Friday, December 24, 2010

የልደት በአል አደረስዎ

                እንኳን ለጌታችንና የመድሀኒታችን የኢየሱስክርስቶስን የልደት በአል አደረስዎ፤ 
   መጪውም አዲስ አመት የጤና፣ የፍሰሀና የስላም አመት ይሆንልዎ ዘንድ ምኞታችን ይድረስዎ!

1 comment:

Anonymous said...

ቤተክርስቲያናችን ያለው እቋፍ ላይ ነው።
ውድቀቱም ደህንነቱም ያለው በእናንተ በማህበርተኞቹ እጅ መሆኑን አትዘንጉ፤ ችላም አትበሉ።
የሚመጣውን ምርጫ እንደቀላል ነገር ቆጥራችሁ ችላ ለምትሉ ግለሰቦች መልእክቴ፤-
አንድም ሆነ ሁለት ለቦርድ የምታስገቧቸው ግለሰቦች ለምንድነው ቦርድ ለመግባት የሚፈልጉት
አንድ ለማጥፋትና ለመዝረፍ አለበለዚያም ቤተክርስቲያኑን ለመሸጥ ወይስ እዉነት ቤተክርስቲያን በንጽህ ልቦና ለማገልገል የሚለውን ጥያቄ አውጥታችሁ አውርዳችሁ መሆን አለበት።
የድሮ ሃጢያታቸው በዝርዝር በመረጃ እየቀረበላችሁ አይታችሁ እንዳላየ ሰምታችሁ እንዳልሰማ በመሆን የምትመርጡት ግለሰብ በዝምድናና በጓደኝነት ከሆነ ግን ቤተክርስቲያኑን አደጋ ላይ የሚጥል መሆኑን አትዘንጉ።
ስላዚህ፡
ሚካኤል ቤቱን እየጠበቀ ነው? ወይስ እየተፈታተነ ነው?
ካሁን ቀደም የሚካኤል ምእመን እያወቀ እንደነ ኢዮኤልን አይነት ቁማር አጫዋችና ብር ባራጣ አበዳሪ መርጦ ደብሩን ሲያስበዘብዝ ኖረ። እንደነ ኪዳኔ ምስክርን አይነት መርጦ ከነ ዘመዶቻቸው በማህበረ ቅዱሳን ስም ቤተክርስቲያኑን ሲያሟጥጡቱ ኖሩ። እንደነ ኪዳኔ አለማየሁ አይነት ጋር በመተባበር ማህበር ካህናት የሚባል የቀረጥ ነጻ (501.c) ያለው ድርጂት አቋቁመው የምእመኑን ገንዘብ በጎን እያወጡ ሲከፋፈሉት ኖሩ። አሁን ደግሞ ይህ አልበቃ ብሏቸው አይን ያወጣ ሌባ የሰው ቤት የራሱን አስመስሎ የሚሸጥና በእርግጥ የተፈረደበት ሌባ ቤተክርስቲያኑ ዉስጥ አስገብተው ሊያስበዘብዙት ይሆን?
የማህበረ ቅዱሳን ደጋፊና ጥቅም አባራሪ ሰሞኑን በ http://senbete.blogspot.com/ እንደተጠቀስው ግለ ሰብ ያሉና ስማቸውን እየቀያየሩ አንዴ በትሩ አምሳለ በሌላ ጊዜ በትሩ ገብረእግዚአብሄር ሌላው ደግሞ አንዴ ተፌ በሌላ ጊዜ ተፈራ ወርቅ እየሉ የአሜሪካንን መንግስትና ህዝብ የሚያታልሉ ግለሰቦችን ወደ ቤተክርስቲያኑ መሃል አስገብተው ሊያስበዘብዙ መሆናቸውን የማያውቅ ምእመን ይኖር ይሆን? ወይስ እየወቁ የአቶ ጌታቸው ትርፌ ዘመዶች እንደሚሉት ለስለት ክፈል ብለው ሲሰጡትና ሲበላው “ እኛ የሰጠነው ለሚካኤል ነው በእኛ ፊት የሰጠነው ደርሶልናል እሱ ቢበላው የራሱ ሃጢአት ነው” እያሉ በመደጋገም የሚሰጡና ሌባ ሲመርጡ ቤተክርስቲያኑንም ሆነ አገልግሎቱን እንደሚጎዱ አልተረዱም ማለት ይሆን?።
በእኔ አስተያየት የሚካኤልን ቤተክርስቲያን ቢሆንላቸው በክስ አዳክመው ባይሆንላቸው ሰርገው ገብተው እንደገና በዝብዘው እራቁቱን ካስቀሩ በኋላ ቤቱን ሸጠው ለመከፋፈል እንጅ ለአማኙ ም እመን አዝነው አለመሆኑን የተገነዘበ ሁሉ መተባበርና እነዚህን ነቀዞች በቃችሁ ማለት አለበት ባይ ነኝ።
እዩኤል የተመረጠበትንና መቅደስ ላይ ቆሞ የማለበትን አገልግሎት ለምን ረግጦ ጠፋ ብላችሁ ላዘናችሁ ሁሉ፤ አይናችሁን ክፈቱ እባካችሁ። እየኤል ሚካኤልን ላባ ጳውሎስ ለመሸጥ ተስማምቶ አቡነ ቅወስጦስን አስመጥቶ ሊያስረክብ ሲል ተነቅቶበት ሃሳቡ ሲከሽፍ ምእመኑም ተናዶ ከቦርድ እናስወጣው የሚል ክርክር በነበረበት ጊዜ የተናገረውን ትእቢት የረሳቸሁ ካላችሁ ላስታውሳችሁ እፈልጋለሁ “ ከቦርድ ካወረዱኝ ይህን ቤተክርስቲያን አዘቅት ዉስጥ ከትቸው ነው የምወጣው” ማለቱ ይፋ እንጅ ሚስጢር አልነበረም። ይሄም አባባል የንዴት ወይም የዛቻ ብቻ እንዳልነበረ የምትረዱት፤ ያን ጊዜ የቤተክርስቲያኑ ሂሳብ የሚመራው አንድ በሱ ሁለት በ አለማየሁ ሶስት በሌላ ማህበር ቅዱስን ተወካይ የቦርድ አባል እንደነበረና ከነዚህ ሁለቱ ብቻ በሚፈርሙበት ሰነድ የቤተክርስቲያኑ ሃብት ባዶ መሆን ይችል ነበር። ሚካኤል በጥበቡ ግን እዚያ ከመድረሱ በፊት ቀስ በቀስ ይሄን ሃይሉን እያመነመነ ምርጫ ደርሶ ደጋፊወች በማጣቱ የዛተበትን ተንኮል አቀዝቅዞ እንዲባረር አደረገው።
የሱ ጥሎ መጥፋት ገና ምርጫው መካሄድ እንደተጀመረ የተተነበየ እንደነበረ ለሁላችንም ግልጽ ነበር።
የሱ ብቻ መቅረት ከቤተክርስቲያኑ የሚያገኘው የስርቆት ገንዘብና ከኮንትራክተሮች ላይ የሚያገኘው የደላላነት ተግባር እንደተቋረጠ ሲያውቅ ካልሰረቅሁና ጥቅም ካጣሁ ለምንድነው በነጻ የማገለግለው በማለት መሆኑን ገና ሳይታወቅ የተፈታ ነበር።
አሁንም መልሳችሁ እንደሱ የመሳሰለ ሰው ለመምረጥ የምትቃጡ ካላቸሁ ቤተክርስቲያኑን አደጋ ላይ መጣላችሁን እንድታውቁት ይሁን አላለሁ።
ቤተክርስቲያናችንን የምንጠብቅበት አእምሮ ይለግሰን ዘንድ ሁላችንም ተንበርክከን እንጸልይ
አሜን!