዛሞች ናቸው። የኛም ገጽ እነዚህን መርዛም እባቦችን ለይተን ስናሳውቃችሁ አብረን ከርመናል።እንግዲህ የነቃችሁባቸውና እያደበያችሁ የጣሏችኃቸው ብዙዎች ናችሁ። ነገር ግን ዛሬም እነዚህን መርዛም እባቦችን ያዙልንና እንለፍ የምትሉ ቂላቅሎች ደግሞ እኛ መርዛም እባቦችን እናንተው ሞክሩና ከመርዙ ካመለጣችሁና ከተረፋችሁ፣ ብላችሁም ከልባሞቹ ጎራ ከገባችሁ እንያችሁ ነው የምንል። የተወደዳችሁ የገጻችን ተከታታዮች እንደምን ከርማችኃል? የእርሱ ፈቃድ ሆኖ ለዚህ ጊዜ ላደረሰን ለልዑል እግዚሀብሔር ክብርና ምስጋና ይሁን። አሜን።

በተለያየ ጊዜ አስረግጠን በደብራችሁና በመረዳጃ ማህበራችሁ ላይ የተደረገውንና እየተደረገ ያለውን ሂደት በሚገባ እያስጨበጥናችሁ አብረን ከርመናል። በየጊዜውም አዲስ አበባ እየደረሱ ለሚዘግቡት መረጃ ካሳ ጥቅማጥቅም ከሚደለሉት ውስጥ ብዙዎቹ ባለ መሬት ሆነዋል። መቃብር ቦታን ሳይቀር እያፈራረሰ እንዲሁም የገጠር መሬት ሳይቀር ለውጭ ባለ ሀብቶች በነጻ ለማለት በሚያስደፍር ዋጋ እየቸበቸበ ያለ መንግሥት፤ ምንም አይነት ለነዋሪው ዜጋ፣ ለአካባቢው አየርም ሆነ መሬት ብክለት ደንታ እንደሌለው ባለፉት ጥቂት አመታት ከአበባው እርሻ ሂደት የጨበጥነውን ዋቢ በማድረግ ስንተች ለወደፊቱ የተሻለ አቀራረብ እንዲሰነጽ ለሚመለከተው አካል የመጠቆም የትውልድ ግዴታችንን ለመወጣት በማሰብ ነው። ካካባቢው ከሚወጡት ዘገባዎች፣ በአበባው ምርት ምክንያት ካካባቢው ለተፈናቀሉት ዘለቄታዊነት የጎደለው የአኗኗር ልውውጥ (ትራንስፎርሜሽን) ፤ በምርቱ ምክንያት የተፈጠረው የተፈጥሮና የአካባቢ ብክለት ያስከተለው ፤ ባምራች ሰራተኞች ላይ የደረሰው የጤና ችግርና በምድረ ከርሱ ላይ ያተረፈው ብክለት በቀላሉ የሚታለፍ አይደለም።

ቤተ ክህነቱ ባለው የአስተዳደር ብልሹነትና የውስጥ ምዝበራ የተነሳ እያንዳንዱ የአዲስ አበባ ደብር ለንዋይ የሚያደርገው ሩጫ ወደ ሌላውም የሀገሪቱ ክፍሎች እንዳይሰራጭ እየተሰጋ ያለ ችግር ነው። አጽማቸው እየወጣ ያሉት ብዙዎቹ ለዚያ ቤተ ክርስትያን በዚያ ቦታ ከምስረታው እስከ ህልውናው በሕይወታቸው የከፈሉት የሚዘነጋ አይደለም። የመሬት ችግር የለብንም የሚል መንግሥት ተርፎት ለባእድ የሚቸረችር እንዴት ይህንን ጉዳይ በዝምታ ያየዋል። እኛ ሀገር አይሰልጥን አንልም ነገር ግን ሁሉም በአግባቡ ቢሆንና ለቀጣዩም ትውልድ በማስተዋል ይሁን ነው የምንል።

በመረዳጃ ማህበራችሁ ስር በሕገወጥ መንገድ የተለጠፈውን እድር በማደራጀት የያዙት የጴንጤ እምነት ካላቸው ውስጥ ወደ አዲስ አበባ ጎራ እያሉ መረጃ ባቀረቡ ቁጥር በጥቅማ ጥቅም እየተደለሉ የሚመለሱትን እያዩ ከእስልምና ሀይማኖት የያዙትም እሽቅድድም እየገቡ ነው የሚል ዘገባ በማየታችን ብዙም አልተገረምንም። አዲስ የሚመረጡ ከተገኙ ፣ እድሩን በፍጹም ከመረዳጃው ማፋታት የቅድሚያ አጀንዳቸው መሆን የሚገባ ነው። በአሁኑ ሰአት ህብረተሰቡ ሁኔታዎችን በሚገባ አላምጦ የጨረሰ በመሆኑ ተግባራዊ ያደርገዋል የሚል ተስፋ እየታየ ነው። በተለይም በአሁኑ ሰአት ለሁለት ተከፍሎ ያለው የመረዳጃው ማህበር አመራር በቅርቡ ራሱን እየቀረጸ ይመጣል የሚል ተስፋ እየታየ ነው። አንዳንዶች አመራር ላይ ያሉት አንጃ እየሆኑባቸው የመጡት በወንጀል ደም እጃቸውን ከታጠቡት ጋር ላለመስራት እራሳቸውንም ለመለየት ወስነዋል። አሁንም በነ ይልማ ፈለቀ የሚመራው የወያኔ ቡድን ቀስ እያለ መሬት እየከዳው ይገኛል። አዲሱ ምርጫም በፊት እራሳቸውን ያገላሉ ተብሎም ይጠበቃል። በሌላ በኩል ከወይዘሮዋ ጦመር እየተጋለጡና እየተመቱ ያሉት ፤ በህብረተሰቡ ስም በብዙ ሺህ ዶላር ሲዘርፍ የነበሩት የነ በትሩ ገ/እግዚሀብሔር ጉድ በማስረጃ እየተቀነባበረ እየተሰራ ለመሆኑ እንደዚሁም የመንግሥትም እጅ በቅርቡ ይገባበታል የሚባልም መረጃዎች ለመመዝገብ በቅተናል።

በሌላ በኩልም የእስስቱ ተፈራወርቅ ቡድን የተከላቸው እነ ፍቅረማሪያም ደረሰ ቡድን በመጋለጡና አዋቀርን ያሉትም ቡድን በመፍረሱ እነ ግርማቸው አድማሴ የጤና ቀውስ ውስጥ ከቶአቸው ይገኛል። እነዚህን መርዛም እባቦች የዳላስ ሕዝብ አንቅሮ ከተፋቸው እንግዲህ ከርሟልና መቃብራቸውን እየተመኙ ናቸው። ሰይጣናዊ ስራቸውን በመልካም ስም ለመሸፈን ሲሉ መለከት ያሉትም ገጻቸው እንደ በረዶ ከደረቀ ከርመ፣ ሀሰታቸው ሁሉ ተጋለጠ፣ እርቃናቸውን መቅረታቸውን ሀገር አወቀው። መሪዎቻቸው የሆኑት በቤተክርስትያኑና በዳላስ ነዋሪ በሆነ የኢትዮጵያ ተውላጆች ስም መነገዱን እንዲያቆሙ የሁላችሁም ግዴታ መሆን ያለበት፣ ባቆሙዋቸው የሀሰት ግብረ ሰናይና የባለሙያዎች ድርጅቶች ስም በሚንቀሳቀሱበት ሁሉ እየተገኛችሁ እናንተን እንደማይወክሉ ማጋለጥ ከሁላችሁም የሚጠበቅ ትግል ነው። በተለይም የወይዘሮዋ ጦመር ባለፈው ባወጣው መልዕክት ላይ በየሳምንቱ በሚካሄደው የቴሌኮንፍረስ የፓለቲካ ውይይት ላይ በመመዝገብ እየተሳተፋችሁ እነዚህን መርዛም እባበቦችን ማጋላጥ ግዴታችሁ ነው።

ፓለቲካው ውስጥም ፓለቲከኛ፣ ቤተ ክርስትያን ውስጥም ሀይማኖተኛ፣ በመረዳጃ ማህበር ውስጥም የወገን አሳቢ በመምሰል ለግልና ለወያኔ ጥቅም ማደሪያው ጊዜ አብቅቷልና ጥፉ በሏቸው። ከናንተ በተለያየ መንገድ የሚሰበስቡት ገንዘብ የት እንደሚገባ ታውቃላችሁን? እነሱና ቢጤዎቻቸው ኪስ ውስጥ ነው። ለምሳሌ የቅንጅቱ ብርሀኑ ነጋ በቅርቡ በጥሬ ገንዘብ ፩ ሚሊዮን ዶላር የሚያወጣ መኖሪያ ቤት መግዛቱ፤ የማይበራ ባትሪ የሚሉት የናንተው የዳላሱ ደጀኔ ወይንም ፍቅረማሪያም ስንት ደርሷቸው ይሆን?

ለመሆኑ በደብራችሁ ቅዱስ ሚካኤል አዲስ የተቀጠረው መምህር ስለ ልጆቻችሁ የሚሰራውን ጎብኝታችሁ የጣላችሁልን ባይኖርም፤ እኛም የሱ የርቀት ተማሪ ሆነን ጀምረናል። ይህ በኢንተርኔት የምናገኘው ትምህርት አጀማመሩን ብንወደውም ለምስጋና ገና አልደረስንም። የሚነቅፉንን መነኩሴ አባትንም አዲስ አበባ ኮሌጅ ውስጥ እንዳስተማራቸውም የደረሰን መረጃ ይጠቁማል። እርሳቸው ግን እርሱ ባገኘው ተወዳጅነት ብዙም ተደሳች ባይሆኑም የስራ ቅጥራቸው እንዲፈረም በጣም የቸኮሉ ሆነው ተገኝተዋል። እንደሚደርሰን ዘገባ ከሆነ በጣሙን ከነክፈተው (ኢዮኤል) ነጋ ቡድን ጋር እጅና ጓንት እንዲሉ የዕለት ጎብኜ ወዳጆቻቸውና አማላጆቻቸው ሆነዋል። ምናልባት አንዳንዶቻችሁ ካንድም ሁለቴ አውግዘዋችሁ አልፎ እርግማን ስለጣሉባችሁ ነው ትሉን ይሆናል! ያ ለኛ አይደለም። እኛ ዕውነትን ዕውነት፣ ሀሰትንም ሀሰት እንደምንል ሁሉ ለሳቸው ወዳጆች የሰጠነው ዕውነተኛ ባሕሪያቸውን ነው እንጂ ፈጥረነው እንዳልሆነ በግልጽ የተቀመጠ ነው። እኛም የግለሰቡን መብትና ነጻነት ስለምናከብር ከመሰላቸው ሁሉ የመወዳጀት መብታቸውን በድጋሚ እናከብራለን። የነሱንም ተጽዕኖ ተቀብለው ቢያራምዱም እንዳመጣጡ በጊዜው የደብሩን ህልውና በማስቀደም እናስተናግደዋለን።    

ከዚህ ባለፈ እንግዲህ ለልጆቻችሁ ትምህርት በተመለከተ የምታደርጉት አስተዋጾ በጣሙን ከማስኮራት አልፎ የሚያስቀና ሆኖ አግኝተነዋል። በደብሩ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ከ፹ በላይ ፈቃደኛ ሆነው ለልጆቻችሁ የትምህርት ክፍል ለመርዳት የተመዘገቡ ተገኝተዋል። ልዑል እግዚሀብሔር ምስጋና ይግባው። አሜን። እንደምንሰማው ከሆነ አስተዳደሩ የተቀሩትንም ንዑሳን ክፍሎችን ሁሉ በሚገባ ማደራጀት ስለጀመረ የምትችሉ ሁሉ በሚመስላችሁ ንዑሳን ክፍል እየተመዘገባችሁ አገልግሎት በመስጠት እንድትባረኩ በዚህ አጋጣሚ ከሚካኤል ሰይፍ ተወካይ የቀረበውን ጥሪ እናስተላልፋለን። እየተዋቀሩ ካሉት ውስጥ የአባት መዘምራን፣ የመስተንግዶ ክፍል ተጨማሪ የሰው ኃይል፣ እንደዚሁም የበዐል ቀን ዝግጅት የመሳሰሉ ሲገኙ ፤ ለመጪው የቅዱስ ሚካኤል በዐለ ንግሥ የገንዘብና የሁለቱንም ጾታ የሰው ኃይል ፈቃደኞችን ስለሚያስፈልግ የተቻላችሁን ሁሉ እንትተባበሯቸው በቅዱስ ሚካኤል ስም ጥሪ እናቀርባለን?

እርሶስ ምን ይላሉ?

1 comment:

Anonymous said...

Are these people not Christians as they claim to be? If they are, don't they know whatever they are doing against the Church, all their lies, law suits, blaspheme are going to come down on their children and grand children and their generations to come?

They need to read their BIBLES for the proof. God always keeps his promise!! Never fails.

Psalm 101:7: He who works deceit shall not dwell within my house; He who tells lies shall not continue in My presence.”
Numbers 14:18: 'The LORD is slow to anger, abounding in love and forgiving sin and rebellion. Yet he does not leave the guilty unpunished; he punishes the children for the sin of the fathers to the third and fourth generation.'
2 Corinthians 12:20: For I am afraid that when I come I may not find you as I want you to be, and you may not find me as you want me to be. I fear that there may be quarreling, jealousy, outbursts of anger, factions, slander, gossip, arrogance and disorder.
Lam 5:7: It was our ancestors who sinned, but they died before the hand of judgment fell. We have suffered the punishment they deserved!
James 1:21 Therefore, get rid of all moral filth and the evil that is so prevalent and humbly accept the word planted in you, which can save you.
Therefore, let us all BE AWARE OF whom we are worshiping, if it is the God of Abraham and Jacob, we should know that HE is slow to anger but quick to JUDGE.