Wednesday, June 30, 2010

ዝምታ ወርቅ አይደለም

የርሶ ብዕር አስተያየት ተሳትፎ ሕብረተሰባችንን ይጠቅማል ያሉትን አይንፈጉን ገንቢነቱ ቦታ ይኖረዋልና!


ማሳሰቢያ፡ ይህ ገጽ የተዘጋጀው የተለያዩ የኅብረተሰባችንን ሀሳብ ለመለዋወጫ እንጂ ለሚሰጡት ማንኛውም አስታየቶች በማንኛውም መንገድ ተጠያቂ አይደለም። ጉግል ድርጅትም ኃላፊነት አይወስድም። ኃላፊነቱ በሙሉ የአስታየት ሰጪው ብቻ ነው።





እንደምን አላችሁ?



የሚቀጥለውን ጽሁፍ የቸሩንን ታዳሚያችን ከልብ ምስጋና ይድረሳቸው፣ ብዙዎቻችን ከዚህ በፊት አንበነው ይሆናል ግን ምን ያህል ተረድተነው ይሆን? ለማንኛውም ደግመን በማስተዋል እናነበው ዘንድ እንጋብዛለን።



ዝምታ ወርቅ አይደለም





ሰውዬው ከሚስቱ ሌላ አንዲት ሴት ወደደና እፍ ክንፍ አለ፡፡ ልጁን እና ሚስቱን እየተወ ከዚህችኛይቱ ጋር ማምሸት፣ ብሎም ማደር ጀመረ፡፡ በመጨረሻም አንድ ቀን ወደ ሚስቱ መጣና ድንገተኛ የሆነ ጥያቄ አቀረበ፡፡ «እኔ እና አንቺ እንድንፋታ እፈልጋለሁ፤ ለምን ብለሽ ምክንያቱን አትጠይቂኝ፡፡ መፋታት ብቻ እፈልጋለሁ፡፡ ደግሞም ሌላ ቀን አይደለም፣ ነገ እንዲሆን እፈልጋለሁ» አላት፡፡ ሚስቱ በሁለት ነገሮች ተጨነቀች፡፡ በአንድ በኩል ምንም ነገር አትጠይቂኝ ብሏታል፡፡ በሁለተኛ ነገር ልጇ ወደ ዩኒቨርሲቲ የመግቢያ ፈተና ልትቀመጥ ጥቂት ቀናት ቀርቷታል፡፡



«ባልፈልገውም፣ ባልስማማበትም፤ ካልክ የግድ እቀበለዋለሁ፡፡ ነገር ግን በኛ ምክንያት ልጃችን መጎዳት የለባትምና የአንድ ወር ጊዜ ያህል እንታገሥ፡፡» አለችው፡፡ እርሱም አሰበና «ጥሩ አንድ ወር መታገሥ አያቅተኝም፤ ነገር ግን በዚህ አንድ ወር ውስጥ ሽማግሌ መላክ፣ ምክንያቱን መጠየቅ የለም፤ ስለ ፍቺው ማናችንም ምንም ነገር ማንሣት የለብንም፤ በዚህ ቃል ግቢ» አላት፡፡ እርሷም «እስማማለሁ፤ ግን አንተም የምነግርህን ለመፈጸም ከተስማማህ ነው፤ ታድያ በዚህ አንድ ወር ጠዋት ጠዋት ከዕንቅልፌ ስነሣ፣ ማታ ማታም ወደ አልጋዬ ስሄድ ያኔ የሠርጋችን ዕለት አቅፈህ እንደ ወሰድከኝ አድርገህ አቅፈህ ትወስደኛለህ» ስትል ጠየቀችው፡፡ ነገሩ ያልጠበቀው እና ያልተለመደ ዓይነት ቢሆንበትም፣ ቀላል እና ሊያደርገው የሚችል ስለሆነ እሽ ብሎ ቃል ገባላት፡፡



አንዱ ወር ተጀመረ፡፡



ጠዋት ጠዋት ከዕንቅልፏ ስትነሣ አቅፎ፣ ከፍ አድርጎ፣ ወደ በረንዳ ካደረሳት በኋላ ወደ ሥራው ይሄዳል፡፡ ማታ ማታም እንዲሁ አቅፎ ወደ አልጋዋ ይወስዳታል፡፡ ስለ ፍችው አይነጋገሩም፡፡ እየዋለ እያደረ ሲሄድ የሰውነቷ ጠረን፣ የምትለብሳቸው ልብሶቿ፣ የዓይኖቿ እና የፀጉሯ ሁኔታ፣ የገላዋ ልስላሴ እና የአካሏ ቅርጽ እየሳቡት መጡ፡፡ በየቀኑ እያቀፈ ሲያወጣት እና ሲያስገባት ሰውነቷ እየቀለለው፤ ለርሱም እርሷን አቅፎ መሸከሙ አንዳች እንግዳ የሆነ የደስታ ስሜት እየፈጠረለት መጣ፡፡



ከራሱም ጋር ሙግት ጀመረ፡፡ «ለምንድን ነው እንፋታ ያልኳት፤ አሁን የሚሰማኝን ስሜት ያህል ስሜት ከአዲሷ ወዳጄ ጋር ለምን አይሰማኝም? ለምንስ ነበር ይህንን ነገር እንዳደርገው ቃል ያስገባችኝ ? ይህን የመሰለውን ገላዋን፣ እንዲህ የሚማርከውን ጠረንዋን፣ እንዲህ የሚያስደስተውን ፈገግታዋን፣ እንዲህ የተዘናፈለውን ፀጉሯን፣ እንዲህ ልዩ የሆነውን አካሏን እንዴት እስከ ዛሬ አላስተዋልኩትም ?እርሷ ናት ከኔ ጋር የነበረችው ወይስ እኔም ከርሷ ጋር ነበርኩ?»



የወሩ መጨረሻ እየደረሰ መሆኑን ሲያውቅ ከእርሷ መለየቱ ጨነቀው፡፡ እንዲያውም ይህ ሁኔታ የፈጠረበትን እንግዳ ስሜት እየወደደው መጣ፡፡ ነግቶ እና መሽቶ እርሷን አቅፏት እስከሚወስዳት በጉጉት መጠበቅ ጀመረ፡፡ በሌላም በኩል ደግሞ በዚህ ድርጊቷ በውስጡ ያሳደረችበትን ስሜት እያሰበ ያደንቃትም ጀመር፡፡ ብልህነቷን፣ አስተዋይነቷን እና በቀላል ድርጊት ቀልቡን ልትገዛው መቻሏን ሲያስበው «ምን ዓይነት አስገራሚ ሴት ናት?» ይላል፡፡



ወሩ ሊያልቅ ሁለት ቀን ሲቀረው የመፋታቱን ሃሳብ በውስጡ መረመረው፡፡ ነገር ግን አላገኘውም፡፡ በዚህ ሁኔታ መፋታቱ ደግሞ ለሕይወቱ የማይፈታ ዕንቆቅልሽ እንደሚሆንበት እያሰበ ተጨነቀ፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ በዚህ አንድ ወር ውስጥ ፍችን በተመለከተ ላለመነጋገር ቃል ተግባብተዋልና እንዴት አድርጎ ይናገር፡፡ ዛሬም በደስታ ስሜት አቅፎ ከአልጋዋ እንደወሰዳት ሁሉ ማታ ወደ አልጋዋ መለሳት፤ ከበፊቱ እጅግ በጣም ቀለለችው፤ አሳዘነችውም፡፡



በወሩ መጨረሻ፡፡



ወደ አዲሲቱ ወዳጁ ዘንድ ሄደና «የፍችውን ሃሳብ ሠርዤዋለሁ፡፡ እኔና ባለቤቴ ፍቅር የሌለን መስሎኝ ነበር፡፡ እኛ ግን ለካስ ፍቅር አላጣንም፡፡ ያጣነው ሁለት ነገሮች ብቻ ነው፡፡ መነጋገር እና መቀራረብ፡፡ ለዚህ ያደረሰንም አለ መቀራረባችን እና አለመነጋገራችን ብቻ ነው፡፡ አሁን ግን መነጋገር ባንችል እንኳን መቀራረብ ግን ችለናል፡፡ ዛሬ ደግሞ መነጋገር እንችላለን፡፡ ስለዚህ ሌላ የሚሆንሽን ፈልጊ» አላት፡፡



ሴትዮዋ ተናደደችና በጥፊ መታችው፤ ከአጠገቧ የነበረውንም ውኃ ቸለሰችበት፤ «ይሄ ለብዙው ኃጢአቴ የተከፈለ ቅጣት ነው» እያለ ወጥቶ ሄደ፡፡ ከዚያም ወደ አበባ መሸጫ ሱቅ ውስጥ ገባ፡፡ ያኔ ሲጋቡ የገዛላትን ዓይነት አበባ ገዝቶ ወደ ቤቱ ከነፈ፡፡ «ጓደኛዬ ትዳር ማለት አግብተው የሚኖሩት ሳይሆን በየጊዜው የሚጋቡት ነው ያለው እውነቱን ነው፡፡ ትዳር እንደ አሥራ ሁለተኛ ክፍል ፈተና አንድ ጊዜ አልፈውት ሰርተፊኬቱን የሚሰቅሉት አይደለም ያለው እውነቱን ነው፡፡ ትዳር እና ተክል ክብካቤ ይፈልጋሉ፡፡ እንዲሁ ቢያድጉ ይደጉ ተብለው የሚተው ነገሮች አይደሉም፡፡



«ልክ እዚህ ሀገር ችግኝ የመኮትኮት፣ የማጠጣት፣ የመከባከብ እና የማሳደግ እንጂ የመትከል ችግር እንደሌለብን ሁሉ፤ እኛም ጋር የመጋባት ችግር የለም፡፡ ፍቅር ግን ማግባትን ብቻ ሳይሆን ማጠጣትን፣ መኮትኮትን፣ ማረምን፣ ከብት እንዳያበላሸው አጥር ማጠርን፣ በየጊዜው ማዳበርያ መጨመርን ጭምር ይፈልጋል፡፡ በርግጥ በዕድሉ የሚበቅል ዛፍ እንዳለው ሁሉ በእድሉ የሚኖር ትዳርም ይኖር ይሆናል፡፡ ይህ ግን ሕይወትን ለራስ ጥረት ሳይሆን ለአጋጣሚዎች ብቻ አሳልፎ መስጠት ነው» ያለው እውነቱን ነው፡፡ እኔ አልሰማሁትም እንጂ እርሱስ ተናግሮ ነበር፡፡»



መኪናውን አቆመና ወደ ግቢው ውስጥ ገባ፡፡ በረንዳ ላይ ትጠብቀው የነበረችው ባለቤቱ የለችም፡፡ በሩንም አንኳኳ፡፡ የሚከፍት ግን አልነበረም፡፡ ደግሞ ሲያንኳኳ ገርበብ ብሎ የተዘጋው በር በራሱ ጊዜ ተከፈተ፡፡ ባለቤቱ ግን በዚህች በወሩ ሠላሳኛ ቀን ሳሎንም የለችም፡፡ እየተገረመም፣ ግራ እየተጋባም ወደ መኝታ ቤቱ ዘለቀ፡፡ አልጋው ላይ ፈገግ እንዳለች ጋደም ብላለች፡፡ አበባውን እንደያዘ ጠጋ አለና በእጁ ጉንጯን ነካው፡፡ ቀዝቅዟል፡፡ በቁልምጫ ጠራት፡፡ መልስ ግን አልነበረም፡፡ ግራ ተጋብቶ ዓይንዋን ገለጥ አደረ ገው፡፡ ሊገለጥለት ግን አልቻለም፤ በርከክ አለና ሰውነቷን ደባበሰው፤ ቀዝቅዟል፡፡



«የመጨረሻው ቀን ነው፤ ይህችን ቀን ማየት አልፈልግም፤ ለልጄ ስል እስከዛሬ ታግሻለሁ፤ በቃኝ» የሚል ጽሑፍ ራስጌዋ ላይ አገኘ፡፡



እርሷ ፍችውን አትፈልገውም፤ ስለዚህም ሳትፋታ ሞተች፡፡ በርሱ ውስጥ የነበረውን የሃሳብ ለውጥ አላወቀችም፤ ምክንያቱም ላይነጋገሩ ቃል ተግባብተው ነበርና፡፡ እርሷ የዛሬዋን ቀን በስጋት እና በጭንቀት ነበር የጠበቀቻት፡፡ የመለያያቸው ቀን፤ የሕይወቷን ግማሽ የምታጣበት ቀን፡፡ የማትፈልገውን ነገር የምታደ ርግበት ቀን ናትና፡፡ እርሱ ግን የዛሬዋን ቀን በጉጉት ነበር የጠበቃት፡፡ የሚነጋገሩባት ቀን፤ ፍችውን እንደተወው የሚነግርባት ቀን፤ ፍቅሩን የሚነግርባት ቀን፤ ይቅርታ የሚጠይቅባት ቀን፤ ለፍቅሩ ሲል ትንሽም ብትሆን ቅጣት ከፍሎ የመጣባት ቀን፤ በእርሱ እና በባለቤቱ መካከል የመነጋገር እና የመቀራረብ እንጂ፣ የመዋደድ እና ስሜት ለስሜት የመስማማት ችግር እንደሌለ መረዳቱን የሚገልጥባት ቀን ናትና፡፡ ግን ምን ያደርጋል፤ ሁለቱም ይህንን በየልባቸው ያውቁታል እንጂ አልተነጋገሩም፤ ሃሳባቸውንም በሌላ መንገድ አልተለዋወጡም፡፡ በዚህ የተነሣም በችግሩ መፍቻ ቀን ዋናው ቸግር ተፈጠረ፡፡



ሁለት የትዳር ነቀርሳዎች፡- አለመቀራረብ እና አለመነጋገር፡፡ አብረው አንድ አልጋ ላይ እያደሩ፤ አብረው እየበሉ፤ አብረው እየኖሩ የማይቀራረቡ ባል እና ሚስት አሉ፡፡ አንድ አልጋ ላይ የሚተኙት አንድ አልጋ ላይ መተኛት ስላለባቸው ብቻ ነው፡ ከመጋባታቸው በፊት የነበራቸው ጉጉት እና ናፍቆት አሁን የለም፡፡ ሳይተኙ እንቅልፍ ይወስዳቸዋል፡፡ አብረው ይበላሉ፤ በአንድ ማዕድ መሆኑ፣ አንድ ጠረጲዛ ላይ መሆኑ እንጂ ያኔ በፊት ለምሳ ሲገባበዙ የነበረው ናፍቆት እና ጉጉት የላቸውም፡፡ ዝም ብሎ መብላት ብቻ፡፡



እያንዳንዷን ቀን ልዩ፣ ደስታ የሚፈጠርባት እና ከትናንት የተለየች ለማድረግ አይጥሩም፡፡ ዛሬም እንደ ትናንቱ፣ ነገም እንደ ዛሬ ነው፡፡



በስንት ልመና በስንት ጥየቃ፣

በስንት ደጅ ጥናት በስንት ጥበቃ፣

እንግዲህ ምን ቀረሽ አገባሁሽ በቃ፣



እንደተባለው ይሆንባቸዋል፡፡ አገባኋት በቃ፤ አገባሁት በቃ፤ ከንግዲህ ምን ቀረ? ብለው ያስባሉ፡፡ ሰው ተፈጥሮ አላለቀም፡፡ በየጊዜው ነው የሚፈጠረው፡፡ ፈጣሪም ሰውን እንደ ተወለደ እንዲያልቅ አላደረገውም፡፡ በየቀኑ፣ በየሰዓቱ፣ በየደቂቃው ላስተዋለው ሰው እንግዳ ፍጥረት ነው፤ አዳዲስ ነገር ይታይበታል፡፡ ይህ ግን መቀራረብን ይጠይቃል፡፡ ባል እና ሚስት ከተቀራረቡ ሳይፋቱ በየቀኑ ይጋባሉ፤ ጋብቻቸው እየታደሰ ይሄዳል፡፡ የትናንቷ ሚስት ከዛሬዋ ትለያለች፤ የዛሬው ባልም ከትናንቱ የተለየ ነው፡፡ ለውጥ፣ ዕድገት፣ ብስለት፣ አለ፡፡ መልክም ተለውጧል፡፡ ግን ቀርቦ የሚያየው ያስፈልገዋል፡፡



የዚያ ባል ችግሩ ሚስቱን አግብቷት እንጂ ቀርቧት አያውቅም ነበር፡፡ አብሯት ይኖራል እንጂ ከርሷ ጋር አይኖርም ነበር፤ ምድር በፀሐይ ዙርያ ስለምትዞር ይመሻል ይነጋል እንጂ በእነርሱ የተለየ የሕይወት ጉዞ ምክንያት አይመሽም አይነጋም፡፡ በማክሰኞ እና በረቡዕ መካከል ከስሙ በቀር በሕይወታቸው ውስጥ ልዩነት የለውም፡፡



ሌላው ችግር ደግሞ ያለ መነጋገር ነው፡፡ መነጋገር ማለት በሚያውቁት ቋንቋ ማውራት ማለት አይደለም፡፡ እርሱንማ ከብትም ሲገናኝ እምቧ እምቧ ይባባላል፡፡ ይህ ግን መነጋገር አይደለም፡፡ በየጊዜው፣ በየሰዓቱ፣ ሁለመናን መለዋወጥ ማለት ነው፡፡ ካልተነጋገሩበት የምሥራች፣ የተነጋገሩበት መርዶ ይሻላል፡፡ ካልተነጋገሩበት ፍቅር የተነጋገሩበት ጠብ ይበልጣል፡፡ ካልተነጋገሩበት ስጦታ የተነጋገሩበት ንጥቂያ ይሻላል፡፡



ባል እና ሚስቱ ባለመነጋገራቸው ችግሩን በሁለት አቅጣጫ ፈቱት፡፡ የሁለቱም ፍላጎት ችግሩን ላንዴ እና ለመጨረሻ ጊዜ መፍታት ነበር፡፡ የሁለቱም ፍላጎት ፍቺ የሚባለውን ነገር ላለማየት ነበር፡፡ የሁለቱም ፍላጎት ሠላሳኛዋን ቀን መገላገል ነበር፡፡ ነገር ግን ባለ መነጋገር ምክንያት በሁለት አቅጣጫ ሆነ፡፡ እርሷ ሞትን መረጠች፤ እርሱ ደግሞ ይቅርታን መረጠ፡፡ ችግሩ የመጣው በዚህ ጉዳይ ላለመነጋገር ሲወስኑ ነው፡፡ እርሷ በጉዳዩ ትጨነቃለች፤ ለምን ይሆን ከኔ መለየት የፈለገው? የሚለው ጥያቄ ያሳስባት ነበር፡፡ በሃሳብ ብዛትም እየከሳች ሄዳ ነበር፡፡ ለዚህም ነበር በየቀኑ ሲያቅፋት ትቀልለው የነበረው፡፡ እርሱ ግን መቅለሏን እንኳን ለመጠየቅ ፈራ፡፡ እርሱ ከራሱ ጋር እንጂ ከእርሷ ጋር አይነጋገርም ነበር፡፡



እናም አንዳንድ ጊዜ አስፈላጊ ቢሆንም እንኳ፤ በትዳር ውስጥ ግን ዝምታ ወርቅ አይደለም፡፡







ከዲዳለ





እርሶስ ምን ይላሉ?

Sunday, June 27, 2010

ሰላም ለሁላችሁም ይሁን

የርሶ ብዕር አስተያየት ተሳትፎ ሕብረተሰባችንን ይጠቅማል ያሉትን አይንፈጉን ገንቢነቱ ቦታ ይኖረዋልና!

ማሳሰቢያ፡ ይህ ገጽ የተዘጋጀው የተለያዩ የኅብረተሰባችንን ሀሳብ ለመለዋወጫ እንጂ ለሚሰጡት ማንኛውም አስታየቶች በማንኛውም መንገድ ተጠያቂ አይደለም። ጉግል ድርጅትም ኃላፊነት አይወስድም። ኃላፊነቱ በሙሉ የአስታየት ሰጪው ብቻ ነው።



ሰላም ለሁላችሁም ይሁን


ትሮፒካል ድፕሬሽን አሌክስ እስኪያልፍ ምክንያት ተገኝቶ ወደ ደረቅ መሬት ስለወጣን፤አንድ የምናውቅው ለብዙ ጊዜ የዳላስ ነዋሪ የሆነውን በስልክ አነጋግረነው ነበር። ከሰላምታም በኃላ ብዙ ከተጨዋወትነው ውስጥ አሁንም የወያኔ ኢትዮጵያ ቀን በአል ፤ በጥብቅ የአካባቢው የኢትዮጵያ ተወላጅና የኢትዮጵያ ወዳጆች ሁሉ ግምባር ፈጥረው  እውነተኛ የኢትዮጵያ ቀን በሀቀኛ የኢትዮጵያ ተወላጆች እስኪመቻች ድረስ ጠብቀው እንዲታገሉና ከአድር ባይ ፣ ቅጥርኛ ፣ ባንዳና መሰሎቻቸው ዝግጅት እንዲገለሉ መልእክታችንን እናስተላልፋለን።

በኛ መራቅና ዝምታ የብዙዎቻችሁን ቅሬታ ጽሁፎች ደርሰውናል። ስለተሳትፎዎቻችሁ ሁሉ ከልብ እናመሰግናለን ፣ ባገኘናቸው እድሎች ሁሉ አንባቢዎቻችንን ከማገልገል ወደ ኃላ አንልም፤ ነገር ግን አሁንም ለዳላስ ነዋሪ የሚበቃ የብሎግ አቅራቢ አናሳ ቁጥር አድጎ የማየት ምኞታችን እውን እስኪሆን ድረስ እንደጥያቄዎቻችሁ መሰረት ከርቀት ብቅ ጥልቅ ለማለት እንሞክራለን።

የደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ካቴድራልን በተመለከተ ደብሩና ምዕመናኑ ምህላ ላይ ስለሆኑ እኛም ባለንበት ሁሉ ከጎናቸው በመሆን የነሱን ዕንባ፣ ፀሎትና ምህላ አብረን በማቅረብ እንካፈላለን። ይህ አምዳችንም ይህን በተመለከተ በአዘጋጆቹ የሚቀርቡትን በጥንቃቄ ከነቀፌታ አርቆ ፣ ሕዝበ ክርስትያኑን አቀራርቦ ፣ ሰላምን በምዕመኖቹ መካከል ወርዶ ፣ ይቅር ለእግዚሐብሔር ተባብሎ ፣ አንድ አምላክን በሕብረት ለማምለክ ወገኖቻችን እንዲበቁ  ለመተባበር ተዘጋጅተናል። በአንጻሩም ከአንባቢዎቻችን የሚደርሱንን ለማውጣትና ሕብረትሰቡ የራሱን ሚዛን የመውሰድ መብቱን እንጠብቃለን።

ቀድሞ አንድ ነገር ሲሆን ወሬ ከወዲያ ብሎግ ከንፋስ ይቀድም ነበር ፣ እንግዲህ ስብስባቸው 24 ሰአት ካለፈው ነው እኛም የጣፍነው፣ ወይ እንደ ሰንበቴው ብሎግ ትንቢት፣ አሊያም ሌላ ይሆን? ወይስ እኛን ያስተማረን የመከረን አምላክ የቀረበውን ምህላ መልስ ሰጥቶ የነሱንም ልቦና ለውጦ  ይሆን?

እርሶስ ምን ይላሉ?

Monday, June 21, 2010

ሰላም ዳላስ

የርሶ ብዕር አስተያየት ተሳትፎ ሕብረተሰባችንን ይጠቅማል ያሉትን አይንፈጉን ገንቢነቱ ቦታ ይኖረዋልና!

ማሳሰቢያ፡ ይህ ገጽ የተዘጋጀው የተለያዩ የኅብረተሰባችንን ሀሳብ ለመለዋወጫ እንጂ ለሚሰጡት ማንኛውም አስታየቶች በማንኛውም መንገድ ተጠያቂ አይደለም። ጉግል ድርጅትም ኃላፊነት አይወስድም። ኃላፊነቱ በሙሉ የአስታየት ሰጪው ብቻ ነው።


ሰላም ዳላስ

ብዙዎቻችሁን በዚች አምድ አጭር ቆይታ ለተሳትፍዎቻችሁ ከልብ እናመሰግናለን። መወያየት ካልተቻለ መተቸት እንደአጸያፊ ተደርጎ በባሕላችን ይቆጠራል ። ብዙውን መጣጥፍ የመጣው ከናንተው ተሳትፎ ነው።

በጥቂት አመት የዳላስ ቆይታችን ብዙም ከሕብረተስቡ ጋር ሳንቀላቀል በጣት የሚቆጠሩ ግለሰቦችን ለመተዋወቅ ቢያበቃንም ለኮሚኒቲው እንግዳ ሆነን ነበር። በኛ ግንዛቤ ሕብረተሰቡ እርስ በራሱ ተጠራጣሪ፣ ለማወቅ ከመፈለግ ይልቅ እንደሚያውቅ ራሱን ማድረግ፣ ከስህተት አለመማርን፣ ችግሮችን በቀና መንፈስ ተወያይቶ መፍትሔ አለመፈለግን፣ በተለየ ዩልኝታ የሚባለው ነገር ፣ አስመስሎ ማደር፣ ሀቅን አለመቀበል፣ በሰሩት ስማቸው በነቀፋ መውጣቱ የሚቆጫቸውን፣ ወዘተ…… ከሚደርሱን መልዕክቶች ተረድተነዋል።

እኛ ደግሞ በተለያየ የአሜርካን ግዛት በስራ ምክንያት በቆየንበት ቦታ በብዛት የኢትዮጵያ ተወላጆችን ሳናይ አመት የቆጠርንበትን ጊዜ ፣ ፈጣሪ ምስጋና ይግባውና የእንጀራ ናፍቆታችንን አሁንማ በፌዴክስ እየተወጣን፣ ቅዳሴ በድሕረ ገጽ እያካሄድን ፣ ኸረ ስንቱን ቆጥረን…….እናንተ ግን ፈጣሪ በብዙ የሰጣችሁ ፤ መቻቻል የሚባለውን መተግበር ያቃታችሁ ፣ እስቲ ወደ ኃላ ዞር ብላችሁ የመጣችሁበትን ቀዬ ወይንም መንደር በዐይነ ህሊናችሁ ቃኙ? ሕብረተሰቡ እንዴት ነው የሚገኘው? በሰው ሀገር መጥታችሁ በሕብረት ያከናወናችሁትን ለምን በመናናቅና ባለመስማማት ታጠፉታላችሁ? ተረጋጉ ፣ ተደማመጡ ፣ በቅንነት ተወያዩ ፣ ለአዲስ አመለካከት ሕሊናችሁን አዘጋጁ ፣ በየጊዜው የሚነሱትን የጋራ ችግሮች ሁሉ በወቅቱ አስተናግዱ ለወደፊቱም ቅድሚያ ዝግጅት አድርጉ፣ በኃላፊነት የምትመርጡትን የተከታታይ አገልግሎት ዘመኑን ከሁለት ጊዜ በላይና ቢያንስ የአምስት አመት ዕገዳ ዳግመኛ ለመመረጥ ቢሆን የበለጠ ፍሬ ይኖረዋል የሚል ግምት አለን። በተለይም ከዘመኑ የቴክኖሎጂ ዕውቀት ጋር የሚራመዱትና ዘመናዊ ትምህርት ያላቸውን መቀላቀሉ ጥቅሙ ከፍ ያል ይሆናል ብለን እናምናለን።

ይህቺ አምዳችን በአንባቢዎቻ ድጋፍና በሚሰጡት ጽሁፎች የተመታችሁ፣ የቆሰላችሁ ፣ ያዘናችሁ ሁሉ በሰጣችሁን አስተያየት ስለተሰማችሁ ሁሉ አምዳ ከልብ ይቅርታ ትጠይቃለች። ያለ አግባብ በዚህ አምድ ምክንያት የታማችሁ፣ ጣት የተጠነቆለባችሁ ፣ ንጹህነታችሁና መብታችሁ የተነካባችሁ ሁሉ ይቅርታ እየጠየቅን በዳላስ አካባቢ የእንደዚህ አይነት መወያያ መድረክ አስፈላጊነቱ በሚገባ የምናምንበት ስለሆነ ሌሎችም እንዲቀጥሉበት እናሳስባለን!

በመጨረሻም የውቂያኖስ ሳይንስ፣ የተፈጥሮ ጥበቃ ሳይንስ፣ የውቂያኖስ ጥበቃና መከላከል ምርምር ሳይንስ፣ የዘይት ሀብት ልማትና ጥበቃ ምህንድስና፣ በውቂያኖስ ውስጥ ጥልቅ የዘይት ፍለጋ ምርምርና በመሳሰሉት ሙያ ዕውቀት ያላችሁ ወገኖች በአማካኝ የ36 ወራት የስራ ዕድል በደቡብ ምስራቅ የባሕር ሰላጤያችን በጥብቅ ይፈለጋልና ይህ መልክት ይድረሳችሁ። በተረፈ በዚህ የመጨረሻ የዳላስ አካባቢ ምሽታችን ስንብት ስናደርግ ፤ ከገልፉ አሳ ተርፈን የሄድንበትን አጠናቀን የት እንደምንሰፍር ባናውቅም በቆይታችን ከጎበኘናቸው የኢትዮጵያ ምግብ ቤቶች በንጽህና ፣ በዋጋ እንደዚሁም በአገልግሎት ለአዲሱ አይቤክስ ብናደላም ገና ብዙ ይቀረዋል ፣ የሚቀጥለው አዲስ አበባ ሲሆን የተቀሩትም በሚገባ ደረጃ የሚመዘኑበትና የሚሻሻሉበት መንገድ እንዲወስዱ ከዚሁ እንጠቁማለን። በተረፈ በመካከላችሁ ሰላም ወርዶ በፍቅርና በመተሳሰብ ለጋራ እድገት እንድትቆሙ ከልብ እንመኛለን።


ሰላም ዳላስ  

ከድጡ ወደ ማጡ

የርሶ ብዕር አስተያየት ተሳትፎ ሕብረተሰባችንን ይጠቅማል ያሉትን አይንፈጉን ገንቢነቱ ቦታ ይኖረዋልና!

ማሳሰቢያ፡ ይህ ገጽ የተዘጋጀው የተለያዩ የኅብረተሰባችንን ሀሳብ ለመለዋወጫ እንጂ ለሚሰጡት ማንኛውም አስታየቶች በማንኛውም መንገድ ተጠያቂ አይደለም። ጉግል ድርጅትም ኃላፊነት አይወስድም። ኃላፊነቱ በሙሉ የአስታየት ሰጪው ብቻ ነው።




ከድጡ  ወደ ማጡ
ጠንካራ ዲፕሎማቶችና ኤምባሲዎች ያስፈልጋሉ
SUNDAY, 20 JUNE 2010

ይህ ከዚህ በላይ የተጠቀሰው ቀንና ጥቅስ የወሰድነው ‘ሪፓርተር‘ እየተባለ በኢትዮጵያ ውስጥ በመንግስት እየተረዳ የሚወጣ ገጽ ነው። ይኸው ገጽ በርዕሰ አንቀጹ እንደጠቀሰው ያሉትን የዲፕሎማቲክ ሕብረተሰቦችን በበለጠ ዘመቻቸውን እንዲያጠናክሩ ለመግፋት ሲሆን ፣ በዚህ ባለንበት ከተማም ወኪሎቻቸው ያነጣጠሩት በራሳቸው ዜጎች ላይ ብቻ ነው።

እነዚህ ወኪሎቻቸው ከእውነተኛው የዲፕሎማቲክ ስራ አልፈው በከተማችን ውስጥ የተቆቃሙትን የሀይማኖትና የሲቭክ ድርጅቶች ውስጥ ሰርገው በመግባት ሕብረተሰባችንን በመከፋፈል ለመቆጣጠር ያላሰለሰ ፍለሚያ ውስጥ ይገኛሉ። ከዚህም በቅርቡ በዳላስ ደብረ ምህረት ቅዱስ ሚካኤል ካቴድራል በሜይ 2 የተፈጠረው ሁከት በግምባር ቀደምትነት ያስተባበሩና ተሳታፊ የነበሩት ውስጥ ሶፍያ ዘሪሁንና እህታ የሺ ዘሪሁን የተባሉት ወያኔዎች ወንድማቸው የቀድሞ የዚሁ ከተማ ነዋሪ የነበረና አጎታቸውም ከፍተኛ የኢትዮጵያ ባለስልጣን ቤተሰብ ፤ የተፈጠረውን አጋጣሚ በመጠቀም ለመንጠቅ ወይም ለማፍረስ የፈጸሙት ተግባር የቅርብ ጊዜ ትውስታ ነው። የቤተክርስትያኑ ለጊዜው ቢከሽፍም በወኪሎቻቸው አማካኝነት የማይፈነቅሉት ድንጋይ የለም። ከዚህ ባሻገር በዳላስ የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ መረዳጃ ማኅበር ውስጥ እንደ አሸን ፈልተው ድርጅቱን ተቆጣጥረው ይገኛሉ። ይኸው የማሕበረሰቡ ድርጅት ሁልጊዜም አንገቱን ቀና ማድረግ ያልቻለው በየጊዜው በአመራር ላይ የሚጠላጠሉት የሚፈጽሙት ተግባር በግል ለሚያምኑበት ርዮተ አለም እንጂ ለኮሚኒታችን አንድነትና እድገት ያደረጉት አስተዋጽዎ በጣም ውስን ነው።

በአሁኑ ሰአት ሁለት አመት ያስቆጠረው እድርም ቢሆን በጥበብ የተዋቀረ ቅርንጫፍ የአባላትን ቁጥር ለመጨመር ሆኖ ከዚሁም በሚገኘው ገቢ፣ ድርጅቱን እድሜ ለማራዘም በዚያም የኢትዮጵያን ተወላጆች አንድነትና ሕብረትን ለመበታተን ከፍተኛ መሳሪያ አድርጎ መጠቀሚያ ለማድረግ ነው። ምክንያቱም ይህ እድር የተባለው ቅርንጫፍ አካል የሚያስከፍለው ገንዘብና የሚሰጠው ግልጋሎት በፍጹም የማይገናኝ ነው። ምክንያቱም በዚህ ክፍለ ንግዱ ዘርፍ የተሰማሩት የኢንሹራንስ ድርጅቶች የሚሰጡት ግልጋሎትና ክፍያ እጅግ በጣም የበለጠ ብቻ ሳይሆን ኮሚኒቲውን ከሚያስከፍለው ዋጋ እጅግ በጣም ያነሰና በሕግም ቀጥተኛና ተቀባይነት ያለው ነው። በዚህ አይነት ኢንሹራንስ ተጠቃሚ የሆናችሁ ወጎኖች በተለይ በዚሁ ዙርያ አስተያየታችሁን በዚህ አጋጣሚ እንድታካፍሉን እንጋብዛለን? እኛም ወደፊት የምናገኛቸውን የዚሁን ንግድ ዘርፍ ጥቅምና ክፍያውን በተመለከት ልናካፍላችሁ እንፈልጋለን።

ሌላው የዚሁ ኮሚኒቲ ልሳን ነኝ የሚለው የራድዮ ክፍል በሁለት ቢላዋ የሚበላ ክፍል ነው። አዘጋጁም ቢሆን ለረዥም ጊዜ በዚሁ ዘርፍ ከመቆየቱ የተነሳ ይመስላል አስተዋጽዎ ለኮሚኒቲው አስመዝጊቤአለሁ የሚለው የረባ የለውም፣ የግል ጥቅሙን አካበተበት እንጂ። በተለይም ለብዙ ግዜ ጸረ- ወያኔ አስመሳይ ዘመቻ ያደርግ በነበረበት አንደበቱ ዛሬ ተቀልብሶ እነዚህ የወያኔና ወኪሎቻቸው በከፈቱት ጸረ- ኦርቶዶክስ ፣ ጸረ-ሀይማኖት ፣ ጸረ-አንድነት ግብር ተካፋይነቱን በዚሁ ራዲዮ ፕሮግራም እያስመሰከረ ይገኛል። በማንኛውም የነሱ ስብስባ በመገኘት እንደ ሪፖርተር ሳይሆን እንደአማካሪና እንደ ሕዝብ ግኑኝነት ተጠሪም እያደረገው ከመሆኑ በላይ በያዘው የራዲዮ ፕሮግራም ጭምር የነሱን ሰይጣናዊ ተልዕኮ ማስታወቂያ አድርጎት ይገኛል። እርሱም ሆነ የድርጅቱ ተመራጮች ከቀን ወደ ቀን የሚወስዱት ጸረ- ሚካኤል ምግባር በሁለቱም መካከል ቆይቶ የነበረውን መተባበር ከመጉዳት አልፎ በከፍተኛ ፍጥነት እየገታው ይገኛል። ድርጊታቸው ሁ ሉ ከድጥ ወደ ማጡ እንዲሉ ሆናል።

የኮሚኒቲው መሪዎችም ቢሆኑ እስከ ዛሬ ድረስ በቤተክርስትያን ውስጥ ተፈጥሮ ስለነበረው ችግር ለኮሚኒቲው አቁዋም ያልገለጠ ሲሆን እንደዚሁም በወቅቱ ሜይ 2 የድርጅቱ ሊቀ መንበር በቤተክርስትያኑ ውስጥ መገኘቱ ብቻ ሳይሆን የሰጠውም አስተያየት በሙሉ ሁካታ ፈጣሪዎቹን ደጋፊነቱን ያረጋገጠ ነበር። ከዚህም በተጨማሪ በኢትዮጵያ ውስጥ በቅርቡ ተጠናቀቀ ለተባለውና በአይነቱ አቻ ያላስመዘገበው የመንግስት ሕዝባዊ ምርጫ ውጤትን አስመልክቶ ለምን መግላጫ አላወጣም፣ ለኮሚኒቲው አባሎች በትውልድ አገራቸው ውስጥ ስላለው ሶሲዎፖለቲክም ሆነ ኢኮኖሚያዊ ወይንም ስላለንበት ሀገር አስመልክቶ የሕብረተሰባችንን ግንዛቤ ለምን ሊያጎለብትና ካለው የሌላው መጤ ሊያስተካክል አልቻለም ተብሎ ለሚነሱ ጥያቄዎች ሁሉ እስከ ዛሬ መልስ ያልሰጠ ድርጅት ነው።

ከጥቂት አመታት በፊትም ለግል ጥቅማ ጥቅም ሆነ ለወያኔ ባደሩ ቅጥረኞች፣ የጡረታ ዕድሜ የደረሱና ወደ ትውልድ ሀገራቸው መመለስ የሚፈልጉ፣ እንደዚሁም ወያኔ ባንዳዎችን ቁጥራቸው በዚሁ ድርጅት ውስጥ ከመቸውም በላይ ጨምሮና አመራሩን ተቆጣጥሮ ይገኛል። በየአመቱ መከበር የተጀመረውንና በቅርቡም የኢትዮጵያ ቀን
ተብሎ የሚከበረውን አመታዊ በአል የወያኔ ኢትዮጵያዊ ቀን ለማድረግ የቅድሚያ ዝግጅቱን ጀምሮ ይገኛል። ለዚሁም መነሻ መድረክ ያደረገው ድሪምስ የምሽት መጨፈሪያ ቤትን ነው። የዚሁ ምሽት ቤት ባለቤት ደግሞ ለወያኔ የሚሰራ  ፤ በከተማችን ውስጥ የሚገኘውን ማንኛውንም የኢትዮጵያ ተወላጆችን ያቀፈ የሀይማኖትና የሕብረተሰቦች አገልግሎት ሰጪ የሆኑትን ድርጅቶችን ለወያኔ ማስረከብ ወይንም ማጥፋት ስራዬ ብሎ የተነሳው ሀይሉ እጅጉ (ቀዩ ሰይጣን) የሚባለው ነው። በቅርቡም  ዳላስ ደብረ ምህረት ካቴድራልን ለዚሁ አላማው ሰለባ ለማድረግ ከግብር ቢጤዎቹ ጋር በማበር የተለያዩ ስብሰባዎችን በማዘጋጀት ፣ በመቀስቀስ፣ በማሳደም ፣ ሁከቶች እንዲቀሰቀሱ ፣ የሀስት ክሶች በቤተክርስትያን ላይ እንዲመሰረቱና ሲረቱም ይግባኝ እንዲሉ፤ ከዚህም አልፎ አባል ያልሆኑ ደግሞ አዲስ ክስ እንዲመሰርቱና መሳይ ተግባራትን በቀንዳምነት የሚያካሂድ የሕብረተሰባችን ጸር የሆነ ግለሰብ ነው።

በዚህ መልኩ ለተዋቀረ ድርጅትና ተግባር መሳተፍ አሉታ ብቻ ሳይሆን ሕሊናን እንደ መሽጥ ያስቆጥራል። እንደ ኢትዮጵያ ተወላጅነታችን የማንነታችን መታወቂያ የሆኑትና ብርቅዬ ክብራችንን ማስደፈር ልንፋለመው የሚገባን አበይት ምግባር ነው።


እርሶስ ምን ይላሉ?

Saturday, June 19, 2010

አይ ሜይ 2

የርሶ ብዕር አስተያየት ተሳትፎ ሕብረተሰባችንን ይጠቅማል ያሉትን አይንፈጉን ገንቢነቱ ቦታ ይኖረዋልና!

ማሳሰቢያ፡ ይህ ገጽ የተዘጋጀው የተለያዩ የኅብረተሰባችንን ሀሳብ ለመለዋወጫ እንጂ ለሚሰጡት ማንኛውም አስታየቶች በማንኛውም መንገድ ተጠያቂ አይደለም። ጉግል ድርጅትም ኃላፊነት አይወስድም። ኃላፊነቱ በሙሉ የአስታየት ሰጪው ብቻ ነው።







አይ ሜይ 2

እንደምን ከረማችሁ? አንዳንዴም በመካከላችን ሆነ ብለው ይሁን ወይ ዘግቶባቸው ነገር የተማታባቸው ፤ ተነፈስ ብለውም ጤና የማይሰጣቸው ፤ ከመጥፎ  ተግባርም የማይለዩና ድንግርግር ያለባቸው አልፎ አልፎ በሕብረተሰባችን ውስጥ ብቅ ጥልቅ ማለታቸው አይቀርም። ለዚህ መነሻ የሆነን ደግሞ ጋሼ ተኮላ (ተኩላ) Looser  በገጹ እንደለመደው ጫፍ ይዞ መሮጡን አላቃረጠም።

እሱና የሱ የተግባር ቢጤው በከሰሱት ጉዳይ ላይ ቀደም ሲል ፍርድ ቤት ዳኛው በጊዜአዊነት በሰጠው ትእዛዝ ላይ የዳኛው ውሳኔ ያለአግባብ በኃይማኖት ውስጥ ጣልቃ ገብታል፣ ይህም ጉዳይ ጊዛዊነቱ ይጎዳኛል ስለዚህም ሕግ ከሆነ ቁዋሚ አልያም ይሰረዝ በማለት ያመለከተው በውቅቱም ጉዳዩን ለተመለከተው ዳኛም ያሳወቀ ሲሆን፤ እስካሁንም ያልፈጸመው የተባለው ጊዛዊ ትእዛዝ በዳኛው እስኪፈረም ጠብቆ ነው። ምንም ኣዲስ ነገር የለውም። መቸም አይገባህምና እናስረዳህ። በየደረስክበት የተናገርከውና የፈጸምከው ማስረጃ እያሳደደ ያባንንሀል መሰለኝ ከታቦት መጣላት እንዲ ያደርጋል።
ሊያው ይኼ አንተን አይመለከትም፣ ጉዳዩ የሚታየው በይግባኝ ሰሚው አካልና በቤተክርስትያኑ መካከል ብቻ ነው።

2ኛ/ ከዚህ በፊት ስላለው ክስም ቢሆን በከሳሽ ለተከፈተው የብይን ይግባኝ፣ ከሳሽ ሲያጛትተው ከቆየ በኃላ በመጨረሻው የይግባኝ ማኅደር ያስገባውን ዝርዝር በተመለከተ የቤተክርስትያኑ የሕግ አማካሪዎች ቡድን ተመልክቶ ጉድፍ አግኝቼበታለሁና ለዚህ መልስ የመስጠት መብቴ ይጠበቅልኝ ባለው አንቀጽ መሰረት ይግብኝ ሰሚው ስለፈቀደለትና ይህንኑ የገደብ ቀን የሰጠው መሆኑን በስተቀር እንደ Looser ገጽ ተአምር የተፈጠረ አይደለም። የተረፈው የተለመደው የአዞ እንባ ለቅሶ ብለን እናልፈዋለን።

እንደዚህም በሜይ 2ቱ ሁከት ቀንደኞችና ከዚሁ ደብር ቀደም ብሎ ያለብቃቴ ቄስ ሆንኩኝ ብሎ ከማስተማር የአገለግሎት መድረክ በመኮብለል ቅስናውን ያፈረሰው መስፍን ከደብራችን አጥር ሥር  ካልጠፋ ቦታ ነገር ፍለጋ በመጽሀፍ ቅዱስ ስም መንቀሳቀሱን ልሳናቸው በሆነ የከልት ገጻቸው ይናገራል። ከዚሁም ጋር ከካድሬው ሲደልል ጋር እንደልተለያዩም ሊያስተባብል ሞክሮአል።

ሌላው ሳንነካ የማናልፈው ቢኖር ባለፈው ስላቀረብነው የኢትዮጵያን ቀን ቅድመ ዝግጅት ስብሰባ ጥሪ በተመለከተ ሕብረተሰባችን እየተወያየበት ሲሆን ከኮሚኒቲው ጽ/ቤት እስካሁን የተሰጠ መግለጫ የለም።
እኛም በቅርቡ በአምዳችን ግምባር ላይ ብቻ ሳይሆን ዘመቻችን አድማሱን እናሰፋዋለን።

በሌላ በኩል ጸረ ኦርቶዶክሶች ሆነው የቀሩት ጥቂት የሕብረተሰባችን ግለስቦች ተልኮዎቻቸው ሁሉ እየፈረሰባቸው በመምጣቱ ያጠፉት ጊዜና ገንዘብ እየቆጠቆጣቸው የስነልቦና ችግር  እንደዚሁም ጸጸት ውስጥ ገብተው ይገኛሉ። አንዳንዶችም ይህ አምዳችን የመነዠጋቸው ሲቅበዘበዙና ጣታቸውን በአላፊ አግዳሚው ላይ ሲቀስሩ ይታያሉ። ስማቸውን ጠቅሰን በመተቸታችን፣ ስማቸው ከእምነታቸው ብለውም የተቀበሉት ስጋዎደም በላይ፣ አድርገው መቁጠራቸውን እያስመሰከሩ ይታያሉ። ይህ አምድም ምን እንደሆነም ምንም ሊገባቸውም ስላልቻለ፣ በጭንቅላታችሁ የያዛችሁትን እምነት ወደ ልባችሁ አስገቡ፣ እንደ ቃሉ ማንም ፍጹም የለምና ሁላችንም በደለኞች ነን ነገር ግን ምህረት በሱ ብቻ ነውና ወደ ዕውነት መንገድ እንግባ እንላለን። ይህን ደብር ስናቁዋቅም በወቅቱ ከፖለቲካ ጋር ሳንለየው ቀርተናል። ነገር ግን ጊዜውን ጠብቆ የፖለቲካው ስራ መለያየት ሲጀምር፣ ከስራችን ሳናውቀው የበቀሉ ከልቶች ሲያብቡ፣ በሙያቸው የሚቀጠሩት የሀይማኖት አባቶች (ባለሙያዎች) ካለንበት ጊዜና አጠቃላይ ሁኔታዎች ጋር ያለመጣጠምና የአቀጣጠር ሂደት፣ በየጊዜው የሚፈጠሩትን ችግሮች በወቅቱ እንደመፍታት ስናለባብስ ከአንድ ቦርድ ወደሌላው ስናሸጋግር፣ ጉልቻው ቢለዋወጥ ወጥ አያጣፍጥም እንዲሉ አስተዳደሩ በተመሳስይ አስተሳሰብ ባላቸው የተወሰኑ አባላት እጅ ብቻ በመሽከርከሩ የተወሳሰቡ ችግሮች ይዘን ለዚህ በቃን።

የቀደሙትንና በየጊዜው ተመርጠው በአስተዳደር ቦርድ አባልነት አገልግሎት ሁሉ  ባላቸው እውቀትን ጊዜ ከፍተኛ መስውዕት ከፍለው እስካሁን ደብሩን ለዚህ በማድረሳቸው ምን ጊዜም  በደብሩም ሆነ በምዕመናንም ጭምር ትልቅ ክብርና ምስጋና ይገባቸዋል። በአንጻሩም ደብሩን እኛ ብቻ ብለው በመያዛቸው፣ የሚቀርብላቸውንም የምዕመናን ቅን ጥያቄ ብሎም ምዕመናንም ጭምር መናቅ ጀመሩ። እየተሰሩ ያሉትን ስህተቶች ማየት ተሳናቸው፣ አገልግሎታቸው ለበረከት መሆኑ ቀርቶ ለግል ስም መጠሪያ፡ እርስ በርስ  የስልጣን ጸብ፣ አለመግባባት፤ እርስ በርስ መወነጃጀል አልፈው ደብሩንም ለአለም ፍርድ ቤት አበቁት፤ አንዳንዶችም ከከሳሽ ጀርባ በስውር ቆሙ ፤ ከመከፋፈላቸውም የተነሳ  እንካን ምዕመናን ሊመሩ ምዕመናኑ እነሱን ሸምጋይ ሆነ ፤ ቢሰለቸው በምርጫ ለወጣቸው ፣ ይህንንም ውጤት ለመለወጥ እስከ አሁን ተስፋ አልቆረጡም፣ ድምጸ አናሳ ብቻ ሲቀሩና እንደ ድሮው ሳይሆንላቸው ሲቀር ራስቸውን ከቦርድ አባልነት አወጡ።

ሁላችንም እንደምናውቀው ለአገግሎት መመረጥ ለበረከት ነው። የቦርድ  ወይንም የቤተክርስትያን አባል ብቻ ያገልግል የሚል ሕግ በኦርቶዶክስ ቤተክርስትያን  የለም። ማንኛውም የዕምነቱ ተከታይ የሆነና ግብረ ገብ ያለው ሁሉ ትሕትና ብቻ ሳይሆን ለደረሰበትና ላጋጠመው ቤትክርስትያን እንግዳ መሆን የለበትም ፣ አቅሙና ጊዜው በፈቀደለት ሁሉ መስክ ማገልገል ይገባዋል።

ቀደም ብለው የተመረጡት አዲስ ቦርድ አባላት ያሉትን ችግሮች በአንክሮ ተመልክተው እንዲስተካከል ለመንቀሳቀስ ባደረጉት ጥረት መጀመሪያ በቦርዱ ውስጥ ብሎም በምዕመናን መካከል  ጥላቻ እንዲነሳ ዘመቻ ተከፈተባቸው፣ በመቀጠልም በመጨረሻ የተመረጡትም ከዚህ በፊት በቦርድነት ያላገለገሉ በመሆናቸው ገና ስማቸው ይፋ ሳይሆን የተለያየ ስም ወጣላቸው ፣ ገና ለገና የሰራነው ስህተት ይወጣብናል፣ ሳይቀድሙን እንቅደም ሩጫ ከፈቱባቸው። አንዳንዶችም አውቀውም ሆነ ሳያውቁ ፣ ፈጣሪን የማመን ይሁን የክህደት በሁሉም አቅጣጫ በፍርድ ቤትም ጭምር የተለያዩ ጸረ ኦርቶዶክስና ጸረ ቤትክርስትያን ቡድኖች የከፈቱትን ዘመቻ ለመግታት ብሎም ለመጣል ክእግዚሐብሔር ጋር የተስለፉት ያላሰለሰ ጥረት በጾም በጸሎት ምልጃ ላይ ናቸው። ምልጃቸውንም እየተቀበለ ያለ ፈጣሪም የተሳሳቱት ቁጥራቸው በየቀኑ እያነሰ ፣ ወደ ቤትክርስትያን ልጅነታቸውም እየተመለሱ ይገኛል።

በመጨረሻም በሜይ 2 ቀደም ሲል እንዲያስተምሩ ተጋብዘው በመጨረሻው አልችልም ያሉት የሁስተኑ ቄስ መኮንን ፣ ከዚያም ያንኑ ክፍተት እንዲሸፍኑ ተጠይቀው ሲያበቁ ከጥቂት ሰዐታት በፊት ያስያወቁት የአርቪንግ ማርያም መምህር ሰይፉ በቅዱስ ሚካኤል በአለ ንግስ ከተገኙት ካሕናት መካከል ይግኙበታል።  በእለቱም አጭር ትምህርት የስጡት የሁስተኑ ሲሆኑ በ ሜይ 2ቱ ሁከት የተሰማቸውን ሀዘን በጠቃሚ ትምህርት ቢገልጹም ለምን በእለቱ እንዳልተገኙ ማናቸውም አልገለጹምና በምዕመኑ አሉታን ፈጥሮ አልፋል።


እርሶስ ምን ይላሉ?

Wednesday, June 16, 2010

አሁንስ ጉዱ በዛ !

የርሶ ብዕር አስተያየት ተሳትፎ ሕብረተሰባችንን ይጠቅማል ያሉትን አይንፈጉን ገንቢነቱ ቦታ ይኖረዋልና!ማሳሰቢያ፡ ይህ ገጽ የተዘጋጀው የተለያዩ የኅብረተሰባችንን ሀሳብ ለመለዋወጫ እንጂ ለሚሰጡት ማንኛውም አስታየቶች በማንኛውም መንገድ ተጠያቂ አይደለም። ጉግል ድርጅትም ኃላፊነት አይወስድም። ኃላፊነቱ በሙሉ የአስታየት ሰጪው ብቻ ነው።



አሁንስ ጉዱ በዛ !


ሁላችንም ከዳላስ የኢትዮጵያን ኮሚኒቲ እርቀን ለረዥም ጊዜ ተቀምጠን የነበረው ያለ ምክንያት አይደለም። ሁለት አመት ያስቆጠረው እድር ግን አዳዲስ ፊቶችንና ሀሳቦችን ይዞ ትንሽ ሊያሰባስበን ቢነሳም፣ በውስጡ ያግበሰበሳቸው ጥቂት አባላት አሁንም ለማንበርከክ በተለያይ መንገድ እየተዋቀሩ ይገኛሉ። ባገኙት ቦታ ሁሉ በተለያየ መንገድ ሕብረታችንን ይተናኮላሉ፣ ትንሽ ነገር ይዘው መሀል ከገቡ የዘሩት መርዝ ቶሎ አይወጣም። እነዚህም ግለሰቦች በአንድ የፖለትካ ፣ በአንድ ቤተክርስትያን፣ በአንድ ጽዋ፣ በአንድ እድር፣ በአንድ ማህበር ወዘተ….ብቻ አባልነት የማይወሰኑ፤ አንዱ ጋር ሆነው ያንኑ ከማጠናክሩ፤ በምትኩ የአንድነትና የጥንካሬ ቦርባሪ የህብረተሰባችን ጠንቆች ናቸው።

ለዚህ መነሻ የሆነን፡- የዳላስ ፎርት ዋርዝ ኢትዮጵያን ኮሚኒቲ ለአባላት ባሰራጨው የኢትዮጵያን ቀን ዝግጅት አስመልክቶ በጠራው ስብሰባ የሚካሄድበትን ስፍራ በተመለከተነው። የስብሰብ ቦታ በሀይሉ እጅጉ መሰጠቱ ባልከፋ ነበር ነገር ግን የሱ በጎ የመሰለ ነገር በማር የተጠቀለለ መርዝ ስለሆነ በምስጋና ቦታውን መለወጥ ይገባል። ከግላችንም ቢሆን የስብሰባውን ወጪ ከፍለን ሌላ ቦታ እንዲሆን አምዳችን እያሳሰበ ፣ ኮሚኒትው መሪዎች ባላቸው ግንኙነት ሲሉ እንቢኝ ካሉ ማናችሁም እንዳትገኙ ከወዲሁ ጥሪ ለሚመለከታቸው ሁሉ እናቀርባለን።

አምዳችንም ለዚህ አቀም የበቃው፣ ሀይሉ እጅጉ የጳውሎስ ሎሌ ብቻ ሳይሆን የዳላስ ኢትዮጵያ ተዋህዶ ደብረ ምህረት ቅዱስ ሚካኤል ካቴድራል የሆነውን ደብር፣ የማንኛቸውንም ኢትዮጵያዊና የኢትዮጵያ ተወላጅ ሁሉ በዘር፣ በሀይማኖትም ሆነ በጎሳ ሳይለያይ፤ እንደ ግል ሀብቱ፣ መታወቂያው፣ ኩራቱና ክብሩ የሆነውን ታላቅና ክብር ቦታ ነጥቆ ለመስጠት ሌት ተቀን የሚተጋና በኮሚኒታችን ውስጥም ቀዩ ሰይጣን የሚል ቅጽል ስም የተሰጠው ግለሰብ ዳንስ ቤት ነው። ይኸው ቦታም ወደፊት ኮሚኒታችንን ሊያስተች የሚያስችል ሊሆን ይችላልና ከአሁኑ ይታሰብበት እንላለን። የበለጠ ስለ ሀይሉ እጅጉ ለማወቅ ቀደም ሲል በአምዳችን ያወጣነውንና እንዲሁም በሰንበቴ ገጽ የወጡትን ኣንዲያነቡ እንጋብዞታለን።

እርስዎስ ምን ይላሉ?

Tuesday, June 15, 2010

እኝህ አንባብያችንን

የርሶ ብዕር አስተያየት ተሳትፎ ሕብረተሰባችንን ይጠቅማል ያሉትን አይንፈጉን ገንቢነቱ ቦታ ይኖረዋልና!ማሳሰቢያ፡ ይህ ገጽ የተዘጋጀው የተለያዩ የኅብረተሰባችንን ሀሳብ ለመለዋወጫ እንጂ ለሚሰጡት ማንኛውም አስታየቶች በማንኛውም መንገድ ተጠያቂ አይደለም። ጉግል ድርጅትም ኃላፊነት አይወስድም። ኃላፊነቱ በሙሉ የአስታየት ሰጪው ብቻ ነው።


Bekalu to me
show details 9:30 PM (56 minutes ago)
Bekalu has left a new comment on your post "ጋሼ ተኮላ":

I am so glad that we have this site to express our views and concerns about the Dallas D.M.St. Michael Orthodox Church. I am sure many of us ,who have followed the Mehabere kidusan and those of the bugs' hidden agenda have come to our mind. There are still a lot of people remained confused. There are also many people who are working with the ASMESAYOCH with out knowing their intended goals.We should call on those friends and use every means available to tell them the truth about these enemies of our church. Please. Please, let's come together and defend our church from these Asafari Yeken Jiboch and Bandas.let them play their dirty political game somewhere outside, not in our church.By the way , I would suggest our Board to take some time after Kidase and brief the people about the current situation, "the reason why they are fighting and what step they are taking to protect the church. At least give them a hint what the interests of those stupids.
That is how we create solidarity and defend our church.It is when we get a full picture and understanding of their intention that we can clear our church from insurgents.
Egziabeher Hailina Birtatun Yisten. Amen.

እኝህ አንባብያችንን የመሰሉ ብዙ ምላሾችን እናገኛለን። ሁላችሁንም ስለተሳትፎዎቻችሁ ከልብ እናመሰግናለን። የተለየ ሀሳብ ወይንም ይህ አምዳችን የተቸባችሁ ፣ የተቆረቆራችሁ ፣ ከየትንኛው ጎራ ያላችህን ጭምር፣ ከሳሽ ተከሳሽ፣ ወንጃይ ተወንጃይ ሁሉ፤ ምንም እንካን ከተለያየ ቀዬ ብንመጣም ሁላችንም ከኢትዮጵያ ነንና በዚህ መድረክ ስነ ስረት በያዘ መንገድ መወያየትንና መተቻቸት እንችላለንና ሞክሩን አናሳፍሮትምና።

እናስተዋውቃችሁ፡-

የርሶ ብዕር አስተያየት ተሳትፎ ሕብረተሰባችንን ይጠቅማል ያሉትን አይንፈጉን ገንቢነቱ ቦታ ይኖረዋልና!ማሳሰቢያ፡ ይህ ገጽ የተዘጋጀው የተለያዩ የኅብረተሰባችንን ሀሳብ ለመለዋወጫ እንጂ ለሚሰጡት ማንኛውም አስታየቶች በማንኛውም መንገድ ተጠያቂ አይደለም። ጉግል ድርጅትም ኃላፊነት አይወስድም። ኃላፊነቱ በሙሉ የአስታየት ሰጪው ብቻ ነው።



እናስተዋውቃችሁ፡-

ዛሬ የምናስተዋውቃችህ እነዚህ ሁለት ግለሰቦች ስማቸው፡-
1ኛ/ ዶ. ሰለሞን አበበ
2ኛ/ ኪዳኔ አለማየሁ በቀንደኝነት የሚጠቀሱ ናቸው።

ሰሎሞን አበበ ማለት ቀደም ብሎ በንጉሡ ስርዐት ለማባበያነት እድል ከተሰጣቸው ወገኖች ውስጥ ለትምህርት በኢትዮጵያ ሕዝብ ሀብት ወደውጭ ሀገር ተልኮ ከተመለሰም በኃላ ይህን ለሀገሬ አድርጌ ብሎ ያስመዘገበው የሌለው የከተማ አውደልዳይ፣ ሀገራችን የተማረ ያለህ ብላ በምትማጸንበት ወቅት ክዶ ለተባበሩት መንግስታት በመቀጠርና ጡረታ እስኪወጣ ድረስ፣ ከዚያም የልጆቹን እናት ክዶ ወደ አሜሪካን በመምጣት ከሀገሩንና ከወገኑን ይልቅ የራሱን የግል ጥቅም የሚያስቀድም፣ ከሁሉም በላይ የተባበሩት መንግሥታትና የኢትዮጵያ መንግስት ጡረተኛ ፣ የራሱ ቤት በጋርላንድ ከተማ ያለው፣ የተለያይ ጥቅማጥቅሞችን ከአሜሪካ መንግስት የሚወስድ፣ በወር 30 ዶላር መክፈል ማለት በቀን አንድ ዶላር ለቤተክርስትያን የአባልነት ክፍያ ላለመክፈል ያመለከተ በጣሙን እርካሽ የሆነ ግለሰብ ነው።

ይኸው ግለሰብ ወደ ዳላስ ከመጣ ጊዜ ጀምሮ በአጭር ጊዜ ውስጥ ከሕብረተሰባችን ጋር ተመሳስሎ ከመኖሩም በላይ የቀድሞ የሚካኤል አስተዳደር ቦርድና በፈቃዱ ከምዕመናንና ከፈጣሪ የተሰጠውን አገልግሎት ጥሎ የኮበለለው የኢዮኤል ነጋ ቀኝ እጅ የነበረና አሁንም የሆነ ግለሰብ ነው። ሰሎሞን አበበ ወያኔ ያሰረው የበደለው አርጎ ሲኮንን በሌላ በኩል ወደ ኢትዮጵያ ያለ ችግር ይመላለሳል እንደውም የነሱ ነውም ይባላል። እኛም እስከምናውቀው ድረስ ኢዮኤል ሊቀመንበር በነበረበት ወቅት የሱ ምስጥረኛ ብቻ ሳይሆን የደብሩም እቡዕ ዋና ጸሐፊ በመሆን አብዛኛውን የኢዮኤል ፊርማ ያለበትን ሰነዶች የተላላከና በግሉም የወሰደውን ውሳኔም በሊቀመንበሩም ሆነ በቢጤዎቻቸው ጥያቄ ያላጋጠመው፣ ኣስካሁን ሰአት ድረስ ኮምፒተር መሀይሙ ኢዮኤል ኢሜል ተቀባይና መላሽ ፣ አማካሪውና ልዩ ሚስጥርኛ ብቻ ሳይሆን ኢዮኤልን ከጀርባ ሆነው ከሚያሽከረክሩት ከነ ጌታቸው ትርፌ የበለጠ ቦታ ያለው ነው። ከርሱም ጋር ከገጠመ በኃላ ኢዮኤል ራሱን ከሌላ ፕላኔት የመጣ ወይም ራሱን እንደ አምላክ ማየት የከጀለው።

ሰሎሞን አሁንም በቤተክርስትያኑ በሚሰጡት የምሽት ትምህርቶች ላይ በመምጣት ስለላን ማካኼድ፣ ከየቦታው የሚሰበስባቸውን መጻሕፍቶችን እንድ ሱቅ በደረቴ በውድ መሸጥ ብቻ ሳይሆን፣ የሚጋበዙትንም አስተማሪዎችን በጎ ስራቸውን ለማደናቀፍ ስውር ደባ ፈጻሚ ነው። ከጥቂቱ በትንሹ ኢትዮጵያ ውስጥ የሚያውቃቸውንም ሆነ እነርሱን በመጠቀም በመተዋወቅ ከደብራችን ጋር ጤናማ ግንኙነት እንዳይኖራቸው መጥፎ መርዝ በመርጨት ከነኢዮኤል ጋር እየሰራ ያለ ፣አዛውንት መባል የማይገባው አስነዋሪ ስራው ቢቆጠብ፣ የሚቀበለው የስጋወደሞ ባያስቆጣ እንላለን። በተጨማሪም የኢትዮጵያ ትውውቁን ምክንያት በማድረግ አዲስ የተቀጠሩትን መነኩሴ ከጥቂት ሳምንት በፊት ታጋብዘው በመጡበት ወቅት ወደኢዮኤል ቤት ድረስ ወስዶ ያስተዋወቀና በትላንትናው እለትም ወደዚሁ መነኩሴ አባርትመንት ድረስ በመውሰድ ያገናኘ ነው። እኛ በግላቸው ላላቸው ጉዳይ ባያገባንም ቂመኛው ኢዮኤልና የሰሎሞን መርዝ ለደብራችን እንዳይተርፍ ለማሳሰብ ነው።

ባለፈው እሁድ ገጻችን እንዳስነበብነው ‘ የበግ ለምድ የለበሱ……….’ ያልናቸው እነዚህንና ቢጤዎቻቸውን ነው። ሎላው ደግሞ ኪዳኔ አለማየሁ የተባለው እንደ ሰሎሞን አበበ ተመሳሳይነት ያለውና ያስተማረውን ወገን ከድቶ እንደቢጤው ለተባበሩት መንግሥታት ከዚያም ለዐረብ አገር የሰራ፣ ጡረተኛ ነኝ ብሎ ወደ ዳላስ ከመጣ ጀምሮ ሳይሳካለት ቀረ እንጂ ያልሞከረው የለም። ሀይማኖተኛም ነኝ ብሎም ከቀድሞ የትምህርት ቤት ጋደኞቹ ጋር በመሆን በኢዮኤል አጋፋሪነት የተወጋገዙትን ጳጳሶችን እናስታርቅ ብሎ ለጳውሎስ ሎሌ የሆነ፣ በቤተክርስትያናችንም ውስጥ ለነበሩት ችግሮች ሁሉ በእጅ አዙር የሚመርዝ ብቻ ሳይሆን ምዝበራ ውስጥም እጁን የዶለ ግለሰብ ነው። ገናም መቀጠራቸው ይፋ ሳይሆን አዲሱን መነኩሴ ያሉበት ከተማ ድረስ እጅጉን ስራዬ ብሎ በሰው አፈላልጎ ለመተዋወቅ ያልፈነቀለው ድንጋይ አልነበረም።
የመጡ ዕለትም ቤተክርስትያን ድረስ በመሄድ የተዋውቀ የመጥፎ ምግባር ማደሪያ የሆነ ግለስብ ነው። ስለ እርሱም ሆነ ስለሌሎቹ ጸረ-ኦርቶዶክስ በሰፊው ከነ መረጃው ሰንበቴ በተባለው ገጽ በተለያየ ጊዜ በሰፊው የውጣ ስለሆነ ያንን ገጽ እንድትመለከቱ እንጋብዛለን።

ከሁሉም በላይ እኛን የሚገርመን ቢኖር ‘ አንድ ህይማኖትና አንድ ዕምነት ‘ ያለው ምዕመን ለምን ጥላችና ጠብ ውስጥ እርስ በራሱ ይገባል? የጥበብ ሁሉ መጀመሪያ ምንድን ነው? እስቲ ሁላችንም ወደ መልካም መስመር ፣ ወደ ፈሪሀ እግዚሐብሒር እንመለስና እኛም ጣታችንን በመጥፎው ልይ ከመጠንቆል ፣ እከሌ እንዲህ መልካም አደረጉ ብለን ለመዘገብ እንዲያበቃን መልካም ፈቃዱ እንዲሆንለን እንጸልይ፣ ከልባችን ካደረግነው የሱ ማደሪያ እንሆናለንና።

እርሶስ ምን ይላሉ?

Monday, June 14, 2010

ለቀድሞ የአስተዳደር ቦርድ አባል

የርሶ ብዕር አስተያየት ተሳትፎ ሕብረተሰባችንን ይጠቅማል ያሉትን አይንፈጉን ገንቢነቱ ቦታ ይኖረዋልና!ማሳሰቢያ፡ ይህ ገጽ የተዘጋጀው የተለያዩ የኅብረተሰባችንን ሀሳብ ለመለዋወጫ እንጂ ለሚሰጡት ማንኛውም አስታየቶች በማንኛውም መንገድ ተጠያቂ አይደለም። ጉግል ድርጅትም ኃላፊነት አይወስድም። ኃላፊነቱ በሙሉ የአስታየት ሰጪው ብቻ ነ

ይድረስ ለአቶ ኃይሉ አራጋው፡ -

ይህ አምዳችን በ06/13/2010 ባወጣው ላይ አንተን የሚመለከት አስተያየት ተሰንዝሮብሀልና መልካም ፈቃድህ ሆኖ መልስህን ለሚመለከታቸው ወይንም ለዚህ አምድ ትገልጽን ዘንድ በእግዚሐብሔር ስም በትህትና እንጠይቃልን?

እንኻን ለበረከት ተብሎ ግልጋሎት ለሚሰጥበት ሀይማኖታዊ ቦታ፣ በአለም ውስጥም ማንም በአገልግሎቱ ምክንያት በእጁ ያሉትን ለተተኪው ወይንም ለሚመለከትው አካል የማስረከብ ኃላፊነት ብቻ ሳይሆን በሕግም ግዴታ ጭምር እንዳለበት ለአንተ ማስረዳት ተገቢ አይመስለንምና ፤ ስምህ በዚህ ምክንያት ተነስቶ መጠቀስ ተገቢ አይደለም ። በተለያየ ምክንያት ሳይመችህ ቀርቶ ስለሚሆን ስለ ቅዱስ ሚካኤል ብልህ ባስቸክይ እልባት እንድታደርግለት በትህትና እንጠይቅሀለን። ባንተ ምክንያት ሰበብ እንዲሆን መልካም አይሆንም ። ቀድሞ የሰጠኸውን አገልግሎት እንዲቆጥርልህ አሁንም የቦርድ አባል ብቻ መሆን የለብህም በምትችለው ሁሉ የእግዚሐብሔርን ቤት ማገልገል የሁላችንም ግዴታ መሆኑን እያስገነዘብን፣ አንተም ያካበትከውን እውቀት በስራ በማዋል በአርያነት ማሳየት ይጠበቅብሀል። እልህ፣ ቂምና በቀል፣ ስምና ዝና ወይንም ንቀት ለማንኛውም ወገን በጌታ ቤት ቦታ የለውምና።

እርሶስ ምን ይላሉ?

ውድ አንባቢዎቻችን ሆይ!

የርሶ ብዕር አስተያየት ተሳትፎ ሕብረተሰባችንን ይጠቅማል ያሉትን አይንፈጉን ገንቢነቱ ቦታ ይኖረዋልና!ማሳሰቢያ፡ ይህ ገጽ የተዘጋጀው የተለያዩ የኅብረተሰባችንን ሀሳብ ለመለዋወጫ እንጂ ለሚሰጡት ማንኛውም አስታየቶች በማንኛውም መንገድ ተጠያቂ አይደለም። ጉግል ድርጅትም ኃላፊነት አይወስድም። ኃላፊነቱ በሙሉ የአስታየት ሰጪው ብቻ ነው።


ውድ አንባቢዎቻችን ሆይ!

እንደምን አላችሁልን? ያለናንት ተሳትፎ አይሆንምና ለምትሰጡት አስተያየት ሁሉ ከልብ እናመሰግናለን። ሕብረተሰባችንም ጥሩ ግንዛቤ እያገኘ በመምጣቱ የዕምነትና የጎሳ ልዩነቱን ጥሎ ለአንድዬና ለብርቅዬ መመኪያውና ለስሙ መጠሪያው፣ የራሱ የግሉ ክብሩና መመኪያ ኩራቱ አድርጎ በመቀበል፤ ጥቂት ጊዜ አስቆጥሮና በቅርብ ጊዜ የፈነዳውን በዳላስ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ደብረ ምህረት ቅዱስ ሚካኤል ካቴድራል ውስጥ በጥቂት ግለሰቦችና ራሱን ማኅበረ-ቅዱሳን ብሎ የሚጠራው ከልት ወግነው የፈፀሙትን ጥፋት በምሬት በመግለጽ በማንኛውም መንገድ ከጎን በመሰለፍ እንደሚዋጋቸው እየገለጸ ይገኛል።

ጋሼ ተኮላም (Looser) ማምሻውን በገጹ ያወጣው፣ ከዚህ በፊት ቢተክርስትያኑ ተርጉሞ ያወጣውን በወቅቱ ሀሰት ብሎ የተቸውን ነው። ምንም አዲስ ወሬ አይደለም። ምንግዜም ጠበቆች ውሳኔውን ሲመቻቸው ጽፈው የወሰነውን ዳኛ በማስፈረም በሰነድነት ይያዛል፣ ይሄ ደግሞ ለአንተ ብጤ ትምህርት ‘ሀ‘ ብለን እንዘለዋለን። ሌላው ደግሞ ከሚቀጥለው ምዕራፍ ቀጥሎ የምናስጨብጠው የሕግ ነጥብ ለጋሼ ተኮላ(Looser) አይገባውምና እንደፈረደባት ሚስቱ ወይም ልጁ መጽደቂያ ቢሆናችሁ የተጣባው እስኪወጣለት ድረስ ጋቱት እናንተ ብቻ ናችሁ የቀራችሁት፣ ወይንም እናንተም እንደ ኪዳኔ ምስክርና ሚስቱ መዋቀር ጀመራችሁ። የጥልን ካነሳን ካድሬው ሲደልል ቅስናውን አፍርሶ ከአገልግሎት የኮበለለው መስፍን ጋር ጦርነቱ ከፍቶ ይግኛል አሉን። ዋ ገና ሚካኤል………

የኛም ገጽ እያደረገች ያለውንም አስተዋጽዎ ቀላል አለመሆናን ከሕብረተሰባችን ውይይቶችና ከሚደርሱን መልዕክቶች ተገንዝበናል። የኛ መድረክ ለሁሉም ክፍት ነው። በተለይም በሌላ ጎራ ወይንም አስተሳሰብ ያሉትን ይህ መድረክ መጋበዙን አላቃረጠም። እኛም እነዚህ አውቀውም ሆነ በስህተት ጸረ-ኦርቶዶክስ ጎራ በከተማችን የከፈቱትን በየደረስንበት ሁሉ በመምከር ወደ እውነተኛው መንገድ እንዲመለሱ፣ ቀንዳሞቻቸውንም ከማጋለጥ ወደ ኃላ አንልም። ለዛሬ ደግሞ ተግባራቸውና የሀገሪቱን ሕግ ለማመሳሰልና አንባቢዎቻችንን ለማስጨበት እንደሚቀጥለው እንተነትናለን በረጋ መንፈስ እንዲያነቡት እንጋብዞታለን ፡-


Stalking is a term used to describe a set of behaviors that has been exhibited by individuals for thousands of years. While all states have had laws about assault and harassment for some time, the first law prohibiting stalking was not enacted until 1990. California was the first state to make acts of stalking illegal. This law was passed in response to some high profile stalking cases that eventually resulted in the victim's murder. Today, every state has a stalking law which prohibits individuals from engaging in a course of conduct directed at a specific person that causes them to reasonably feel fear or duress.

The specific definition of stalking can vary from state to state. Many states define stalking specifically as: the willful, malicious, or repeated following or harassing of another individual, causing them fear for their safety or wellbeing, or that of their immediate family. The crime of stalking can be considered a misdemeanor or a felony offense depending on the state laws and specifics of the case.

ከዚህ በላይ ያቀረብነው ጽሁፍ የማኅበረ-ቅዱሳንና ሌሎች ፀረ ቤትክርስትያን ወገኖች የከፈቱት የድህረ-ገጽ ዘመቻ የተነጣጠረው በቤተክርስትያና እና በተመረጡ የአስተዳደር አባላት ላይ በግልጽ የጀመረው ካለፈው አመት ጀምሮ ነበር። የሚቀጥሉትም ሁለት ክፍሎችም ይህንኑ ያሳያሉ።

Slander is defined as the act of making false and injurious statements that do injury to a person's reputation. Both slander and libel are forms of defamation. Slander is defamation that is spoken, while libel is defamation that is written. Slander can include any false statement which does injury to a person's business or personal reputation and can relate to the person's character, morals, ability, business practices, or financial status. The victim of slander has the legal right file a civil lawsuit against the person who committed the slander to seek compensation for their damages.

Inchoate Crime, Attempt is the inchoate crime closest to actually carrying out the crime itself, while solicitation is the furthest removed. Attempt using involves trying to commit a crime but failing to complete the intended actions. Threats and challenges may also qualify as attempt.

Conspiracy involves agreeing to commit a crime. This crime can be charged in addition to the crime itself. For example, you can be charged with murder and conspiracy to commit murder. Conspiracy is a favorite prosecutorial weapon because it is relatively easy to obtain a conviction for conspiracy. It is important to have a strong defense in order to fight allegations of conspiracy.

ይህ አስመልክቶ ያለውን የሕግ ሐረግ ለማስጨበት የቀረበ ነው።

Solicitation is the crime of asking another party to commit a crime. Even if the solicited party does not commit the crime, the asking party may be charged with solicitation. For example, a person who offers a bribe to a public official may be charged with solicitation even if the official did not accept the bribe.

Being an accessory or accomplice to a crime is similar to inchoate crimes because they do not involve the actual commission of the crime. Both accessory and accomplice involve knowingly and intentionally helping to facilitate the success of a crime. The person who actually commits a crime is called the principle. Those who help are called accomplices. For example the person with the gun to a teller's head collecting cash in a bank robbery is the principle; the getaway car driver, lookout person, and other helpers are the accomplices. An accessory may help a principle or accomplices before or after a crime. For example, the person who knowingly shelters criminal offenders after the crime, to help them escape arrest, is an accessory after the fact.

ይህ ደግሞ በቀደምት አስተዳደር ተመራጮችና በማኅበረ-ቅዱሳን በተባለው ከልት አማካኝነት ተመዝብሮ ያልተዘጋ ሂሳብ ፣ የቤተክርስትያኑን ሀብት በተመለከተ የሕግን ሀሳብ የሚያሳይ ነው።

Embezzlement, The wrongful use of the property of another person for one's own benefit may be considered embezzlement if the property in question has been legally entrusted by the owner to the person who is misusing it. Although most charges of embezzlement are levied against persons who are employees of a company or individual, acts of Congress classify as embezzlement the stealing of letters and other mail by postmasters, clerks, and letter carriers. Embezzlement is a serious charge; in most states it is considered a felony offense. The potential punishments for an embezzlement conviction include prison time and significant fines.

There are many different types of embezzlement, but around 80% of cases involve the misappropriation of assets, including inventory and supplies. Most commonly, persons accused of embezzlement are being investigated in relation to missing cash, either on hand or from business bank accounts. Embezzlement charges may be levied against almost anyone who has access to these accounts or cash on hand (such as petty cash), and a charge of embezzlement can be almost as damaging as a conviction.

As previously mentioned, there can be strict consequences for a person convicted of embezzlement. These may include any combination of imprisonment, probation or parole, loss of the right to be bonded, restitution to be paid to the victims of embezzlement, court-ordered counseling, and large fines. Sentencing for embezzlement may take into account any prior convictions, attitude of the community towards crimes such as embezzlement, degree of media attention on the case, and mitigating circumstances.

ከዚህ በኃላ ያለው ደግሞ በተዘዋዋሪ መንገድ ከላይ የተጠቀሱትን የሕግ መተላለፍ በገንዘብ፣ በቁሳቁስ፣ በእውቀት፣ በሞራል የተሳተፉ፣ ያሳተፉ፣ የተባበሩ፣ ያስተባበሩ ወዘተ… ይመለከታል።

An accomplice is an individual who participates in the commission of a crime knowingly, willingly, and with common interest. An accomplice is one who intentionally aids in the commission of a crime whether or not they physically commit the act itself. An accomplice can be charged with the same crime as the principle actor who carries out the offense. In the eyes of the law, helping someone in the commission of a crime makes one just as guilty as the criminal themselves.

ከዚህ ቀጠሎ ያለው ደግሞ የሕግ ጥፋት ወይንም መተላለፍ የቅጣት አይነትን ነው።

A misdemeanor is a criminal charge that is less serious than a gross misdemeanor or a felony. A misdemeanor is typically a crime that is punishable by less than one year of incarceration and a certain maximum fine. Some crimes can be considered a misdemeanor or a felony depending on the specific facts of a case. In some criminal cases, a person charged with a felony offense will be charged with additional misdemeanor charges as part of the prosecution's statutory scheme. A criminal defense may also succeed in reducing charges from a felony to a misdemeanor offense, which can be very advantageous to a defendant.

Some examples of misdemeanor offenses include certain traffic violations, property theft at a value lower than a specific amount, trespassing, disorderly conduct, possession of a controlled substance, and more. Each state has passed specific laws which apply to the classification of criminal offenses. Many states also have a system which classifies misdemeanor offenses based on severity.

A felony crime is more serious and is punishable by more than one year of prison or even death. The criminal process for felony offense cases differs from the process employed for misdemeanor crimes. In a misdemeanor case, the prosecution will not often convene a grand jury to indict the defendant. In many jurisdictions, individuals who face misdemeanor charges are not granted the right to a court appointed lawyer as they are in felony cases. Though the potential punishment is less serious than for a felony, a misdemeanor is a criminal offense and one charged with this offense will greatly benefit from professional legal help to protect their legal rights and options.

A person who is charged with a misdemeanor will face a criminal trial by judge or jury to determine their guilt or innocence. In many jurisdictions, misdemeanor cases are handled in special courts that use abbreviated procedures. A defendant will often have to request and pay for a jury trial, if they seek this legal option in a misdemeanor case. If convicted, a judge will usually have broad discretion in determining the sentence, or penalty, imposed. In cases of misdemeanor traffic violations, the court will typically have a pre-determined fee schedule that will determine the penalty for their crime.

penalties. The additional penalties for a misdemeanor will often depend on the type of offense that was committed. For some misdemeanor convictions, a person's driving privileges may be revoked for months and even years. Some people convicted of a misdemeanor may lose the right to possess a firearm, or may have a concealed weapon permit permanently revoked. A misdemeanor conviction may also be grounds for employment termination and may preclude a person from obtaining a professional license and similar credentials and opportunities.

ይህ ደግሞ እነዚህ ቡድኖች የህግ ጥፋታቸው ደረጃ የሀይማኖት ጥላቻ መሆኑ በሕግ ከተረጋገጠና በተለይም ራሱን ከልት ያደረገው ቡድን አባሎች ወገኖቻችን (በሜይ 18 የፍርድ ቤት ጉዳይ ቤተክርስትያኑ ባቀረበውና በማህደሩ እንደሚገጘው) ሊጎዳ የሚችል የሕግ ክፍል ነው። ከዚህና ከሌላው ሕግ ክፍል ጋር የሚያያዘው፣ በጥላቻ ላይ ተመርኩዞ አባሎችንና ምዕመናኑ ወደ ቤተክርስትያን እንዳይሄዱና ምጽዋት እንዳይሰጡ፤ የዚህም ውጤት ይህ የሀይማኖት ቤት እንዲዳከም ብሎም ከጉዳት አልፎ እንዲጠፋ ለማብቃት የሚሉትን ሊጨምር ይችላል።

A hate crime is any malicious act committed against a property, group or person because of a bias against a particular religion, sexual orientation, race, ethnicity, nationality, or disability. Hate crimes are often acts of force or threats of force upon a particular group because the offender disagrees or does not understand the group's affiliation.

While a number of different factors may motivate people to commit hate crimes, certain groups are more frequently the victims. Motivations for hate crime offenders are typically racial, ethnic, sexual orientation, or religious based. Following the enactment of the 1990 Hate Crime Statistics Act by the federal government,

የኛ ዐምድ ፍላጎትና አላማ በሕብረተሰባችን ውስጥ የሀይማኖት ተቁዋማትን ጨምሮ በሰላም አብሮ ለተሻለ እድገት መቀጠል የሚቻልበትን መድረክ እንጂ ሁኔታዎች ወደ መጥፎ አቅጣጫ እንዲጛዙ አይደለም። በስህተት መስመር የቀራችሁና ወደ ሕግ የተጛዛችሁ ሁሉ፣ የሌለ መብት ምክንያት የምታደርጉ፤ የእውቀት ሁሉ መጀመሪያ እግዚሐብሔርን መፍራት ነውና እሱን በልባችሁ ያዙ። እንደዚህ ከሆነ ይቅር ለእግዚሐብሔር ብላችሁ ነገርን ተውት። እናንተም ሚካኤል ብቻ አይደለምና የማምለኪያ ቤትክርስትያን እልህ አትያያዙ፡ካሳችሁን እርሱን አድርጉ። ደብሩም ከነምዕመናኑ ይቅር መባባልን ይገባዋልና። ጉዳቱ የሁሉም ነው። ሁሉንም እንደስራው የሚከፍል እሱ ነውና።

እርሶስ ምን ይላሉ?

Sunday, June 13, 2010

የመረዋው ጋሼ ተኮላ Looser

የርሶ ብዕር አስተያየት ተሳትፎ ሕብረተሰባችንን ይጠቅማል ያሉትን አይንፈጉን ገንቢነቱ ቦታ ይኖረዋልና!ማሳሰቢያ፡ ይህ ገጽ የተዘጋጀው የተለያዩ የኅብረተሰባችንን ሀሳብ ለመለዋወጫ እንጂ ለሚሰጡት ማንኛውም አስታየቶች በማንኛውም መንገድ ተጠያቂ አይደለም። ጉግል ድርጅትም ኃላፊነት አይወስድም። ኃላፊነቱ በሙሉ የአስታየት ሰጪው ብቻ ነው።


ጋሼ ተኮላ (ሉዘር) የመረዋው ኸረ ለመሆኑ እንደምን ተርፈህ ከርመህ ነው አሁንም ያለስራህ ገብተህ የምትፈተፍትው? አንዴ ከምግባር ቢጤህ ጋር ሁነህ የሰው ቤተክርስትያን የከሰስክ፣ የምትደሰኩርልት መብት የሚመጣው ከግዴታ ጋር መሆኑ ያልገባህ ደንቆሮ በምን ቀንቀ ብናስረድህ ይገባህ ይሆን? ጉዳይ ሳይኖርህ ከሳሽ፣ አባል ሳትሆን መብት ጠያቂ፣ ኸረ ለመሆኑ አንተ ከየትኛው ፕላኔት ነህ ወይስ የምትጠጣው ቢራ አስክሮህ ነው እንዲህ የሚያደርግህ፣ በውትድርናህ ጊዜህ የሸተተህ ባሩድ ወይስ ያደክበት ቀዬ የለከፈህ ሰይጣን አሁንም ይጫወትብሀል?

አዎን በእውነት እንላለን አንድ ሰው ለአንድ ድርጅት አባል ሲሆን፤ ጠንቅቆ መብቱንና ግዴታውን አምኖ ይሆናል። ማንኛውንም እንቅስቃሴ በሕጉና በደንቡ ነው። አንተና መሰሎችህ ቤተክርስትያና ከሀይማኖት አገልግሎት ውጭም ያላትን ምግብም ሆነ መጠጥ ያለክፍያ አስተናገደቻችሁ፡ የአንተና የምግባርህ ተካፋዮች ግን የተመገባችሁበትን ወጪት ሰባሪዎች ናችው። አልፋችሁ ተርፋችሁ በስብሰባችሁም ኣኔ ሚካኤል የሚሄደው ለትዝብት እንጂ ለፀሎትማ ሌላ ቦታ ነው የሚሄደው፣ አንተም ራስህ ምዕመናን ወደ ሚካኤል እንድይሄዱ ገንዘብም እንዳይመፀውቱ የቅስቀሳ ዘመቻ እንዳደረክ እና እንደምትቅጥልበት ኃይሉ እጅጉና ሙላው ወራሽ የተባሉት ፀረ ኦርቶዶክሶች ባዘጋጁት ስብሰባ ላይ፣ በኩራት እንደ ጀግና የተናገርከውና ማኅብር-ቅዱሳኑ መስፍን ኢሕአፓው የቀዳውን ቪዲዮ እንዳለ አላወክምን? ሚካኤልን በተመለከተ መናገር የሚችል የሚካኤል አባል እንጂ እንደ አንተ አይነት የርኩስ መንፈስ ማደሪያ አልተፈቀደለትምና። ይህ መልክት ላንተና ለብጤዎችህ ለነ ሰላም ተዋህዶ ጭምር ነው።

አንዳንድ ቃል የተገባላቸው ለሥልጣንም ሆነ ለስም ስትሉ፣ ዘመድ፣ ወዳጅ ወይም ጋደኛ ላለማስቀየም ብላችሁ ለርኩስ መንፈስ መጠቀሚያ ፤ አውቃችሁም ሆነ ሳታውቁ፣ በስህተትም ሆነ በግድፈት በየዋህንት የቀራችሁ ጥቂት ግለሰቦች ንስህ በመግባት አሁኑን ወደ ፈጣሪያችሁ ተመለሱ። የመዳን ሰአቱ አሁን ነውና።

ዕምነታችሁ የተፈተነባችሁ፣ ከቤተክርስትያን ራሳችሁን ለማራቅ የአሰባችሁ፡ ቤቱን በአሽዋ ላይ እንደሰራው አትሁኑ፡ በአለት ላይ ወደ ቆመው ቤተክርስትያን ተመለሱ። አልፎ አልፎ የክርስትናው መንገድ ይጎረብጣልና ጽኑ እርሱ አብሮአችሁ ነውና።

በዛሬው ዕለት አዲስ የመጡትን አባት አባ ምህረትን ይህ ግጽ እንካን ደህና መጡ ይሎታል። እንደስሞም ምህረት እንዲሆኑን ፀሎታችን ነው። በትውውቁ እንደተገለጸው ያልዎት ደረጃና ያካበቱት ዕውቀት ለከተማችን ተመሳሳይ አቻ የሎትምና የበግ ለምድ የለበሱ አንዳንድ ተኩላዎች ቀደም ብለው ሊያጠምዱዎት እንደሞከሩና እዚህም ከደረሱም ሰአት ጀምሮ የተለያዩና የረቀቁ ዘዴዎችን እያቀናበሩ ይገኛሉ። ሌላው በዛሬው ትውውቅና ትምህርቶ፡ ሴት ወንድ ሳይል ካሕናቱን ጭምር ዕንባችንን መቆጣጠር እስኪሳነን ድረስ ልብ የሚነካ ነበር። እንግዲህ እርሶም እኛም ንጹህ ልቦና ይዘን ከቀረብን እግዚሐብሔር ከኛ ጋር ይሆናልና፣ በዛ ፈጽሞ ሀዘን አይኖርም።

እርሶስ ምን ይላሉ?

Saturday, June 12, 2010

ይድረስ ለመምር ሽታና ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስትያን፡-

የርሶ ብዕር አስተያየት ተሳትፎ ሕብረተሰባችንን ይጠቅማል ያሉትን አይንፈጉን ገንቢነቱ ቦታ ይኖረዋልና!ማሳሰቢያ፡ ይህ ገጽ የተዘጋጀው የተለያዩ የኅብረተሰባችንን ሀሳብ ለመለዋወጫ እንጂ ለሚሰጡት ማንኛውም አስታየቶች በማንኛውም መንገድ ተጠያቂ አይደለም። ጉግል ድርጅትም ኃላፊነት አይወስድም። ኃላፊነቱ በሙሉ የአስታየት ሰጪው ብቻ ነው።

ይድረስ ለመምር ሽታና ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስትያን፡-

በቅርብ ባናውቅህም ሆነ ያንተን ትምህርት ባንሰማም ቅዱስ ሚካኤል ከተተናኮሉት ውስጥ ፕሮግራም የተያዘለት አስተማሪ የመምጣት ሀሳቡን ሲያጨናግፉበት በተፈጠረው ክፍተት፣ አንተ አገልግሎት በመስጠትህ ጠላቶች ተነስተውብሀል። አንተ ማንም ይሁን ማን የኔ ተግባር እግዚሐብሔር በሰጠኝ ዕውቀትና ልሳን ክርስትናን ማስተማር ነው ብለህ በማገልገልህ፤ የውሸት ክርስትያኖች፣ፀረ-ኦርቶዶክስ ሀይማኖትና ቤተክርስትያኖች፣ ራሱን ማኅበረ-ቅዱሳን ብሎ የሚጠራው ከልትና ጥፍሮቻቸው በነገው ጁን 13, 2010 የቤተክርስትያን አገልግሎት ሁካታ ለመፍጠር እየተዘጋጁ መሆናቸውን ስለሰማን ለቤተክርስትያና አስተዳደርና ምዕመናን እንዲያውቁትና እንዲጠነቀቁ ልንገልጽ ተገደናል። እኒህ ግለሰቦች የሀይማኖት ደንቃራዎች ብቻ ሳይሆኑ የርኩስ መንፈስ ማደሪያዎች ናቸውና።

አንተን አስባረው የቀድሞ የሚካኤል ቄስ የነበረና ከአገልግሎት መድረክ ላይ “እኔ ሳይገባኝ ያለዕድሜዬ ቅስናን የተቀበልኩ“ ብሎና ቅስናውን ያፈረሰውን መስፍን የማኅበረ-ቅዱሳን አባል ለማስቀጠር ሲሆን፤ ይህም ባይሳካ ቦዘኔውን ካድሬ ሲደልልን ለማስቀጠር ብሎም የመኖሪያ ፈቃዱ ተስተካክሎለት በየቦታው ምዕመናን እንዲያምስ ለማድረግ በቤተክርስትያናችሁ ውስጥ ዘመቻው እናንተን በመከፋፈል ተያይዘውታል። ስለሲደልል አንድ ነገር እናካፍላችሁ እንወዳለን “ የሚካኤል ቦርድ ለምን ኪዳን እየመጣህ አታደርስም ብለው ሲጠይቁት እኔ እንደሳቸው አረጋሁም፣ ገና ትኩስ ነኝ፣ ደሜም የሞቀ ነው“ ብሎ ያለና ለቅስና ያልበቃ አጥበርባሪ፣ለቤተክርስትያን መሰሪ፣ ከወስላታ ዱርዬ የማይለይና ቅዳሴውንም የትንሴ ለት ሲለውጥ እጅ ከፍንጅ የተያዘ ነው።

ሌላው ደግሞ የነዚሁ ቡችላዎች የሆኑት እንዚህን መሰሪዎችን ወደ ሚካኤል መልሶ ማስቀጠሩ ልፋታቸው የከሸፈባቸው ተባባሪዎች ናቸው። ምክንያቱም በነሱ ምትክ ሚካኤል አዲስ ቀጥራልና። ስለዚህ ጊዮርጊሶች አንድ ሁኑ፣ ጽኑ፣ በጸሎትና በጾም ትጉ፣ ሊለያዩአችሁ የተነሱትን ድል የምታገኙት በዕምነት ነውና እኛም በፀሎት ከናንት ጋር ነን። ሚካኤል ያገኘውን ድል ለናንተም ፈጣሪ ይስጣችሁ፣ ጌታ ይጠብቃችሁ እንላለን።

እርሶስ ምን ይላሉ?

Thursday, June 10, 2010

እኝህ አንባቢያችን እንዲ ማለት የፈለጉ ይመስለናል፡-

የርሶ ብዕር አስተያየት ተሳትፎ ሕብረተሰባችንን ይጠቅማል ያሉትን አይንፈጉን ገንቢነቱ ቦታ ይኖረዋልና!ማሳሰቢያ፡ ይህ ገጽ የተዘጋጀው የተለያዩ የኅብረተሰባችንን ሀሳብ ለመለዋወጫ እንጂ ለሚሰጡት ማንኛውም አስታየቶች በማንኛውም መንገድ ተጠያቂ አይደለም። ጉግል ድርጅትም ኃላፊነት አይወስድም። ኃላፊነቱ በሙሉ የአስታየት ሰጪው ብቻ ነው።


Anonymous said...
ato eyoel nega bmercha teshenefeu
yatuten seletan bekodita lesemelesu
degafiwchachewon eyasebasbu mehonachewon andande mmenchuch ytkomalu semonun pitishn lebord yasegebut budenochem yezhu tegebar
tebbariwch endehono yminageru ena
endemiktelubetem sinagru tdemetal

June 10, 2010 6:20 PM

እኝህ አንባቢያችን እንዲ ማለት የፈለጉ ይመስለናል፡-

“አቶ ኢዮኤል ነጋ በምርጫ ተሸንፈው ያጡትን ስልጣን በኩዴታ ለመመለስ ደጋፊዎቻቸውን ያሰባሰቡ መሆናቸውን አንዳንድ ምንጮች ይጠቁማሉ ሰሞኑንም ፐቴሽን ለቦርድ ያስገቡት ቡድኖችም የዚሁ ተግባር ተባባሪዎች እንደሆኑ የሚናገሩን እንደሚቀጥሉበትም ሲናገሩ ተደምጣል“።

ከአምዱ አዘጋጅ፡- አንባቢያችንን ስለተሳትፎ እያመሰግን ፣ ኢዮኤል በምርጫ ተሸንፎ ሳይሆን የተመረጠበትን ኃላፊነትና የመረጠውን ምዕመን አሳፍሮ ከእግዚሐብሔር አገግሎት ፈርጥጦ ታቦቱንም ደፍሮና አስቀይሞ በፈጠረው አምላክ ፊት የኮበለለ ሲሆን እኛ ይቅር ብለነዋል ከአምላኩ መታረቅ ግን የሱ ነው። ሁለተኛ ለአገልግሎት እንካ በዚህ ቦታ የለውምና አያስቡ። አላርፍም ካለ ጠበቃ ፍለጋውን ካሁኑ ቢጀምር ስለሚያስፈልገው ይቺን ሹክ የሚለው ቢኖር ጥሩ ይመስለናል፣ ምክንያቱም የሱ ጣት ምልክት ያላረፈበት የምዝበራ ሰነድ የለም ማለት አዳጋች ነውና ወዮ ያቺ ቀን እንደተባለው እንዳይሆንበት እንሰጋለታለን። በሌላ በኩል ደጋፊ የሚባሉት ከወልቃይት በኩል ያሉትም ሆነ በጣት የሚቆጠሩትም አያስጋዎት ቁርጠኛው ቀን ሲመጣ ወይንም እንደቢጤው ከጽዋና ከቁብ እንደተባረረው አሊያም በምርጫ ሳጥን እንደነ ፈትለወርቅ ለመክሰር ብቻ ነው እንላለን።

ጋሼ ተኮላ

የርሶ ብዕር አስተያየት ተሳትፎ ሕብረተሰባችንን ይጠቅማል ያሉትን አይንፈጉን ገንቢነቱ ቦታ ይኖረዋልና!ማሳሰቢያ፡ ይህ ገጽ የተዘጋጀው የተለያዩ የኅብረተሰባችንን ሀሳብ ለመለዋወጫ እንጂ ለሚሰጡት ማንኛውም አስታየቶች በማንኛውም መንገድ ተጠያቂ አይደለም። ጉግል ድርጅትም ኃላፊነት አይወስድም። ኃላፊነቱ በሙሉ የአስታየት ሰጪው ብቻ ነው።


ሰላምታችን ለሁላችሁም ይሁን። በተለይ የመረዋው ጋሼ ተኮላ አዲሱ ሥራህ እንደምን ይዞኃል? ለምርጫ ማዋከቢያ ከኢትዮጵያ መንግሥት ለአንተና ብጤዎችህ ለዳላስ የተመደበው ድርጎ የዘላለም መስሎህ ከሻትል መባረርህ፣ ቤተክርስትያንና ጸረ ሀይማኖት ሥራህን የተጸየፉብህም ወገኖች ፊት መንሳታቸው፣ አሽሽቶህ አሁን ዳረጎቱ በመቆሙም ሌላ Looser (ይህ ቃል ያምሀልና)እንዳትሆንብን ለስሚዝ ኩባንያ እድሜ ለማኝ ለመሆን እንካን አበቃህ።

ይቺ ገጻችን በጣም ስላስቆጣችህ ልትቀባት ያልሞከርከው የቀለም አይነት የለም። ሊያው ያንተ ጎራ ብቻ ሳይሆን ያንተው ኣኩይ የተግባር ወዳጆችህ ኣነ ሰላም ተዋህዶዎችም (ሽኮኮው በቀለና መስፍን ኢሕአፓው) እርር ብግን ብለውብናል። ከሁለታችሁም ጎራ እውነቱን እየተረዱ የራቁዋችሁ በየቀኑ በዝተዋልና በቅርቡ ብቻችሁን የንስህ እድል እንካን ሳታገኙ እንዳታልፉ እንሰጋላችኃለን። እኛና እናንተ በዚህ ገጽ ያቀራረብ ችሎታ እንደናንተ አገማገም ሙያውም ሆነ ችሎታውም የለንም። እኛ ተራ፣ በሙያችንም ሆነ በኑራችንም ቀጥተኞች፣ የማንንም መውደቅ የማንሻ፣ ፈጽመንም ንጽህና የሌለን ነገር ግን በሱ አምነን በመጠመቃችን ብቻ እንደዳንን ያመንና፣ ባልንጀራችንን እንደራሳችን ፣ ወንድማችንንም የምንወድና እውነትን የያዝን ብቻ እንጄ እናንተ ኣንደምታስቡት የፖለቲካም ሆነ የሌላ ድህረ-ገጽ ወይንም የቦርድ አፈ ቀላጤ አለመሆናችንን በፈጣሪ ስም እውነት ብለን እንናገራለን። ለዚህም ነው ብዙ አንባቢያን ከቀን ወደ ቀን በአጭር ጊዜ ውስጥ መጨመር ብቻ ሳይሆን አንባቢዎቻችንም ወደ ትክክል አቅዋም እይተመለሱ ያሉት። ከሁሉም በላይ ይህ ገጽ ምን ጊዜም ቤሆን በሩን ለእናንተም ጭምር ክፍት ያደረገ ገጽ ነው። የሁሉንም አስተያየት እያስተናገደ ይገኛል።

የኛ ገጽ ባይገርማችሁ ከኢትዮጵያው ኤምባሲ አልፎ የቤተክሕነትና የመንግሥትን ቀልብ እንደሳበ ከኤምባሲው ውስጥ ያሉት ወዳጆቻችን አካፍለውናል። ስለ ጠላታችሁ ሰንበቴም ከናንተ አልፋ ለጳጳሱ ደብዛዋን እንዲጠፉላቸው የቅርብ ዘመዳቸውና ሚስጥረኛቸውን የእንግሊዝ ዜጋ ነገር ግን በኢትዮጵያ ዲፕሎማት ፓስፖርት አለምን የሚዞረውን ሰላይ በለንደን 3 አባላት ያለው ቡድን አቃቁሞ ስራውን እየሰራ የሚገኘውን ተመድቦበታል። ይኸው ቡድን ያቀፈው የኮምፒተር ባለሙያዎች ሲሆን፣ እነሱም ከኤዥያ በተለይ ከቻይና እንደዚሁም ከአውሮፓ ዕውቀት ያላቸውን እየተኮናተሩ የሳይበር ዘመቻ ያካሂዳሉ። ቡድኑም ተጠሪነቱ ለውጭ ጉዳይ ሚኒስተርና ለአገር ውስጥ ደህንነት ጉዳይ ስር የሚገኝ የጸረ-ስለላ መምሪያ ቢሮ ነው። ሰንበቴም እንደ ሌሎቹ የዚህ ቡድን ሰለባ ሆኖም እንደሆነ ገና አላረጋገጥንም፣ ነገር ግን የሚያወጣው የጽሁፍ መረጃዎች ግን አዲስ አበባን እየረበሻቸው ይገኛል። እኛም በተጠንቀቅ እንጠብቃለን።

በርግጥ እስካሁን ይህ ቦርድ አጠፋ የምንለው ባይኖረንም በሜይ 2ቱ ረብሻ ሳቢያ ለጊዜው በቁጥጥር ሥር የነበረችውን ግለሰብ አንደኛው አባል ጣልቃ ገብቶ ማስለቀቁ (በቅን ልቦና) ትክክል አለመሆሁን ሲቀበል፣ የሕግን ሂደት አደናቅፋል እንላለን። ከዚህ ውጭ ግን ለቦርዱ እንዲ ብሎ ገብቶ እንድህ ብሎ መለሰባቸው ብሎ የናንተ ትችት ፍሬ ቢስ ብቻ ሳይሆን የከፋ ስም ያስከትልባችኃል። መረጃ መረጃ አሁንም መረጃ አምጡ ኣንላለን። እንደ ትችታችሁ ከሆን መናገር ያሻችሁት ስለ አዜብ ኃይለማሪያም ነው። ገና ውሳኔው ሳይወጣ የናንተ ገጾች ዜናውን ለማብሰር ኣሽቅድድም ያዛችሁ። እኛ ደግሞ የምንጠይቃችሁ ያን ያህል ለጉዳዩ ቅርበት ብቻ ሳይሆን ቁጭት የጨመራችሁን ጉዳይ ለምን በአምዳችሁ አውጥታችሁ እኛም የራሳችንን ግንዛቤ እንድንጨብጥበት አታበቁንም?

አዜብን ካነሳን ከምንለው በጥቂቱ፡- በቁርባን ባላን አስራ ከተባረረው በናንት መላክ ሳህል ለኛ ድብተራ ወይንም ካድሬ ሲደልል ጋር ያላትን፣ ብቁነታን ሳትመዝን (ሊያው እሳ ብቻ ሳትሆን አበሮችዋን ጨምሮ) የተቀበለችውን የሥጋ ዎደሙ ይዛ በሜይ 2ቱ ረብሻ ልጃን ደብቃ መጥታ ጩሁ እያለች ስታስጮህ የነበረች፣ ይኸው ሲከሽፍ ከከሳሶችና አስከሳሾች ጋር ተባብሪ፣ ከማኅበረ ቅዱሳን በሚሰጣት መመሪያ ከአበሮችዋ ጋር በመሆን የስብሰባ ቦታ ጥያቄዋ ውድቅ የሆነባትእያልን ብዙ ማለትም እንችላለን። ለርሳም ሆነ ለቢጤዎቻ የምንለው ንስሀ ግቡ፣ በስጋ ወደሙ ተጠብቁ፣ ከቂም በቀል ራቁ፣ በጾም ጸሎት ትጉ እርሱ ቤቱንና በጎቹን ይጠብቃልና። ስለዚህ ለአዜብ የምንለው ፡- ስለስጋወደሙ ፣ እንዴትስ ተወስኖ እንደሚኖር ፣ ክርስትና ህይወቱ እንዴት እንደሚኖር አስፈላጊውን ትምህርት በቶሎ መውሰድ ይገባሻል። አንቺም ያስፈረምሻቸውም ተመሳሳይ እርምጃ እንዲወስዱ የማድረግም ግዴታ አለብሽ። ሌላው ወዳጅሽ ዋሾውና የሕብረተሰባችን ዝቃጭ ሙላው ወራሽ የሚሉት ወደ አገር ቤት ይሄዳል ማለትን ሰማንና፣ተሹሞ ከመጣም እነ ታደሰ ጸሀይን እጅ እንዳያስነሳ ቀድመውትም ከሆነ ከቦሌ ወደ ከርቼሌ እንዳይገጥመው ሹክ በይው።

ከዚሁ ሳንርቅ ጌታቸው ትርፌ ለማኅበረ ቅዱስን የህልም ቦርድ ሊቀ መንበር ምክትሉ ደግሞ ተፈራወርቅ አሰፋ ገና ሳይደርሱ ሹም ሽር አድርገው ጌታቸውን ወደሌላ አዞሩት፣ የተሰጠውም ምክንያት ሆዱ የማይታወቅ ፣ ሰልል ተብሎ ወደ ቤተክርስትያን የማታ ትምህርት ቢላክ ወደ መጨረሻው ላይ ምዳየ ምጽዋት ገንዘብ ለምን እንዲዞር አደረክ፣ በትምህርቱ ልቦናው ተነክቶ በማብቂያው ላይ ቆሞ በሰጠው አስተያየት ፤ ይኽንኑ ሰምተውት ከነበሩት ምዕመናን መካከል ለመወያየት ለሰኞ በመቃጠሩ፣ ሲሆን ቀጠሮውንም እንዳይገኝ አድርገውታል። ሚስቱም ከዚሁ ጎራ የተሰጣት የናቶች መዘምራንና የሴቶችን ክፍል እንድትሰልልላቸው ነው።

ሌላው ጋሼ ተኮላ የተገኘበት የራት ግብዣ በአዲስ አበባ ምግብ ቤት በወያኔ ደጋፌዎች ቁጥራቸው ከ30 የማይበልጡ የተገኙበት ሲሆን፣ አላማው እንደቀዳዳውና መሀይሙ ሙላው ወሬ የምርጫ ማሸነፍ ሳይሆን፣ ኤች አር ለተባለው ጉዳይ የአሜርካን ምክር ቤት በኢትዮጵያ ላይ ያለውን በተመለከተ ነበር። በዚህ ምሽት ጋሼ ተኮላ ከወትሮ የተለየና በጣም የቀዘቀዘ ሆኖ በመገኘቱ አፉ እንደታሰረበት ቸኩሎ ወጥቶ ሄዳል። ሌላው የሱ ቢጤ ጸረ-ሀይማኖትና ጸረ-ቤተክርስትያኑ፣ የቤተክርስትያኑ አጋር ከሳሹ ፀሐይጽድቅ ቤተማርያም ግን ፉከራና ቀረርቶ ቀረሽ በደርግ ላይ እንደለመደው ሁሉ የወያኔን መንግሥት ሲያወድስና ሲያመሰግን ነበር።
ይህ አድርባይ በደርግ ጊዜ የተደበቀ ጉዱን እንዳይወጣ ወይንም ቢወጣም ለይቅርታ ይሆን? ወይስ እዚ በመንግሥት ድጋፍ የሚኖርበት ቤት፣ ታክስ ግዴታውን ያላማላ እንደጋደኞቹ፣ ኢምግሬሽንን ዋሽቶ ያገኘውን፣ ወዘተ… ሲወጣበት መሸሸጊያ ፍለጋ ነውን?

ጋሼ ተኮላን የተተናኮለው መጥፎ መንፈስ ዛሬ አይደለም ከልጅነቱ ነው። ነፍሱን ፈጣሪ ይቀበልና ከደጋጎቹ ይጨምርልን የምንለው ወንድሙና ወዳጃችን መስፍንን የምታውቁ ሁሉ ፤ ከዳዊት ያልተለየ ቤተክርስትያን ወዳጅ፣ ሰው አክባሪና ትሁት፣ የማይጠገብ የነበረው ወንድምህ አሁን በሕይወት ኖሮ ቢሆን እንዴት አዝኖ ባፈረብህ። ትልቅ ስህተትና ጥፋት በዚህ እድሜህ ለፕለቲካ ብለህ መስመር የለቀክ። ይኼ የኢሕአፓ ፖለቲካ ቦታ አይደለም የዚያንም ተለምዶህን ከዚህ ቅዱስ ቦታ አርቅ። ከምዕመናን አልፈህ ከታቦት ጋር ግጭትህን አቁም ብትችል ንስህ ግባ፡ ቅዱስ ሚካኤልን ቦርድ ካልወደድክ ሌላ ቦታ ሂድ። የሌሎቹን ዘመዶች ተነኩ ብለህ አትፎክር አሁን አንተም ዘር ማንዘርህን እንዳታስቆጥረን። ለመሆኑ ባለቤትህና ዘመዶቻ ምን ይበሉ? ለልጆችህስ ምን እያወረሳችሁ ነው?

ሌሎቻችሁም ስለ ፈጣሪ ብላችሁ ቤተ ክርስትያንና ምዕመናን አታውኩ፤ ለሰላምና ለፍቅር ተነሱ!

እርሶስ ምን ይላሉ?

Tuesday, June 8, 2010

ሰላም ተዋሕዶ Selam - Tewahedo said...

የርሶ ብዕር አስተያየት ተሳትፎ ሕብረተሰባችንን ይጠቅማል ያሉትን አይንፈጉን ገንቢነቱ ቦታ ይኖረዋልና!ማሳሰቢያ፡ ይህ ገጽ የተዘጋጀው የተለያዩ የኅብረተሰባችንን ሀሳብ ለመለዋወጫ እንጂ ለሚሰጡት ማንኛውም አስታየቶች በማንኛውም መንገድ ተጠያቂ አይደለም። ጉግል ድርጅትም ኃላፊነት አይወስድም። ኃላፊነቱ በሙሉ የአስታየት ሰጪው ብቻ ነው።


ሰላም ተዋሕዶ Selam - Tewahedo said...
ሰንበቴ ብሎገ ከሠረ ፡፡ የሥራቤቶችንም አሉባልታ ጀመረ ፡፡ ከትንሽ ቀን በኋላ ደግሞ ይሄም ይቆምና በሌላ ብሎግ ስም ወጥቶ እናገኘዋለን፡፡ ጉልቻ ቢለዋወጥ ወጥ አያጣፍጥም ፡፡አቀራረቡ የሥነ ጽሑፍ ሕግን የተከተለ ሳይሆን ተራ ስድብ ስለሆነ ከትንሽ ጊዜ በኋላ እንደ ሰንበቴ ብሎግ በሕዝብ የተናቀ ይሆናል፡፡ሰላም ተዋሕዶም ከዚህ በኋላ ጊዜዋን ይህን ትራሽ በማንበብ አታጠፋም ፡፡

June 7, 2010 10:34 PM

ውድ የሰላም ተዋህዶ ገጽ አዘጋጆች፣ እንደምን ሰንብታችኃል? እናንተም እንደኛው እግዚሐብሔር በአምሳሉ የፈጠራችሁ በሰውነታችሁ የምንወዳችሁ ነገር ግን ስራችሁን የምንጸየፍባችሁ፣ ከዚህ በላይ ለሰጣችሁን አስተያየት እናመሰግናለን። ይህቺ ገጻችን ከመቆንጠጥ አልፋ በሽታችሁን እየዳበሰች በቀላሉ የሚድኑትን ወገኖቻችንን ከአጠገባችሁ እየነጠቀች ይገኛል። የተቀሩትም እውንቱን ሲያዩ ሁላችሁም በንስሐ ትመለሳላችሁ።

ይህቺን ገጽ የሚያዘጋጀው፣ እናንተ እንደምታስቡት ሳይሆን ወይንም ሰንበቴ አለመሆኑን ከዚሁ እናረጋግጥላችዋለን፣ አላማውም ከሕብረተሰባችን ውስጥ ያለውን ችግር መቅረፍ ባይቻል ዕውነተኛ ግንዛቤ ለማስጨበት እንዲረዳ የተዘጋጀ ገጽ ነው። የሚመስላችሁን ግለጹበት እናንተም የሕብረተሰባችን አካሎች ናችሁ፣ የኛ ችግር የናንተ፣ የናንተ ደግሞ የኛ የሚያደርጋቸው ሒደቶች ብዙ ናቸውና። ሥለሥራቤቶች አሉባልታም ነካ አድርጋችኃል፣ በተረት ካልሆነ የምታውቁት ግንዛቤ ትንሽ እንስጣችሁ። የዐጼ ኃይለሥላሴ ቤተመንግትስት የምግብ ክፍል ባለሙያዎች ሲሆኑ እንደናንተ አገላልጽ አሉባልተኞች ሳይሆኑ የነሱን አስተያየት ለማጣጣልና ገንቢነት የሌለው የደረጃ ማሳነሻ የቀድሞ አስተዳደር ስልት መሆኑን ተማሩ እንላለን። ሌላው ጥቅሳችሁ ደግሞ መልሶ እዛው ማዕድ ቤት ከተታችሁ። አንድ እውነት ያላችሁት ቢኖር የዚህ ገጽ አዘጋጆች የሥነ ጽሁፍ ችሎታ የላቸውም ከናንተም ሆነ ከሌላ ለመማር ዝግጁ ናቸው፣ ነገር ግን የሚያቀርቡት ሁሉ መጣጥፍ የእውነት ነውና አትጠራጠሩ። እድሜ ሰጥቶን እናንተም ወደ እውነት መንገድ ገብታችሁ፣ ያስቀየማችሁትን ፈጣሪ ንስሀ ተቀብላችሁ፣ ልታፈርሱት የተነሳችሁትን ቤተክርስትያን በአገልግሎት ክሳችሁ፣ ያቀያየማችሁትን አስታርቃችሁ፣ የተቀየማችሁትን ይቅርታ ጠይቃችሁ ወደ ትክክለኛው መንገድ ተመልሳችሁ ለማየት የዚህ ገጽ ጸሎትና ፍላጎት እንጂ በቶሎ በኖ አይጠፋም።

ስለሰጣችሁት አስተያየት ይኽን ያኽል ካልን በኃላ ለመሆኑ በአዲሱ አቅርቦታችሁ ላይ ‘ሠበር ዜና‘ በሚል የጣፋችሁትን ስናይ፣ እናንተን እንደምን እንበላችሁ ! እንድንማማር ከፈቀዳችሁ “ በቅርቡ ወይንም ትኩስ ዜና“ ብትሉት ፣ የባዕድ ቃል ቀጥታ ትርጉም መጠቀሙ የራስን ሀብትና ባሕል ማጥፋት ይሆናልና ይታሰብብት እንላለን። ከዚሁ አርስት ሳንወጣ የሰጣችሁት ዜና ሳይሆን አስነዋሪ ምግባራችሁን ነው የገለጻችሁት፣ እናንተን ካልመሰለ ጥላቻን መንዛት የክርስትና ተግባር አይደለም፣ ከራሱና ከቤተስቡ አልፎ ሌላውንም ቀጥሮ የሚያስተዳርን ወገን ማበረታት ሲገባ የዚሁን ግለሰብ ምርት በሚያቀርብበት መደብር እየሄዱ ምርቱ ላይ ተንኮል ማድርግ በህግ ያስወነጅላል! ይኽ አይነት በቀል እናንተና ብጤዎቻችሁ መቆጠብ ይገባችኃል። ስለናንተ በአበስኩ ገበርኩ ብቻ አያቆምምና !

ለመሆኑ ራሱን “ማኅበረ ቅዱሳን“ እያለ የሚጠራው ድርጅት እንዴት እንደተፈጠረ ለአንባቢዎቻችን ትንሽ ማስጨበት እንወዳለንና በሚቀጥለው ጽሁፋችን ይጠብቁን። ከቻልንም በተቀጣይ ለምን ጌታቸው ትርፌ በማኅበረ ቅዱሳን ከተሰጠው የኮሚቴ መሪነት ወደ ሌላ ተዘዋወረ? የትላንት ማታው የወያኔ ራት ግብዣ ላይ ጸህይጽድቅና የተኮላ ድርሻ ምን ነበር? እርሶስ ምን ይላሉ?

Sunday, June 6, 2010

ሰላም ተዋሕዶ Selam - Tewahedo

የርሶ ብዕር አስተያየት ተሳትፎ ሕብረተሰባችንን ይጠቅማል ያሉትን አይንፈጉን ገንቢነቱ ቦታ ይኖረዋልና!ማሳሰቢያ፡ ይህ ገጽ የተዘጋጀው የተለያዩ የኅብረተሰባችንን ሀሳብ ለመለዋወጫ እንጂ ለሚሰጡት ማንኛውም አስታየቶች በማንኛውም መንገድ ተጠያቂ አይደለም። ጉግል ድርጅትም ኃላፊነት አይወስድም። ኃላፊነቱ በሙሉ የአስታየት ሰጪው ብቻ ነው።


ሰላም ተዋሕዶ Selam - Tewahedo


ሰላም ተዋሕዶ - በዳላሰ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን የአስተዳደር ቦርድ አባላት ችሎታ እጦት ምክንያት በቤተ ክርስቲያኑዋ ላይ እያደረሰ ያለውን ከፍተኛ ጥፋትና ይህንኑ ለማስተካከል እየተደረጉ ያሉ ጥረቶችን ለአጥቢያውና ለአካባቢው ምእመናን የሚያስገነዝብ ፤ በእውነት ላይ የተመረኮዘ ጊዚያዊ ብሎግ ነው፡፡Blogging Since October 2009


‹ከዚህ የመጨረሻ ዕድል በኋላ ግን እጃችንን አጣምረን አንቀመጥም ! መረጃዎቻችንን ይዘን የ I.R.S ን በር እናኳኳለን ! ሕዝቡ ግን ያን ጊዜ ይህ ለምን ሆነ እንዳይለን !

FRIDAY, JUNE 4, 2010
የስብሰባ ጥሪ !

TUESDAY, JUNE 1, 2010
ማኅበረ ቅዱሳን ጉባዔውን በመልካም ሁኔታ ጀምሮ አጠናቀቀ !

ዛሬ የምናካፍላቹህና የናንተን የአስትያየት ተሳትፎ የምንጠይቀው ከዚህ በላይ ከሰላም ተዋሕዶ ገጽ ያገኘነውን ነው።

ይህ ገጽ የሚታወቀው የዳላስ ማኅበረ ቅዱሳን እየተባለ የሚጠራው ከልት ድምጽ ሆኖ ነው። ከመጀመሪያው አላማውን ሲገልጽ ያነጣጠረው በዳላስ ቅዱስ ሚካ ኤል ላይ ነው። ሌላው ደግሞ ከመንፈቅ በላይ ማስፈራሪያው የግብር ሰብሳቢውን መስሪያቤት ነው። የተሰነጽው ተወልዶ አድጎ እንዳያነብባችሁና እንዳይሰቅባችሁ ፣ ዕውነተ ቢስ ናችሁና በማኅበረ ቅዱሳን ስም የተዘረፈው እያነቃችሁና ሃባዜው እያስለፈለፋቸው ነው።

በFRIDAY, JUNE 4, 2010 የስብሰባ ጥሪ ! በሚል በገጻቸው ያወ ጡት ደግሞ ብጤዎቻቸው ከሌላ ቡድን ሆነው አንዴ በክስ ሌላ ጊዜ ደግሞ እናስታርቅ ወይንም ቦርድ እንገልብጥ እያሉ ጀንበር ለጠለቀችባቸው ጸረ ሀይማኖትና ጸረ ቤተክርስትያኖች ቱልቱላ መሆኑን በግልጽ ያስረዳል። ከዚሁ ሳንወጣ ፣ ከአሁን አሁን ንስሀ ይወስዳሉ ብለን ከምንጠብቃቸው መካከል ኢዮኤል ነጋ ፤ ሀይሉ አራጋው ፤ እንደዚሁም ፈትለወርቅ የቀድሞ ቦርድ አባላትና ሌላ የ11 ግለሰቦች ስም ዝርዝር የያዘ የስብሰባ ፈቃድ ጥያቄ ለቦርዱ ገብቶ ተከለከለባቸው። የዚሁ ኮሚቴ ተወካይና መሪ ደግሞ አዜብ ኃይለማሪያም ስትሆን ያቀፈችው ከወልቃይት ተውላጆችና የባለቤቶቻቸውን ስም ዝርዝር ያካተተ ነው። እንደሚታወቀው ሁሉ እነ አዜብ የወያኔ ደጋፊ ብቻ ሳይሆኑ ለጠቅላይ ሚንስትሩ ሚስት የቀረበ ዝምድና ያላቸው ናቸው። ለዚሀም ነው እነ ጌታቸው ትርፌ ወደ ወልቃይት ሲወርዱ በመንግስት ወጪ የመንግስት ወታደሮች 24 ሰአት በአደጉበት ቀዬ ጥበቃ እንደሚያደርጉላቸው በኩራት የሚናገሩት። ሌላው ደግሞ ሳይሆን ወያኔ ነኝ የሚለውና በዋሾነቱ አቻ ያጣው ፣ በምግባሩ ለአመታት ሲጠጣ ከቆየው ጽዋና ዕቁብ የተባረረው ፣ ለአዲሱ የቤተክርስትያን ክስ አስተባባሪ ብቻ ሳይሆን የራሱን ጠበቃ የቸረው ሙላው ወራሽ ከነሚስቱ ፣ ይኼንኑ ክስ የገንዘብ ድጋፍ የማደርገው እኔ ነኝ እያለ የሚኩራራው ሀይሉ እጅጉ ከነ ሚስቱ የመሰሉ ይገኙበታል። የሚገርመው እነኢዮኤል ጥሩ የሰሩትን ስናስታውስ የመጥፎ ስራቸው ውጤት አብረው ማሻሻል ሲገባቸው ለምን አዋኪ ይሆናሉ? እስከምናውቀው ድረስ ለቤተክርስትያን ማገልገል ለዘር የሚተርፍ በረከት ለማግኛ እንጂ ለዝና ወይንም ለክብር አይደለም። ከዚህስ የተለየ ምን ይኖራቸው ይሆን?

ማንም ቢሆን ምንም ሕግም ቢባል ያለውን ቦርድ መለወጥ የሚቻለው ቦርዱ ፈቃደኛ ሆኖ ወይም በሰላም ጊዜውን ሲጨርስ ብቻ ነው። በሌላ መንገድ ለማፍረስም ሆነ ለመለወጥ የሚደረገው ትግል ፍሬ ቢስ መሆኑን ከዚሁ ልናስገነዝብ እንወዳለን ፣ ታገሱም እንላለን። ምክንያቱም የመተዳደሪያ ደንቡ ላይ ያለው እየተገበረ መሆኑን አልገባ ያላቸውና ፤ ወደ መሰሪ መንገድ የገቡት እንዲሁም አብረው ከኖሩ ወገኖቻቸው የተቀያየሙትን ስላየን ነው።

TUESDAY, JUNE 1, 2010 ማኅበረ ቅዱሳን ጉባዔውን በመልካም ሁኔታ ጀምሮ አጠናቀቀ ! ይህ የዳላስ ድርጅት አንደበት የሆነ ገጽ ምግባሩና ስሙ ለየቅል ነው። እንደሚታወቀው ሁሉ አቡነ ጳውሎስን ብሎም የወያኔን መንግስት ከመገልበጥ ወደ ኃላ እንደማይል ባለፈው አመት አዲስ አበባ ላይ ጳውሎስንና መንግስትን አስደንግጣል። ይኽ ድርጅት በቀድሞ ኢሀአፓዎች አሁን ሀይማኖተኞች መሪነት የሚንቀሳቀስ ነው። የተማሩትንና የተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎች ይዞ ጥሩ ስራ ሲሰራ በሌላ ጎኑ ደግሞ ፖለቲካና ጸረ ክርስትና ስራ የሚያራምድ ቡድን ከሀገር ቤት አልፎ በየትኛውም ክፍለ ዐለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስትያን ውስጥ ተ ሰራጭቶ ይገኛል። በዳላስ ሚካኤልና በሌሎቹም ውስጥ ነጠላ ለብሰው ሲያስቀድሱ፣
በመዘምራንነት፡፣ በትምህርት ክፍል፣ በበጎ አድራጎት፣ በህጻናት ክፍልና በሌሎችም ውስጥ በመሳተፍ ቤተ ክርስትያንን የሚያደሙ፣ በጣባብነት የተወጠሩ፣ ወዘተ……. ናቸው። ሚካኤል ውስጥ በመዘበሩት ሊጋለጡ ሲሉ፤ ከተራ ምዕመን ቀሳውስትና ቦርዱንም ጭምር ለመለያየት የረጩት መርዝ ያልዳኑት ዛሬም ቤተ ክርስትያንን ሲጣሉዋት ይታያሉ።

እርሶስ ምን ይላሉ?

Friday, June 4, 2010

ዜና እረፍት

የርሶ ብዕር አስተያየት ተሳትፎ ሕብረተሰባችንን ይጠቅማል ያሉትን አይንፈጉን ገንቢነቱ ቦታ ይኖረዋልና!ማሳሰቢያ፡ ይህ ገጽ የተዘጋጀው የተለያዩ የኅብረተሰባችንን ሀሳብ ለመለዋወጫ እንጂ ለሚሰጡት ማንኛውም አስታየቶች በማንኛውም መንገድ ተጠያቂ አይደለም። ጉግል ድርጅትም ኃላፊነት አይወስድም። ኃላፊነቱ በሙሉ የአስታየት ሰጪው ብቻ ነው።


As you know one of our community member W/ro Selamawit Mekuria passed away on Wednesday June the 2nd, 2010. You may call the number below to find out the date, time and place of her funeral service or express your condolences.

We are passing our condolences for the family and her friends.

Family Address …
Ato Diriba K. Terfassa
1210 Anacostia Lane, Allen, Texas 75002
PH # (214) 536-3776

የተከበራችሁ ውድ የአካባቢያችን ነዋሪ ወገኖች፣
እንደ አውሮፓውያን አቆጣጥር ሰኔ 2 ቀን 2ሺ10 የዳላስ አካባቢ ነዋሪ የነበሩ ወ/ሮ ሰላማዊት መኩሪያ የተባሉ ወገናችን በመለየታቸው የተሰማንን ሀዘን ከልብ በራሳችንና በገጻችን ስም እየገለጽን ለቤተሰቦቻቸው መጽናናትና ብርታትን እግዚሀብሔር ይስጥልን።

ባለቤታቸውንና ቤተሰባቸውን ለማጽናናትም ሆነ የቀብሩን ቀን፣ ሰአትና ቦታ ለማወቅ ለምትፈልጉ ሁሉ

አድራሻቸው …
አቶ ዲሪባ ተርፌሳ (ባለቤታቸው)
1210 Anacostia Lane, Allen, Texas 75002
ስልክ ቁጥር - (214) 536-3776

እግዚሀብሔር ቤተሰብና ወዳጆቻቸውን ሁል መጽናናትን ይስጥልን።

Ethics vs Rule of Law

የርሶ ብዕር አስተያየት ተሳትፎ ሕብረተሰባችንን ይጠቅማል ያሉትን አይንፈጉን ገንቢነቱ ቦታ ይኖረዋልና!ማሳሰቢያ፡ ይህ ገጽ የተዘጋጀው የተለያዩ የኅብረተሰባችንን ሀሳብ ለመለዋወጫ እንጂ ለሚሰጡት ማንኛውም አስታየቶች በማንኛውም መንገድ ተጠያቂ አይደለም። ጉግል ድርጅትም ኃላፊነት አይወስድም። ኃላፊነቱ በሙሉ የአስታየት ሰጪው ብቻ ነው።


We want to share the following e-mail that we received from a friend. Even though, the entire piece reflects only the view of the author, there is a good part may be learning to our community. We are open to hear your opinion. Thanks.


Joe Sestak, ethics vs rule of law?

Recently, our political parties reached a crossroads that leaves much to be desired in interpreting the rule of law vs ethical behavior. A Democratic congressman from Pennsylvania challenged an old line established Democratic member of the senate.

Congressman Joe Sestak won the primary, ending the career of an 80 year old, five term senator for the senate seat -- the seat held by Arlen Specter. Specter had switched to the Democratic Party thinking it would ensure his reelection to a sixth term.

President Obama was elated, as it gave his party a filibuster-proof majority for his agenda. Obama promised to support Specter in his reelection bid.

When it was discovere that Congressman Sestak was considering running for the senate seat, it was as if a bomb had exploded in the White House. What was supposed to be an unopposed primary now had the potential for a younger man to upset the apple cart.

To make matters worse, political unrest was rampant in the land. There was a lack of trust in government demonstrated by the formation of “tea parties” across America.

The overriding issue was the ramming of the health care reform bill through the senate. Senator Specter was instrumental in the process for Obama.

Now this young pompous congressman had the audacity to challenge the man who had given the Democrats their much needed victory and kept Obama’s administration from facing a defeat by the Republicans.

In light of the promise to support Specter’s bid for reelection, it was determined that Obama would need to do something, since the challenge was coming from within the party. His going to Pennsylvania to campaign personally for Specter was not the answer.

In the recent Massachusetts election, Republican Scott Brown was elected to the Senate. That seat had been held by the Democrats for decades under the late Senator Ted Kennedy. Obama had personally gone to support the Democratic candidate, Martha Coakley, and had come away empty handed.

In Pennsylvania, it was not a Democrat running against a Republican, as in Massachusetts, but instead a younger energetic Democratic politician running against a member of the political establishment from the same party with over 30 years of seniority.

To get Sestak out of the race, it would take nothing less than a monumental offer of political influence.

The Issue Of Ethics Vs The Rule Of Law

Sestak had a great reputation in his own right. There was credibility on his side that was hard to overcome by someone who had switched loyalties late in life. Sestak was a very viable opponent, as proven by his victory.

Since it was considere useless to go to Pennsylvania to campaign for Specter, the next best thing was considered. They needed to get Sestak to not run for the senate and to stay in the House.

It was decided that Sestak might consider a special appointment within the White House that would give him access to the President. It would also ensure that his seat in the House would remain.

However, the congressional code of ethical conduct would not allow an incentive to be offered to a potential candidate to get him to reconsider a political run. Nor would it allow the White House staff to offer a position directly or indirectly that could ultimately sway the outcome of an election in any state.

After careful consideration and counsel by legal experts within the White House, it was decided that Rahm Emmanuel could use an emissary to approach Sestak. The emissary could feel out the potential for a position that would entice Sestak to not run.

Emmanuel contacted former President Bill Clinton to make the offer to Joe Sestak. Since Clinton had awarded Sestak the rank of Admiral in the Navy under his administration, it was thought he would have a special connection with him.

Clinton made the call. The offer was presented to Joe Sestak of a position on a special internal committee with access to the President. Sestak refused the offer.


That should be the end of the story – Right? Wrong! That old culprit, ethics vs the rule of law, reared its ugly head and called the White House to task over the procedure.

According to law, neither a direct or indirect offer by the White House staff can be made that could effect any election. Obviously the position offered even though through an emissary is allegedly a direct violation of this law.

Ethically, was it wrong for the White House to make such an offer? The answer given is that it was politics as usual. Should politics as usual bypass the rule of the law and throw it up for public debate on the merits of the law?

The White House law counsel weighed in on the subject and gave the same answer. It was politics and has always been done in this way.

Several politicians from both sides of the aisle have called for a special investigation either by special counsel or by the FBI to see if violations of the law existed.

What God Says About Ethics Vs The Rule Of Law

James 5:12 says, “Above all, my brothers, do not swear – not by heaven or by earth or by anything else. Let your “Yes” be yes and your “No", no, or you will be condemned.”

Many would ask what this has to do with ethics or abiding by the law. I would submit that it has everything to do with it. Why else would we seek to give evasive answers to the simplest questions regarding ethics vs the rule of law?

Politicians are experts at using double talk. They can speak without saying anything. Their actions are not up for debate if they do not declare themselves. They skirt issues to the nth degree, avoiding contact with the truth.

Lawyers have spent their entire careers studying the use of words. They use words to convey thoughts, laws, and ethical behavior. Politicians on the other hand, have studied legalese. Legalese is the art of addressing a wrong with words and then wording it so the wrongdoer has a chance at absolution.

In the deep recesses of their thinking, they configure words to give themselves wiggle room. Does God give wiggle room in letting our "yes be yes" and our "no be no". NO!


What we have today in politics and in life in general are those who want to walk the line so closely they can feel good about themselves. They want to walk so closely they can not be scrutinized when they champion the use of half truths.

Romans 13:1 says, “Everyone must submit himself to the governing authorities, for there is no authority except that which God has established. The authorities that exist have been established by God.”

Do you see anywhere in that verse that it is OK to circumvent the law by the excuse of “everyone does it". I am being facetious. We can do nothing other than serve God through the governing authorities that have been placed over us.

I know that we have certain laws on the books that grant rights, such as abortion, that are contrary to God’s Word and some even would say that you have a right to circumvent that law. I would agree wholeheartedly.

You can oppose laws that are in opposition to God’s Word! For example you can choose not to have an abortion. When the law grants you the privilege to do something that is in opposition to God’s Word, then just do not do it. Just choose to follow God.


We are no longer considered a nation under God, nor are we considered a nation that places our trust in God. Obama has even characterized us as not being a Christian nation. The critical truth is that he is addressing the reflection of what we have become -- one nation not under God.

We are in such deep peril. Unless we return to God we are going to be held accountable for our actions and our inaction. Please pray for our nation, our leaders, and ourselves in the pursuit of God's hand not leaving us and His keeping us from evil.

God bless…
Bob Hataway/eChaplain

የደንቆሮ ጩኽት መልሶ መልሶ……

የርሶ ብዕር አስተያየት ተሳትፎ ሕብረተሰባችንን ይጠቅማል ያሉትን አይንፈጉን ገንቢነቱ ቦታ ይኖረዋልና!ማሳሰቢያ፡ ይህ ገጽ የተዘጋጀው የተለያዩ የኅብረተሰባችንን ሀሳብ ለመለዋወጫ እንጂ ለሚሰጡት ማንኛውም አስታየቶች በማንኛውም መንገድ ተጠያቂ አይደለም። ጉግል ድርጅትም ኃላፊነት አይወስድም። ኃላፊነቱ በሙሉ የአስታየት ሰጪው ብቻ ነው።


የደንቆሮ ጩኽት መልሶ መልሶ……

የኢትቶጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ደብረ ምህረት ቅዱስ ሚካኤል ደብር በዳላስ፤ የቆዩበት የውስጥ ችግሮቹ አደባብይ ከወጡ ከረም ብለዋል።

እንደተረዳነው ከሆነ ችግሮቹ የተፈጠሩት ከዕምነቱ ሳይሆን፤ ከልባቸው ዕምነቱን ከተቀበሉትና ከአንገት በላይ ዕምነታችን ነው ከሚሉት መካከል ነው። ይኽንን ለማለት ያበቃን፣ አንድ ዕምነት ይዞ የሚከተል የሀይማኖት ተከታይ ሀይማኖቱን መሰረት ያደረገ እንዴት ይለያያል? ከዚኽም በላይ ሀይማኖታዊ ችግሮች ሁሉ የሚፈቱት በሀይማኖታዊ መንፈስና መንገድ መሆኑ እየታወቀ ለምን ወደ ፍርድ ቤት መሄዱ አስፈለገ? የዕምነት ማነስ ወይስ ዕምነተቢስነት? የዕምነት ልዩነት ከሆነስ የእውነተኛ አማኝ ተግባር ለምን ዕምነቱን ለፈተና እንዲሁም ለአለም ፍርድ ይሰጣል? የትኛው የክርስትና ዕምነት ነው ወይስ በነቢያት ነውስ ወይ በሐዋርያት፣ በህግ፣ በቅዱስ መጻህፍት አሊያም በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ዕምናትና ህግ ልዩነታችሁን በፍርድ ቤት አድርጉት የሚል? በደብሩ የሀይማኖት ተግባር የተቃረኑ ከሆኑ ለምን እራሳቸውን እንደቃሉ አይለዩም? እራሳቸውንም ሐዋሪያት ወይስ የሀይማኖት አርበኛ እያደረጉ ነውን?

በዚህ ወቅትና ሀገር እየኖርን ያስገረመን ነገር ቢኖር፤ በፍርድ ቤት እራሳቸውን ሽማግሌ ብለው ለደብሩ ከሳሾችና ጸረ ሀይማኖቱ ምግባር ላይ ላሉ ግለሰቦች ዕማኝነት የቀረቡት ግለሰብ ቀደም ሲል ለደብሩ የከሸፈ አዲስ ሕግ አውጭ ብቻ ሳይሆኑ በፍርድ ቤት ላይ ተይዞ ባለ ጉዳይ ላይ ፤ ከሳሽም ሆነ ተከሳሽ (ደብሩ) የሕግ ጠበቃ ይዘው እየተካሄደ ባለ ሂደት ውስጥ፣ ያለሁለቱም ወገን ጠበቃ እውቅና ውጭ፣ ተከሳሽ ክሱን ሳይሰርዝ፣ የሕግን መንፈስ በተቃረነ መንገድ ላስታርቅ እያሉ በተመሳሳይ መንገድ ሲንቀሳቀሱ ጊዜን ማስቆጠራቸው ብቻ ሳይሆን ስራ ፈትተው ቦርዱንም ስራ እያስፈቱ ይገኛሉ። የዚህ እኩይ ምግባር ግምባር ቀድም ተሳታፊ ግለሰቦች ውስጥ የሚከተሉት ስሞች ይገኙበታል።

1ኛ፡ አቶ ተፈራወርቅ አሰፋ ሊቀመንበር
2ኛ፡ አቶ ግርማቸው አድማሴ ም/ሊቀመንበር
3ኛ፡ አቶ ብርሃነማርቆስ ታደሰ ፀሐፊ
4ኛ፡ አቶ ሳሙኤል ደንቢ ፈረጃ ቃለ ጉባኤና የእቅድ ሥራ
5ኛ፡ ዲ/ን አርአያ ኃይለመስቀል የኃይማኖት አማካሪ
6ኛ፡ አቶ ንጉሤ ጀንበሩ የፍትሕና የሕግ Aማካሪ
7ኛ፡ አቶ ቢራቱ ዎዳ የፍትሕና የሕግ አማካሪ
8ኛ፡ አቶ ደመላሽ ደበበ የሕዝብ ግንኙነት
9ኛ፡ ወ/ሮ በየነች መኮንን የሕዝብ ግንኙነት 2

እነዚህና መስሎቻቸው ያወጡት መግለጫና ውሳኔ ምግባርም ቢሆን ጸረ ሀይማኖታዊ ብቻ ሳይሆን ጸረ ደብርም ጭምር ነው። በአውኑ ሰአት የደብሩ ቦርድ ተመዘበረ የተባለውን ገንዘብ በውጭ የሂሳብ መርማሪ እንዳይመረምር ለማደናቀፍ ፣ በአውኑ ሰአት ግምቱ ወደ መቶ ሺህ ዶላር ይጠጋል ተብሎ የ ሚገመተውን የህግ አማካሪ ወጭ በተፈረደባቸው መሰረት ከከሳሾች ላይ በሕግ ጠይቆ እንዳያስመልስ ለማድረግ፣ጠንካራና ጥሩ ስራዎችን በዚህ አስቸጋሪ ወቅትና የስም ማጥፋት ዘመቻ ያሸነፋቸውን ቦርድ ለማፍረስ የሚካሄድ ብሎም ቤት ክርስትያኑን ካልቻሉ ማዘጋት መሆኑ በግልጽ ኣየታየ የመጣ ሀቅ ሆናል። ሙሉ ዝርዝሩን ከዚህ በከሳሽ ወገን ከሚዘጋጅ ገጽ ያንቡትና አስታየቶን ያካፍሉን።
http://merewametta.blogspot.com/
THURSDAY, MAY 27, 2010 ወደ መጨረሻው ላይ ይገኛል።

Thursday, June 3, 2010

የዳላስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ደብረ ምህረት ቅዱስ ሚካኤል ደብር እንደምን ከረመ?

የርሶ ብዕር አስተያየት ተሳትፎ ሕብረተሰባችንን ይጠቅማል ያሉትን አይንፈጉን ገንቢነቱ ቦታ ይኖረዋልና!ማሳሰቢያ፡ ይህ ገጽ የተዘጋጀው የተለያዩ የኅብረተሰባችንን ሀሳብ ለመለዋወጫ እንጂ ለሚሰጡት ማንኛውም አስታየቶች በማንኛውም መንገድ ተጠያቂ አይደለም። ጉግል ድርጅትም ኃላፊነት አይወስድም። ኃላፊነቱ በሙሉ የአስታየት ሰጪው ብቻ ነው።


የዳላስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ደብረ ምህረት ቅዱስ ሚካኤል ደብር እንደምን ከረመ?

እንደምንሰማው ከሆነ ደብሩ ብዙም ባይሆን ያኮረፉበት ምእመናን አሁንም አሉት። አንዳንድ የቀድሞ የቦርድ አባላት ተመዘበረ ከሚባለው የደብሩ ገንዘብ ጋር ግንኙነት ስላላቸው፣ በቅርቡ ለሚጀመረው የውጭ የሒሳብ አጣሪ ስራ ለማስቆም የተቻላቸውን እየጣሩ ይገኛሉ። ከቶንኮሎቻቸው አንዱ የትውሶ አስተማሪ ለማሳጣት የሚያደርጉት ሴራ እየከሸፈባቸው ይታያል። ግብረ አበሮቻቸው አንዱ ማኅበረ ቅዱሳን ሲሆን፣ መናፍቅ እያለ የስም ማጥፋቱን ቢቀጥልም ገና የቃላቱ ‘መናፍቅ‘ ትርጉም ያወቀው ሆኖ አልተገኘምና ዘመቻው ሁሉ አልሰራለትም። እንዲያውም በMAY 18, 2010 የፍርድ ቤቱ ጉዳይ ሲሰማ፤ ይኽው ድርጅት አባላት በደብሩ ረብሻ ወቅት ከቤተክርስትያኑ ፎቅ ላይ የስው ልጅ ሊወረውሩ መዶለታቸው በምስክር ከተረጋገጠባቸው ወዲህ ቀልብ ስላጡ ያተረፉት ስም ታላባን፣ ከልት፣ አክራሪ ና ወንጀለኛ ነው።

ደብሩም የተሰለፉበትን የውስጥና የውጭ ጠላቶቹን አስመልክቶ በዚህ ሳምንት ምህላ ላይ ይገኛል። አዲስ መምህር ለመቅጠርም የመጨረሻ ዝግጅቱን እያጠናቀቀ ሲሆን ከዚህ በኃላ የሚቀጠሩ ሁሉ በኮንትራት ሆኖ በየጊዜው እየተገመገመ የሚታደስ በመሆኑ አባሎቻቸውን ሁሉ አስደስቶ ይገኛል።

የርሶን አስተያየት ያክሉበት ዘንድ እንጋብዞታለን።

Tuesday, June 1, 2010

የርሶ ብዕር አስተያየት ተሳትፎ ሕብረተሰባችንን ይጠቅማል ያሉትን አይንፈጉን ገንቢነቱ ቦታ ይኖረዋልና!ማሳሰቢያ፡ ይህ ገጽ የተዘጋጀው የተለያዩ የኅብረተሰባችንን ሀሳብ ለመለዋወጫ እንጂ ለሚሰጡት ማንኛውም አስታየቶች በማንኛውም መንገድ ተጠያቂ አይደለም። ጉግል ድርጅትም ኃላፊነት አይወስድም። ኃላፊነቱ በሙሉ የአስታየት ሰጪው ብቻ ነው።

የማኅበረ ቅዱሳን ስብሰባ አጭር መግለጫ

http://selam-tewahedo.blogspot.com/2010/06/blog-post.html

በዚህ ገጽ ገብተው በቅርቡ ስለተጠናቀቀው የማኅበረ ቅዱሳን ስብሰባ አጭር መግለጫ ሊመለከቱ ይችላሉ።

በመግልጫው መጨረሻ “ በዚህ ጉባዬ ማህበረ ቅዱሳን በኢትዮጵያም ሆነ በውጭው አለም ለቤተክርስትያኒቱ ያበረከተውንና እያበረከተ ያልው የሙያ፣ የገንዘብ፣ የጉልበትና የስብከተ ወንጌል አገልግሎት በእውነተኛነቱ የቤተክርስትያን ልጅች ሁሉ እንዲወደድና እንዲደገፍ ያደረገው ቢሆንም የቤተክርስትያናችን መሰረታዊ ጠላቶች የሆኑ መናፍቃንና አስመሳይ ፖለቲከኞች ግን የስም ማጥፋት ስራዎችን እንደተያያዙትም ተገልጣል። ይሁን እንጂ ሕዝቡም ለመናፍቃን ለነዚህ አስመሳይ ፖለቲከኞች ፕሮፓጋንዳና የሐሰት ወሬ ጆሮውን እንረማይሰጥና ዳግመኛ እንደማይወናበድ ውስጣዊ ስሜቱን በቁጭትና በቃላት ገልጣል።“
ይላል።

ቁጭትና ቃላትን በክርስትና ቦታ ምን አመጣው? ምን አይነት ድርጅት ይመስሎታል? ለመሆኑ በMAY 02, 2010 የዳላስ ደብረ ምህረት ቅዱስ ሚካኤል ካቴድራል ውስጥ ለተፈጠረው ችግር የዚህ ድርጅት አቁዋም ምን ይሆን ይላሉ?